Channel: የመዝሙር ደብተር™
Forwarded from 📚👳♂ORThODOX LIFE19👳♂📚
ሥላሴ ‹‹ቅድስት›› ተብለው በሴት አንቀጽ መጠራታቸው ሴት /እናት/ ልጅዋን መውለዷን እንደማትጠረጥረው ሁሉ ሥላሴም ይህን ዓለም መፍጠራቸውን ስለማይጠረጥሩ ነው፡፡ሁሉም ከእነርሱ፣ ለእነርሱ፣ በእነርሱ ሆኗልና፡፡
ሴት ወይንም እናት ልጅዋ ቢታመምባት እንዲሞትባት አትሻም፤ ሥላሴም ከፍጥረታቸው አንዱ እንኳን በጠላት ዲያብሎስ እንዲገዛባቸው አይፈቅዱም፡፡
ሴት ፈጭታ ጋግራ ቤተሰቦቿን እንደምትመግበው ሥላሴም በዝናብ አብቅለው በፀሐይ አብስለው ፍጥረቱን ሁሉ ስለሚመግቡ ‹‹ቅድስት ሥላሴ›› እያልን እንጠራቸዋለን፡፡
የቅድስት ሥላሴ ምህረትና ቸርነት አይለየን🙏
╭══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|:══╮
@ORTHODOX_LIFE19
╰══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|:══╯
ሴት ወይንም እናት ልጅዋ ቢታመምባት እንዲሞትባት አትሻም፤ ሥላሴም ከፍጥረታቸው አንዱ እንኳን በጠላት ዲያብሎስ እንዲገዛባቸው አይፈቅዱም፡፡
ሴት ፈጭታ ጋግራ ቤተሰቦቿን እንደምትመግበው ሥላሴም በዝናብ አብቅለው በፀሐይ አብስለው ፍጥረቱን ሁሉ ስለሚመግቡ ‹‹ቅድስት ሥላሴ›› እያልን እንጠራቸዋለን፡፡
የቅድስት ሥላሴ ምህረትና ቸርነት አይለየን
╭══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|:══╮
@ORTHODOX_LIFE19
╰══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|:══╯
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Forwarded from 👳♂ዝክረ ቅዱሳን ቅዱሳን👳♂
✝እንኳን አደረሰነ!
☞ወርኀ ሰኔ ቡሩክ፤ ወአመ ፱፦
✝ቅድስት ጾመ ሐዋርያት (ንጹሐን)
✝ወበዓለ ቅዱሳን፦
✿ኃያል ወመስተጋድል ማር መርቆሬዎስ ዘሮሜ (በዓለ ፍልሠቱ)
✿ቅዱስ ሳሙኤል ዐቢይ ነቢይ (ወልዳ ለሐና ነቢይት)
✿ቅዱስ ሉክያኖስ ሰማዕት
✿ቅድስት ዕሌኒ ንግሥት
✿፬ቱ ሰማዕታት
✿ዮሐንስ ወአርልክሳ ጳጳስ
❖ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤
ኪያነኒ ይምሐረነ በጸሎቶሙ።
ወበረከቶሙ ይብጽሐነ፤ ለዓለመ ዓለም አሜን
╭══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|:══╮
@zkre_kdusan21
╰══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|:══╯
☞ወርኀ ሰኔ ቡሩክ፤ ወአመ ፱፦
✝ቅድስት ጾመ ሐዋርያት (ንጹሐን)
✝ወበዓለ ቅዱሳን፦
✿ኃያል ወመስተጋድል ማር መርቆሬዎስ ዘሮሜ (በዓለ ፍልሠቱ)
✿ቅዱስ ሳሙኤል ዐቢይ ነቢይ (ወልዳ ለሐና ነቢይት)
✿ቅዱስ ሉክያኖስ ሰማዕት
✿ቅድስት ዕሌኒ ንግሥት
✿፬ቱ ሰማዕታት
✿ዮሐንስ ወአርልክሳ ጳጳስ
❖ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤
ኪያነኒ ይምሐረነ በጸሎቶሙ።
ወበረከቶሙ ይብጽሐነ፤ ለዓለመ ዓለም አሜን
╭══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|:══╮
@zkre_kdusan21
╰══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|:══╯
Forwarded from 📚👳♂ORThODOX LIFE19👳♂📚
የሰማያት ወዳጆቻችንና ቅዱሳን ሁሉ በአንተ ዙርያ ሁነው ስለ አንተ እንደሚማልዱም እወቅ።
╭══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|:══╮
@ORTHODOX_LIFE19
╰══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|:══╯
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Forwarded from 🎤✨ድምፀ ተዋሕዶ✨🎤
በማኅበራዊ ሚዲያ በመልቀቅ የሚታወቀው አቶ ትዝታው ሳሙኤል ላይ ክስ ተመሰረተ !
ሰኔ 10 ቀን 2017 ዓ.ም [ተ.ሚ.ማ/ አዲስ አበባ]
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ላይ የጥላቻ ንግግሮችን በማኅበራዊ ሚዲያ በመልቀቅ የሚታወቀው አቶ ትዝታው ሳሙኤል ላይ ክስ ተመሰረተ።
በዛሬው ዕለት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሕግ አገልግሎት መምሪያ ለኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ባቀረበው ክስ የወንጀል ምርመራ ተደርጎ የምርመራ መዝገቡ መብቱ ለሚፈቅድለት የዐቃቢ ሕግ ዘርፍ እንዲተላለፍ ጠይቋል።
የቤተ ክርስቲያኒቱ የበላይ ውሳኔ ሰጪ አካልን ለማዋረድ፣ለመስደብ እና የምእመኑን ስሜት ለመንካት ብሎም በሀገሪቱ ውስጥ ሁከትና ብጥብጥ እንዲነሳ በማሰብ በተለያዩ የመረጃ ማሰራጫ መንገዶች እና ከ5000 በላይ ተከታዮች ባሉት የራሱ የዪቲዩብ ቻናል በውጪ ሀገር ሆኖ ከፍተኛ ቅስቀሳ ሲያደርግ መቆየቱን ገልጿል።
በተጨማሪም ቅድስትቤተክርስቲያንን “የመተት እና ጠንቋይ ቤት ናት” በማለት ሲቀሰቅስ መቆየቱን የሕግ መምሪያው አስታውቋል።
በማያያዝም ግለሰቡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ብፁዓን አባቶችን፣በየገዳማቱ ውስጥ የሚገኙ ገዳማውያን መነኮሳትና አገልጋዮችን ክብረ ክህነት የሚያቃልል ንግግሮችን ሲናገር እንደነበረም በክሱ ላይ አስታውሷል።
በክሱ ላይ አያይዞ መምሪያው እንደገለጸው ቤተ ተክርስቲያኒቱ የምትገለገልባቸውን ሃይማኖታዊ የጸሎት፣የታሪክ ፣የገድላትና ድርሳናት መጻሕፍትን “ድውያን መጽሐፍት ናቸው መጥፋት አለባቸው” ማለቱን ገልጿል።
ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን በቅድስና የምታከብራቸውንና የምትዘክራቸውን ቅዱሳን አባቶች እና እናቶችን “ጣኦታትና ጣኦት አምላኪ ናቸው” በማለት ግለሰቡ ወንጀል መፈጸሙንም በመሰረተው ክስ ላይ ጠቅሷል።
በአጠቃላይ ሰባት ነጥቦችን ያካተቱ የወንጀል ዝርዝሮችን በመግለጽም ጉዳዩ ለሚመለከተው አካል ቀርቦ ግለሰቡ በሕግ ተጠያቂ እንዲደረግ አቤቱታውን አቅርቧል።
መረጃው:- የ/ኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ነው።
#ድምፀ_ተዋህዶ
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
@News_Tewahdo
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══╯
ሰኔ 10 ቀን 2017 ዓ.ም [ተ.ሚ.ማ/ አዲስ አበባ]
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ላይ የጥላቻ ንግግሮችን በማኅበራዊ ሚዲያ በመልቀቅ የሚታወቀው አቶ ትዝታው ሳሙኤል ላይ ክስ ተመሰረተ።
በዛሬው ዕለት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሕግ አገልግሎት መምሪያ ለኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ባቀረበው ክስ የወንጀል ምርመራ ተደርጎ የምርመራ መዝገቡ መብቱ ለሚፈቅድለት የዐቃቢ ሕግ ዘርፍ እንዲተላለፍ ጠይቋል።
የቤተ ክርስቲያኒቱ የበላይ ውሳኔ ሰጪ አካልን ለማዋረድ፣ለመስደብ እና የምእመኑን ስሜት ለመንካት ብሎም በሀገሪቱ ውስጥ ሁከትና ብጥብጥ እንዲነሳ በማሰብ በተለያዩ የመረጃ ማሰራጫ መንገዶች እና ከ5000 በላይ ተከታዮች ባሉት የራሱ የዪቲዩብ ቻናል በውጪ ሀገር ሆኖ ከፍተኛ ቅስቀሳ ሲያደርግ መቆየቱን ገልጿል።
በተጨማሪም ቅድስትቤተክርስቲያንን “የመተት እና ጠንቋይ ቤት ናት” በማለት ሲቀሰቅስ መቆየቱን የሕግ መምሪያው አስታውቋል።
በማያያዝም ግለሰቡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ብፁዓን አባቶችን፣በየገዳማቱ ውስጥ የሚገኙ ገዳማውያን መነኮሳትና አገልጋዮችን ክብረ ክህነት የሚያቃልል ንግግሮችን ሲናገር እንደነበረም በክሱ ላይ አስታውሷል።
በክሱ ላይ አያይዞ መምሪያው እንደገለጸው ቤተ ተክርስቲያኒቱ የምትገለገልባቸውን ሃይማኖታዊ የጸሎት፣የታሪክ ፣የገድላትና ድርሳናት መጻሕፍትን “ድውያን መጽሐፍት ናቸው መጥፋት አለባቸው” ማለቱን ገልጿል።
ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን በቅድስና የምታከብራቸውንና የምትዘክራቸውን ቅዱሳን አባቶች እና እናቶችን “ጣኦታትና ጣኦት አምላኪ ናቸው” በማለት ግለሰቡ ወንጀል መፈጸሙንም በመሰረተው ክስ ላይ ጠቅሷል።
በአጠቃላይ ሰባት ነጥቦችን ያካተቱ የወንጀል ዝርዝሮችን በመግለጽም ጉዳዩ ለሚመለከተው አካል ቀርቦ ግለሰቡ በሕግ ተጠያቂ እንዲደረግ አቤቱታውን አቅርቧል።
መረጃው:- የ/ኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ነው።
#ድምፀ_ተዋህዶ
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
@News_Tewahdo
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══╯
Forwarded from 📚👳♂ORThODOX LIFE19👳♂📚
✟ ወተጠየቀ ውእቱ ባሕራን ከመ መልአከ ክቡር ሚካኤል ሊቀ መላዕክት ውእቱ ዘአስተርአዮ ሎቱ በውስተ ፍኖት ወነፍሐ ውስተ መልእክተ ወደምስስ ዘውስቴቱ ወጸሐፈ ሎቱ ህየንቴሁ መልእክተ ሕይወት
ባሕራንም በመንገድ የታየው በደብዳቤው ውስጥ የተፃፈውን አጥፍቶ በለውጡ የሕይወትን መልእክት የጻፈለት የመላዕክት አለቃ ክቡር መልአኩ ሚካኤል እንደሆነ ተረዱ
✤ የመልክዐ ሚካኤል ደራሲ አባ ዮሐንስ ዘአክሱም ✤
ሰላም እብል ለአስናኒከ ዘመንፈስ ዘኢይረክቦን ጥረስ ሚካኤል ረዳኢ ለእለ ውስተ ባሕር ወየብስ እስመ ረስየከ ካህነ ምሥዋዑ ክርስቶስ መፍትው ሊተ ትተንብል ቀሲስ
ሠኔ ፲፪ የቅዱስ ሚካኤል ቀሲሱ ቅዱስ ባሕራን የረዳበት ዕለት ነው
ቅዱስ ባሕራን ቀሲስ
❖ ወበዛቲ ዕለት ካዕበ ኮነ ዕረፍታ ለቅድስት አፎምያ ❖
በዚች ቀን የከበረች አፎምያ ያረፈችበት ነው
✥ የድርሳነ ሚካኤል እና የመልክዐ ሚካኤል ደራሲ አባ ዮሐንስ ዘአክሱም ✥
ሰላም ለመልክዕከ ዘኢይጤየቅ ለዓይንነ ኆኀያቲሁ ርቡዐ በከመ ርኢነ ሚካኤል የዋህ እኀወ ማርያም እምነ ዘርግብ አክናፊከ ክድነነ እሞት ውስተ ሕይወት እግዚኦ መርሐነ
ሠኔ ፲፪ ቀን የቅዱስ ሚካኤል ወዳጅ የቅዱስ አስተራኒቆስ ሚስት ቅድስት አፎምያ የዕረፍቷ መታሰቢያ ነው
በረከቷ ይደርብን
✍️ መነ ትብል ርዕሰከ✍️ ፳፻፲፯ ዓ.ም
╭══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|:══╮
@ORTHODOX_LIFE19
╰══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|:══╯
ባሕራንም በመንገድ የታየው በደብዳቤው ውስጥ የተፃፈውን አጥፍቶ በለውጡ የሕይወትን መልእክት የጻፈለት የመላዕክት አለቃ ክቡር መልአኩ ሚካኤል እንደሆነ ተረዱ
✤ የመልክዐ ሚካኤል ደራሲ አባ ዮሐንስ ዘአክሱም ✤
ሰላም እብል ለአስናኒከ ዘመንፈስ ዘኢይረክቦን ጥረስ ሚካኤል ረዳኢ ለእለ ውስተ ባሕር ወየብስ እስመ ረስየከ ካህነ ምሥዋዑ ክርስቶስ መፍትው ሊተ ትተንብል ቀሲስ
ሠኔ ፲፪ የቅዱስ ሚካኤል ቀሲሱ ቅዱስ ባሕራን የረዳበት ዕለት ነው
ቅዱስ ባሕራን ቀሲስ
❖ ወበዛቲ ዕለት ካዕበ ኮነ ዕረፍታ ለቅድስት አፎምያ ❖
በዚች ቀን የከበረች አፎምያ ያረፈችበት ነው
✥ የድርሳነ ሚካኤል እና የመልክዐ ሚካኤል ደራሲ አባ ዮሐንስ ዘአክሱም ✥
ሰላም ለመልክዕከ ዘኢይጤየቅ ለዓይንነ ኆኀያቲሁ ርቡዐ በከመ ርኢነ ሚካኤል የዋህ እኀወ ማርያም እምነ ዘርግብ አክናፊከ ክድነነ እሞት ውስተ ሕይወት እግዚኦ መርሐነ
ሠኔ ፲፪ ቀን የቅዱስ ሚካኤል ወዳጅ የቅዱስ አስተራኒቆስ ሚስት ቅድስት አፎምያ የዕረፍቷ መታሰቢያ ነው
በረከቷ ይደርብን
✍️ መነ ትብል ርዕሰከ✍️ ፳፻፲፯ ዓ.ም
╭══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|:══╮
@ORTHODOX_LIFE19
╰══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|:══╯
Forwarded from 🎤✨ድምፀ ተዋሕዶ✨🎤
ብፁዕ አቡነ ይስሐቅ የወላይታ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በአረካ ከተማ ለሚገነባው የቅዱስ ሚካኤል ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን የመሠረት ድንጋይ አስቀመጡ !
