TG Telegram Group Link
Channel: Tikvah-University
Back to Bottom
በአዲስ አበባ ለሚገኙ መምህራን እና የትምህርት ቤት አመራሮች የሙያ ብቃት የጽሁፍ ምዘና ተሰጠ፡፡

የሙያ ብቃት የጽሁፍ ምዘናው በከተማ አስተዳደሩ ከሚገኙ የመንግሥት እና የግል ትምህርት ቤቶች ለተውጣጡ 18,591 መምህራን እና የትምህርት ቤት አመራሮች በ15 የመፈተኛ ጣቢያዎች መሰጠቱን የከተማ አስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ ገልጿል፡፡

ምዘናው በአማርኛ፣ አፋን ኦሮሞ እና እንግሊዘኛ ቋንቋዎች በ36 የትምህርት አይነቶች የተሰጠ ሲሆን፤ በምዘና ሒደቱ ከአንድ ሺህ በላይ ፈታኞች፣ ሱፐርቫይዘሮች እና አስተባባሪዎች መሳተፋቸው ተገልጿል፡፡

የመምህራኑን ፍቃደኝነት መሰረት በማድረግ የተሰጠው የጽሁፍ ምዘናው፤ የመምህራንን የሙያ ብቃት በማሳደግ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ነው ተብሏል፡፡

የጽሁፍ ምዘናው ከ80 በመቶ የሚያዝና ቀሪው 20 በመቶ ደግሞ የማህደረ ተግባር ምዘናን መሰረት እንደሚያደርግ ምዘናውን በጋራ የሰጡት የከተማ አስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ እና የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ገልፀዋል፡፡

@tikvahuniversity
23 ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች በዩናይትድ ስቴትስ እየተካሔደ በሚገኘው ዓለም አቀፍ የሮቦፌስት ውድድር ላይ እየተሳተፉ ነው፡፡

አብርሆት ቤተ-መፃሕፍት ከአቦጊዳ የሮቦቲክስ ቴክኖሎጂ ማዕከል ጋር በመተባበር እና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ድጋፍ በውድድሩ እየተሳተፉ መሆኑ ተሰምቷል፡፡

በዩናይትድ ስቴትስ ሚችጋን ላውረንስ ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እየተካሔደ በሚገኘው ውድድር 23 ታዳጊዎች ኢትዮጵያን ወክለው በተለያዩ ዘርፎች እየተሳተፉ እንደሆነ ታውቋል።

ግንቦት 5/2016 ዓ.ም እንደሚጠናቀቅ በሚጠበቀው ዓለም አቀፍ የሮቦቲክስ ውድድር፤ ኢትዮጵያውያኑ ታዳጊዎቹ የሚያሸንፉ ከሆነ በሚችጋን ላውረንስ ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን ለመቀጠል የሚያስችላቸውን ነፃ የትምህርት ዕድል እንደሚያገኙ ተገልጿል።

@tikvahuniversity
ክላውድ ብሪጅ ማሰልጠኛ ተቋም

የተለያዩ አጫጭር ኮርሶችን በግራፊክስ ዲዛይን፣ በኢንቴሪየር ዲዛይን፣ በዌብሳይት ዴቨሎፕመንት እንዲሁም በዲጂታል ማርኬቲንግ አዘጋጅተን ምዝገባ ጀምሯል፡፡

🔔 ምዝገባ ላይ ነን!

ፈጥነው ለሚመዘገቡ ተማሪዎች ልዩ ቅናሽ አዘጋጅተናል፡፡ የቅናሹ ተጠቃሚ ይሁኑ!!

አድራሻ፦ መገናኛ ሲቲ ሞል 6ኛ ