TG Telegram Group & Channel
Commercial Bank of Ethiopia - Official | United States America (US)
Create: Update:

አላግባብ የወሰዱትን ገንዘብ ሙሉ በሙሉ ያልመለሱ ግለሰቦች የስም ዝርዝር እና የተሰጠ የመጨረሻ ማሳሰቢያ!
******************
በባንኩ የሲስተም ማዘመኛ ሥራ ላይ የተፈጠረውን ክፍተት በመጠቀም መጋቢት 6 ቀን 2016 ዓ.ም. በሂሳብችሁ ከተቀመጠ ገንዘብ ውጭ በሕገወጥ መንገድ ገንዘብ የወሰዳችሁ ግለሰቦች በፈቃደኝነት ሂሳባችሁ በሚገኝበት ቅርንጫፍ በአካል በመቅረብ ወይም ዲጂታል የክፍያ ዘዴን በመጠቀም ገንዘቡን እስከ ቅዳሜ መጋቢት 14 ቀን 2016 ዓ.ም. ተመላሽ የምታደርጉበትን ዕድል ባንካችን ማመቻቸቱ ይታወቃል።

በዚህ መሰረት 14,441 የሚሆኑ ግለሰቦች በተሰጠው ጊዜ ገደብ ተጠቅመው የወሰዱትን ገንዘብ ሙሉ በሙሉ እና በከፊል መልሰዋል፡፡
ሆኖም ከዚህ በታች ስማችሁ፣ የሂሳብ ቁጥራችሁ እና ሂሳባችሁ የሚገኝበት ቅርንጫፍ የተዘረዘረው 565 ግለሰቦች ባንኩ የሰጠውን ዕድል በመጠቀም ያላግባብ የወሰዳችሁትን ገንዘብ አለመመለሳችሁ ታውቋል።

ባንኩ ቀደም ሲል ባስጠነቀቀው መሠረት ወደ ቀጣዩ ሕጋዊ እርምጃ ከማለፉ በፊት ገንዘቡን በአፋጣኝ እንድትመልሱ አንድ ተጨማሪ ዕድል የሰጣችሁ በመሆኑ እስከ ቅዳሜ መጋቢት 21 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ 11 ሰዓት ድረስ ገንዘቡን በምትመልሱት ላይ በባንኩ በኩል ቀጣይ ሕጋዊ እርምጃ እንደማይኖር ያረጋግጣል።

ነገር ግን እስከተጠቀሰው ቀን ገንዘቡን የማትመልሱ ካላችሁ ግን የተለያዩ የመገናኛ ብዙኃን ዘዴዎችን በመጠቀም ሙሉ ስማችሁን፣ ፎቷችሁን፣ በሕገ ወጥ መንገድ ገንዘብ በመውሰድ ወንጀል መጠርጠራችሁን ጠቅሰን ለሚመለከታቸው የሕግ አካላትና ተቋማት በማሳወቅ ለሕዝብ ይፋ እንደሚደረግ ፤ እንዲሁም ከሕግ አካላትና ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር በመተባበር ቀጣይ የወንጀል፣ የፍትሐ ብሔርና የአስተዳደር ሕጋዊ እርምጃዎች እንደሚወሰድባችሁ ለመጨረሻ ጊዜ እናሳስባለን።

መጋቢት 17 ቀን 2016 ዓ.ም.

የስም ዝርዝሩን ለማየት የሚከተለውን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ፡

https://combanketh.et/cbeapi/uploads/New_No_repayment_alphabet_e1dcbe678e.pdf

አላግባብ የወሰዱትን ገንዘብ ሙሉ በሙሉ ያልመለሱ ግለሰቦች የስም ዝርዝር እና የተሰጠ የመጨረሻ ማሳሰቢያ!
******************
በባንኩ የሲስተም ማዘመኛ ሥራ ላይ የተፈጠረውን ክፍተት በመጠቀም መጋቢት 6 ቀን 2016 ዓ.ም. በሂሳብችሁ ከተቀመጠ ገንዘብ ውጭ በሕገወጥ መንገድ ገንዘብ የወሰዳችሁ ግለሰቦች በፈቃደኝነት ሂሳባችሁ በሚገኝበት ቅርንጫፍ በአካል በመቅረብ ወይም ዲጂታል የክፍያ ዘዴን በመጠቀም ገንዘቡን እስከ ቅዳሜ መጋቢት 14 ቀን 2016 ዓ.ም. ተመላሽ የምታደርጉበትን ዕድል ባንካችን ማመቻቸቱ ይታወቃል።

በዚህ መሰረት 14,441 የሚሆኑ ግለሰቦች በተሰጠው ጊዜ ገደብ ተጠቅመው የወሰዱትን ገንዘብ ሙሉ በሙሉ እና በከፊል መልሰዋል፡፡
ሆኖም ከዚህ በታች ስማችሁ፣ የሂሳብ ቁጥራችሁ እና ሂሳባችሁ የሚገኝበት ቅርንጫፍ የተዘረዘረው 565 ግለሰቦች ባንኩ የሰጠውን ዕድል በመጠቀም ያላግባብ የወሰዳችሁትን ገንዘብ አለመመለሳችሁ ታውቋል።

ባንኩ ቀደም ሲል ባስጠነቀቀው መሠረት ወደ ቀጣዩ ሕጋዊ እርምጃ ከማለፉ በፊት ገንዘቡን በአፋጣኝ እንድትመልሱ አንድ ተጨማሪ ዕድል የሰጣችሁ በመሆኑ እስከ ቅዳሜ መጋቢት 21 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ 11 ሰዓት ድረስ ገንዘቡን በምትመልሱት ላይ በባንኩ በኩል ቀጣይ ሕጋዊ እርምጃ እንደማይኖር ያረጋግጣል።

ነገር ግን እስከተጠቀሰው ቀን ገንዘቡን የማትመልሱ ካላችሁ ግን የተለያዩ የመገናኛ ብዙኃን ዘዴዎችን በመጠቀም ሙሉ ስማችሁን፣ ፎቷችሁን፣ በሕገ ወጥ መንገድ ገንዘብ በመውሰድ ወንጀል መጠርጠራችሁን ጠቅሰን ለሚመለከታቸው የሕግ አካላትና ተቋማት በማሳወቅ ለሕዝብ ይፋ እንደሚደረግ ፤ እንዲሁም ከሕግ አካላትና ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር በመተባበር ቀጣይ የወንጀል፣ የፍትሐ ብሔርና የአስተዳደር ሕጋዊ እርምጃዎች እንደሚወሰድባችሁ ለመጨረሻ ጊዜ እናሳስባለን።

መጋቢት 17 ቀን 2016 ዓ.ም.

የስም ዝርዝሩን ለማየት የሚከተለውን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ፡

https://combanketh.et/cbeapi/uploads/New_No_repayment_alphabet_e1dcbe678e.pdf


>>Click here to continue<<

Commercial Bank of Ethiopia - Official




Share with your best friend
VIEW MORE

United States America Popular Telegram Group (US)