ሰኔ 12 ቀን 2017 ዓ.ም [ተ.ሚ.ማ/ አዲስ አበባ]
ብፁዕ አቡነ ይስሐቅ የወላይታ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በወላይታ ሀገረ ስብከት በቦሎሶ ሶሬ ወረዳ ቤተ ክህነት አረካ ከተማ ደብረ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን አዲስ ለሚገነባው ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ግንባታ የመሠረት ድንጋይ በዛሬው ዕለት አስቀምጠዋል።
ብፁዕነታቸው በዛሬው ዕለት የሚከበረውን የቅዱስ ሚካኤል በዓልን ምክንያት በማድረግ ወደ አረካ ደብረ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ያደረጉ ሲሆን በበዓሉ የተገኙ በርካታ ምእመናንን ወንጌል አስተምረው አባታዊ ቃለ ምዕዳን እና ቡራኬ ሰጥተዋል።
በመጨረሻም ብፁዕነታቸው አሁን አገልግሎት እየሰጠ የሚገኘው ቤተ ክርስቲያን በማርጀቱ ምክንያት አዲስ ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ለመስራት በማቀድ ሰበካ ጉባኤው ባቀረበው ጥያቄ መሠረት ለግንባታው መሠረት ድንጋይ በማስቀመጥ ሁሉም አካል ትብብርና ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል።
#ዜና_ተዋሕዶ
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
@News_Tewahdo
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══╯
ሰኔ 12 ቀን 2017 ዓ.ም [ተ.ሚ.ማ/ አዲስ አበባ]
ብፁዕ አቡነ ይስሐቅ የወላይታ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በወላይታ ሀገረ ስብከት በቦሎሶ ሶሬ ወረዳ ቤተ ክህነት አረካ ከተማ ደብረ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን አዲስ ለሚገነባው ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ግንባታ የመሠረት ድንጋይ በዛሬው ዕለት አስቀምጠዋል።
ብፁዕነታቸው በዛሬው ዕለት የሚከበረውን የቅዱስ ሚካኤል በዓልን ምክንያት በማድረግ ወደ አረካ ደብረ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ያደረጉ ሲሆን በበዓሉ የተገኙ በርካታ ምእመናንን ወንጌል አስተምረው አባታዊ ቃለ ምዕዳን እና ቡራኬ ሰጥተዋል።
በመጨረሻም ብፁዕነታቸው አሁን አገልግሎት እየሰጠ የሚገኘው ቤተ ክርስቲያን በማርጀቱ ምክንያት አዲስ ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ለመስራት በማቀድ ሰበካ ጉባኤው ባቀረበው ጥያቄ መሠረት ለግንባታው መሠረት ድንጋይ በማስቀመጥ ሁሉም አካል ትብብርና ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል።
#ዜና_ተዋሕዶ
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
@News_Tewahdo
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══╯
Forwarded from 🎤✨ድምፀ ተዋሕዶ✨🎤 (☦ማኔ ቴቄል ፋሪስ☦)
በሶርያ ምሥራቅ ደማስቆ በቅዱስ ኤልያስ የግሪክ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ላይ የሽብር ጥቃት ደረሰ
ሰኔ 15 ቀን 2025 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ)
ከደማስቆ በስተምሥራቅ በድዋይሌህ አካባቢ የሚገኘው የቅዱስ ኤልያስ የግሪክ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በቅዳሴ ላይ በነበሩበት ወቅት ኢላማ የተደረገ ሲሆን በጥቃቱ ከ15 በላይ ሰዎች ሲሞቱ በትንሹ 20 ሰዎች መቁሰላቸውን የሶሪያ አረብ የዜና አገልግሎት (SANA) እና በርካታ አለም አቀፍ የዜና ወኪሎች ዘግበዋል።
