ሚኒስትሩ በሙሉ ጤንነት ላይ ይገኛሉ ተባለ!
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ካሳሁን ጎፌ የመኪና አደጋ እንደደረሰባቸው በማህበራዊ ሚዲያ መረጃ ሲሰራጭ ሰንብቷል፡፡ ሚኒስትር መ/ቤቱ በጉዳዩ ላይ በሰጠው መግለጫ ሚኒስትሩ የመጂና አደጋ እንደደረሰባቸው አረጋግጧል፡፡
ሰኔ 15 ቀን 2017 ዓ.ም ወደ ቤታቸው በመመለስ ላይ እያሉ ከምሽቱ 1:00 አካባቢ መኖሪያ ቤታቸው የሚገኝበት ካርል አደባባይ ላይ ድንገተኛ የመኪና አደጋ ደርሶባቸው ነበር ያለው ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ፤ በእለቱ ሚኒስትሩ ወደ ሆስፒታል አምርተው በቂ ህክምና እንዳገኙና አሁን በሙሉ ጤንነት ላይ እንደሚገኙ አስታውቋል፡፡
ሚኒስትሩ ከበቂ የጤና እረፍት ቆይታ በኋላ ወደ መደበኛ ስራ ገበታቸው እንደሚመለሱም መግለጫው ጠቁሟል፡፡"እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ ሁነቱን ለርካሽ ፖለቲካዊ ግብ ለመጠቀም ከአውድ ውጪ ባልተረጋገጠ መረጃና በአሉባልታ የሚናፈሰው የማህበራዊ ሚዲያ ዘገባ የተሳሳተና መሰረተቢስ መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ሚኒስቴር አበክሮ ለመግለጽ ይወዳል" ብሏል፤ ሚኒስቴር መ/ቤቱ በማህበራዊ ትስስር ገጹ ባሰፈረው መግለጫ፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
>>Click here to continue<<