በሩሲያ የዜና አገልግሎት ኖቮስቲ የዘገበው የመጀመርያ ዘገባዎች እንዳመለከቱት አንድ አጥፍቶ ጠፊ በጸሎት ወቅት ወደ ቤተክርስቲያኑ በመግባት በነበሩት ምእመናን ላይ ተኩስ በመክፈት ድንጋጤ ፈጥሯል። ከዚያም የሚፈነዳ ቀበቶ በማፈንዳት ከፍተኛ ፍንዳታ በማድረግ የቤተክርስቲያኑ ክፍሎች ወድሞ የበርካታ ሰዎችን ህይወት ቀጥፏል።
አል-ኢኽባሪያ ቲቪ እንደዘገበው የሀገር ውስጥ የጸጥታ ሃይሎች የጥቃቱን መንስኤ ለማወቅ የወንጀል ምርመራ መጀመሩን ዘግቧል። ይህ በንዲህ እንዳለ የአምቡላንስ እና የሲቪል መከላከያ ቡድን ቁስለኛዎቹን በአቅራቢያው ወደሚገኝ ሆስፒታሎች በማጓጓዝ ከፍተኛ የህክምና ማስጠንቀቂያ መስጠቱ ነው የተገለጸው።
የግሪክ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የቅዱስ ኤልያስ ቤተ ክርስቲያን በደማስቆ እና በአካባቢዋ ከሚገኙት ታዋቂ የክርስቲያን አብያተ ክርስቲያናት አንዱ ነው። ከነቢዩ ኤልያስ ጋር የተቆራኘ በመሆኑ በጥንታዊ እና ታሪካዊነቱ ይታወቃል።
#ዜና_ተዋሕዶ
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
@News_Tewahdo
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══╯
ሰኔ 15 ቀን 2025 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ)
ከደማስቆ በስተምሥራቅ በድዋይሌህ አካባቢ የሚገኘው የቅዱስ ኤልያስ የግሪክ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በቅዳሴ ላይ በነበሩበት ወቅት ኢላማ የተደረገ ሲሆን በጥቃቱ ከ15 በላይ ሰዎች ሲሞቱ በትንሹ 20 ሰዎች መቁሰላቸውን የሶሪያ አረብ የዜና አገልግሎት (SANA) እና በርካታ አለም አቀፍ የዜና ወኪሎች ዘግበዋል።
በሩሲያ የዜና አገልግሎት ኖቮስቲ የዘገበው የመጀመርያ ዘገባዎች እንዳመለከቱት አንድ አጥፍቶ ጠፊ በጸሎት ወቅት ወደ ቤተክርስቲያኑ በመግባት በነበሩት ምእመናን ላይ ተኩስ በመክፈት ድንጋጤ ፈጥሯል። ከዚያም የሚፈነዳ ቀበቶ በማፈንዳት ከፍተኛ ፍንዳታ በማድረግ የቤተክርስቲያኑ ክፍሎች ወድሞ የበርካታ ሰዎችን ህይወት ቀጥፏል።
አል-ኢኽባሪያ ቲቪ እንደዘገበው የሀገር ውስጥ የጸጥታ ሃይሎች የጥቃቱን መንስኤ ለማወቅ የወንጀል ምርመራ መጀመሩን ዘግቧል። ይህ በንዲህ እንዳለ የአምቡላንስ እና የሲቪል መከላከያ ቡድን ቁስለኛዎቹን በአቅራቢያው ወደሚገኝ ሆስፒታሎች በማጓጓዝ ከፍተኛ የህክምና ማስጠንቀቂያ መስጠቱ ነው የተገለጸው።
የግሪክ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የቅዱስ ኤልያስ ቤተ ክርስቲያን በደማስቆ እና በአካባቢዋ ከሚገኙት ታዋቂ የክርስቲያን አብያተ ክርስቲያናት አንዱ ነው። ከነቢዩ ኤልያስ ጋር የተቆራኘ በመሆኑ በጥንታዊ እና ታሪካዊነቱ ይታወቃል።
#ዜና_ተዋሕዶ
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
@News_Tewahdo
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══╯
Forwarded from 🎤✨ድምፀ ተዋሕዶ✨🎤
🥷ከአክራሪ እስልምና ወደ ክርስትና👩⚕
⚫️ ክፍል አንድ 🟡
ስለእውነት ነው የምላችሁ በደንብ አንብቡ በስተመጨረሻ የምታገኙት የመንፈስ ጥንካሬ እንዲህ ነው ማለት አልችልም ብቻ እንድታነቡ የእግዚአብሔር ፈቃደ በእናንተ ላይ ይሁን።
😄 ምዕራፍ አንድ ማን ነበርኩ❓
ናህድ ማሕሙድ ሙትዋሊ እባላለሁ። ሴቶችን ብቻ የሚያስተምረው የሄልሜት ኤል ዘይቱን ትምህርት ቤት ዲን ነበርኩ።
በካይሮ የታወቀ እና ትልቁ ትምህርት ቤት ነው። 4000 ልጃገረዶችን ያስተምራል። ከተማሪዎቹ ብዛት የተነሣ ት/ቤቱ የሚያስተምረው በጥዋት እና በከሰዓት ፈረቃ ነበር።
የት/ቤቱ ዲን እንደመሆኔ መጠን ሁለቱንም ፈረቃዎች መከታተል ነበረብኝ። ምንም እንኳን ከሁሉም ዲኖች በዕድሜ ታናሿ እና በቅርብ ከኮሌጅ የተመረቅኩ ብሆንም ይህንን ወንበር እንዳገኝ ግን ሁለት ነገሮች ረድተውኛል።
እግዚአብሔር ብስለትን፣ በራስ መተማመንን፣ እንዲሁም ኃላፊ ነቴን በሚገባ የመወጣት ችሎታን አድሎኝ ነበር። የማንም ርዳታ ሳያስፈልገኝ የሚሰጠኝን ሥራ ሁሉ በአፋጣኝ የማከናወን ልምድ አለኝ።
ሰወች አንድን ነገር ሲሠሩ መመልከት ብቻ ለእኔ በቂዬ ነበር። ያንኑ ነገር ወዲያውኑ ልምድ እንዳለው ሰው አድርጌ ማከናወን እችላለሁ።
በዚህ ችሎታዬ የተነሣ ይህንን ቦታ ያገኘሁት ቦታውን ላገኘው ከሚገባኝ ዐሥር ዓመታት ቀድም ነበር ከዚህ ችሎታዬ ጋር ተጨምሮ በት/ቤቱ የነበሩትን የሁለቱን ረዳት ዳይሬክተሮች ተግባር የማወቅ ዕድልም ገጥሞኛል። የተማሪዎችን ሰሞች በምሥጢራዊ ኮድ ካገኘኋቸው ዋና ዋና ልምዶች መካከል የሚጠቀሱት ናቸው።
እንዚህ ሁለቱ ተግባራት ደግሞ በት/ቤታችን ውስጥ ዋነኞቹ ሥራዎች ናቸው።
ምክንያቱም ሁለቱም ፍጹም የሆነ ምሥጢር ጠባቂነትን የሚጠይቁ ናቸውና።
አንደኛው ረዳት ዳይሬክተር በ60 ዓመቱ ጡረታ ወጣ፣ ሌላው ደግሞ ወደ ሌላ የዓረብ ሀገር ለሥራ ሄደ።
ይህንን አጋጣሚ በመጠቀምም እነዚህን ሁለቱን ኃላፊነቶች ጠቀለልኳቸው። ይህም የት/ቤቱን ቁሌፍ ቁልፍ አስተዳደራዊ ኃላፈነቶች እንድቆጣጠር ዕድል ከፈተልኝ።
እነዚህን ኃላፊነቶች ከጠቀለልኩ በኃላ ልክ የት/ቤቱ ንግሥት የሆንኩ ያህል ይሰማኝ ነበር።
በእነዚህ ነገሮች ሙሉ ሥልጣን እና ፍጹም የሆነ ኃላፈነት ነበርኝ። ሌላው ቀርቶ የእኔ የበላይ የሆነችው የት/ቤቱ ዳይሬክተር እንኳን በጣም ትቅርበኝ፣ የምትሠራውንም ነገር ሁሉ ታማክረኝ ነበር። የሚፈራ፣ ኃይለኛ፣ አድራጊ ፈጣሪ ሆንኩ።
ለመኞቴ ወሰን አልነበረውም። ለዝቅተኛ ተማሪዎች የሚሰጠውን የትምህርት እገዛ እኔ ራሴ እንድከታለው ኃላፈነቱ እንዲሰጠኝ አስተዳደሩን ጠይቄ ተፈቀደልኝ። በዚህ የተነሣም በየወሩ ከእነዚህ ክፍሎች ለሚሰበሰበው ከ12ሺ-15ሺ ለሚጠጋው ገንዘብ ኃላፊ ሆንኩ። ለዚህ ኃላፊነቴ እንዲሁም ፈተና ለማዘጋጀት እና ለማባዛት ተግባሬ የሚከፈለኝ ገንዘብ ወራኃዊ ገቢዬን በሦስት እጥፍ አሳደገው።
ወደዚህ የሥልጣን እርከን ያሸጋገረኝ ሌላው ነገር ደግሞ የቤተ ሰቦቼ ታዋቂነት እና በመንግሥታዊ ቦታዎች ያላቸው ሥልጣን ነቀር።
ወንድሜ በማዕከላዊው የአስተዳደር እና የአመራር ሥርዓት ቢሮ ውስጥ ሥራ እስኪያጅ ነበር። አንደኛው ዋርሳዬ ደግሞ የማዘጋጃ ቤቱ ጸሐፊ እና የት/ቤቱ የወላጆች እና መምህራን ማኅበር ፕሬዚዳንት ነው።
የእርሱ ሁለቱ ሴቶች ልጆቹም የት/ቤቱ ተማሪዎች ነበሩ።
ሌላው ዋርሳዬ ደግሞ የቤተ መንግሥቱ ፓይለት ነው። እኅቴ የሄልዮፓሊስ አካባቢ የት/ቤቶች አስተዳደር የሕዝብ ግንኙነት ሥራ አስኪያጅ ናት።
ባልዋም በማዕከላዊው የመረጃ አገልግሎት ሹም ነበር። እንዚህ ሁሉ ከእኔ ሰብእና እና በት/ቤቱ ከተፈጠረው ክፍተት ጋር ተደማምረው ከሥልጣን ወደ ሥልጣን አሸጋገሩኝ።
ይህ ሁሉ በሀብት እና በሥልጣን ይጠቀመኝ እንጂ ወስጤን ግን ትዕቢተኛ ፣ ዕብሪተኛ እና ግብዝ አድርጎኛል።
በሌላ በኩል ልቡናዬን ለሚያይ ደግሞ የተለየሁ ፍጥረት ነበርኩ። አምላኬን እወደዋለሁ የምል ቆዳ ስሱ ሰው ነኝ። አዎን ጌታዬ ሆይ ምንም እንኳን ከአንተ ርቄ ብኖርም በፍጹም ልቤ እወድድህ እና እፈራህ ነበርኮ።
እግዚአብሔርን ስፈልገው ኖሬያለሁ፣ እነዚያ የሕይወቴ የተበላሹ ገጽታዎች ግን እርሱን እንዳላገኝው የመከለያ ግንብውቅም ነበር። አብዝቼ እጸልያለሁ፣ ቁርዐንንም አዘውትሬ አነባለሁ ፣ ይሁን እንጂ በውስጤ አንዳች የጎደለ ነገር መኖሩ ይሰማኝ ነበር።
ክርስቲያኖች እኔ የምወደውን አምላክ አይወዱትም ብየ ስለማስብ አብዝቼ እጣላቸው ነበር።
እግዚአብሔርን እኔ በማመልክበት መንገድ ለምን አያመልኩትም? እነርሱ ከእግዚአብሔር የኮበለሉ ናቸው እያልኩ እጅግ እጠላቸው ነበር።
ክርስቲያኖችን ከመጥላቴ የተነሣ እነርሱን ለማዋድ፣ ለመጉዳት እና በእነርሱ ላይ አንዳች ችግር ለመፍጠር ዘወትር እጥር ነበር።
ይህንን የማደርገው ግን በውስጤ ለሰው ክፋት ስላለኝ ሳይሆን የምወደውን እና የማመልከውን አምላክ ለምን አያመልኩም፣ ለምንስ አይወዱም? ብየ ነበር። በርግጥ ሁልጊዜ የሚገርመኝና የሚያሳስበኝ አንድ ነገር አለ።
እኔ ላገኘው የምጓጓለትን ውሳጣዊ ሰላም ክርስቲያኖች ገንዘብ አድርገውታል። እንዴት?
😀 ይቀጥላል
📱 አቅራቢ፦#ድምፀ_ተዋሕዶ
ሼር በማድረግ ለወዳጅ ዘመድዎ ያጋሩ‼️
📱 ሼር // 𝐒𝐇𝐀𝐑𝐄🌐
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
@News_Tewahdo
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══╯
ስለእውነት ነው የምላችሁ በደንብ አንብቡ በስተመጨረሻ የምታገኙት የመንፈስ ጥንካሬ እንዲህ ነው ማለት አልችልም ብቻ እንድታነቡ የእግዚአብሔር ፈቃደ በእናንተ ላይ ይሁን።
ናህድ ማሕሙድ ሙትዋሊ እባላለሁ። ሴቶችን ብቻ የሚያስተምረው የሄልሜት ኤል ዘይቱን ትምህርት ቤት ዲን ነበርኩ።
በካይሮ የታወቀ እና ትልቁ ትምህርት ቤት ነው። 4000 ልጃገረዶችን ያስተምራል። ከተማሪዎቹ ብዛት የተነሣ ት/ቤቱ የሚያስተምረው በጥዋት እና በከሰዓት ፈረቃ ነበር።
የት/ቤቱ ዲን እንደመሆኔ መጠን ሁለቱንም ፈረቃዎች መከታተል ነበረብኝ። ምንም እንኳን ከሁሉም ዲኖች በዕድሜ ታናሿ እና በቅርብ ከኮሌጅ የተመረቅኩ ብሆንም ይህንን ወንበር እንዳገኝ ግን ሁለት ነገሮች ረድተውኛል።
እግዚአብሔር ብስለትን፣ በራስ መተማመንን፣ እንዲሁም ኃላፊ ነቴን በሚገባ የመወጣት ችሎታን አድሎኝ ነበር። የማንም ርዳታ ሳያስፈልገኝ የሚሰጠኝን ሥራ ሁሉ በአፋጣኝ የማከናወን ልምድ አለኝ።
ሰወች አንድን ነገር ሲሠሩ መመልከት ብቻ ለእኔ በቂዬ ነበር። ያንኑ ነገር ወዲያውኑ ልምድ እንዳለው ሰው አድርጌ ማከናወን እችላለሁ።
በዚህ ችሎታዬ የተነሣ ይህንን ቦታ ያገኘሁት ቦታውን ላገኘው ከሚገባኝ ዐሥር ዓመታት ቀድም ነበር ከዚህ ችሎታዬ ጋር ተጨምሮ በት/ቤቱ የነበሩትን የሁለቱን ረዳት ዳይሬክተሮች ተግባር የማወቅ ዕድልም ገጥሞኛል። የተማሪዎችን ሰሞች በምሥጢራዊ ኮድ ካገኘኋቸው ዋና ዋና ልምዶች መካከል የሚጠቀሱት ናቸው።
እንዚህ ሁለቱ ተግባራት ደግሞ በት/ቤታችን ውስጥ ዋነኞቹ ሥራዎች ናቸው።
ምክንያቱም ሁለቱም ፍጹም የሆነ ምሥጢር ጠባቂነትን የሚጠይቁ ናቸውና።
አንደኛው ረዳት ዳይሬክተር በ60 ዓመቱ ጡረታ ወጣ፣ ሌላው ደግሞ ወደ ሌላ የዓረብ ሀገር ለሥራ ሄደ።
ይህንን አጋጣሚ በመጠቀምም እነዚህን ሁለቱን ኃላፊነቶች ጠቀለልኳቸው። ይህም የት/ቤቱን ቁሌፍ ቁልፍ አስተዳደራዊ ኃላፈነቶች እንድቆጣጠር ዕድል ከፈተልኝ።
እነዚህን ኃላፊነቶች ከጠቀለልኩ በኃላ ልክ የት/ቤቱ ንግሥት የሆንኩ ያህል ይሰማኝ ነበር።
በእነዚህ ነገሮች ሙሉ ሥልጣን እና ፍጹም የሆነ ኃላፈነት ነበርኝ። ሌላው ቀርቶ የእኔ የበላይ የሆነችው የት/ቤቱ ዳይሬክተር እንኳን በጣም ትቅርበኝ፣ የምትሠራውንም ነገር ሁሉ ታማክረኝ ነበር። የሚፈራ፣ ኃይለኛ፣ አድራጊ ፈጣሪ ሆንኩ።
ለመኞቴ ወሰን አልነበረውም። ለዝቅተኛ ተማሪዎች የሚሰጠውን የትምህርት እገዛ እኔ ራሴ እንድከታለው ኃላፈነቱ እንዲሰጠኝ አስተዳደሩን ጠይቄ ተፈቀደልኝ። በዚህ የተነሣም በየወሩ ከእነዚህ ክፍሎች ለሚሰበሰበው ከ12ሺ-15ሺ ለሚጠጋው ገንዘብ ኃላፊ ሆንኩ። ለዚህ ኃላፊነቴ እንዲሁም ፈተና ለማዘጋጀት እና ለማባዛት ተግባሬ የሚከፈለኝ ገንዘብ ወራኃዊ ገቢዬን በሦስት እጥፍ አሳደገው።
ወደዚህ የሥልጣን እርከን ያሸጋገረኝ ሌላው ነገር ደግሞ የቤተ ሰቦቼ ታዋቂነት እና በመንግሥታዊ ቦታዎች ያላቸው ሥልጣን ነቀር።
ወንድሜ በማዕከላዊው የአስተዳደር እና የአመራር ሥርዓት ቢሮ ውስጥ ሥራ እስኪያጅ ነበር። አንደኛው ዋርሳዬ ደግሞ የማዘጋጃ ቤቱ ጸሐፊ እና የት/ቤቱ የወላጆች እና መምህራን ማኅበር ፕሬዚዳንት ነው።
የእርሱ ሁለቱ ሴቶች ልጆቹም የት/ቤቱ ተማሪዎች ነበሩ።
ሌላው ዋርሳዬ ደግሞ የቤተ መንግሥቱ ፓይለት ነው። እኅቴ የሄልዮፓሊስ አካባቢ የት/ቤቶች አስተዳደር የሕዝብ ግንኙነት ሥራ አስኪያጅ ናት።
ባልዋም በማዕከላዊው የመረጃ አገልግሎት ሹም ነበር። እንዚህ ሁሉ ከእኔ ሰብእና እና በት/ቤቱ ከተፈጠረው ክፍተት ጋር ተደማምረው ከሥልጣን ወደ ሥልጣን አሸጋገሩኝ።
ይህ ሁሉ በሀብት እና በሥልጣን ይጠቀመኝ እንጂ ወስጤን ግን ትዕቢተኛ ፣ ዕብሪተኛ እና ግብዝ አድርጎኛል።
በሌላ በኩል ልቡናዬን ለሚያይ ደግሞ የተለየሁ ፍጥረት ነበርኩ። አምላኬን እወደዋለሁ የምል ቆዳ ስሱ ሰው ነኝ። አዎን ጌታዬ ሆይ ምንም እንኳን ከአንተ ርቄ ብኖርም በፍጹም ልቤ እወድድህ እና እፈራህ ነበርኮ።
እግዚአብሔርን ስፈልገው ኖሬያለሁ፣ እነዚያ የሕይወቴ የተበላሹ ገጽታዎች ግን እርሱን እንዳላገኝው የመከለያ ግንብውቅም ነበር። አብዝቼ እጸልያለሁ፣ ቁርዐንንም አዘውትሬ አነባለሁ ፣ ይሁን እንጂ በውስጤ አንዳች የጎደለ ነገር መኖሩ ይሰማኝ ነበር።
ክርስቲያኖች እኔ የምወደውን አምላክ አይወዱትም ብየ ስለማስብ አብዝቼ እጣላቸው ነበር።
እግዚአብሔርን እኔ በማመልክበት መንገድ ለምን አያመልኩትም? እነርሱ ከእግዚአብሔር የኮበለሉ ናቸው እያልኩ እጅግ እጠላቸው ነበር።
ክርስቲያኖችን ከመጥላቴ የተነሣ እነርሱን ለማዋድ፣ ለመጉዳት እና በእነርሱ ላይ አንዳች ችግር ለመፍጠር ዘወትር እጥር ነበር።
ይህንን የማደርገው ግን በውስጤ ለሰው ክፋት ስላለኝ ሳይሆን የምወደውን እና የማመልከውን አምላክ ለምን አያመልኩም፣ ለምንስ አይወዱም? ብየ ነበር። በርግጥ ሁልጊዜ የሚገርመኝና የሚያሳስበኝ አንድ ነገር አለ።
እኔ ላገኘው የምጓጓለትን ውሳጣዊ ሰላም ክርስቲያኖች ገንዘብ አድርገውታል። እንዴት?
ሼር በማድረግ ለወዳጅ ዘመድዎ ያጋሩ‼️
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
@News_Tewahdo
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══╯
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
✅❤️የተወለዱበትን ወር በመምረጥ የሚደርሶትን መንፈሳዊ ቻናል በመቀላቀል ዕውቀቶችን ያግኙ
መልካም ዕድል!!!
𝚆𝚊𝚟𝚎 👉 @Beni_tes
https://hottg.com/addlist/A7U6XVGLALJlNjI0
https://hottg.com/addlist/A7U6XVGLALJlNjI0
https://hottg.com/addlist/A7U6XVGLALJlNjI0
መልካም ዕድል!!!
𝚆𝚊𝚟𝚎 👉 @Beni_tes
https://hottg.com/addlist/A7U6XVGLALJlNjI0
https://hottg.com/addlist/A7U6XVGLALJlNjI0
https://hottg.com/addlist/A7U6XVGLALJlNjI0
HTML Embed Code: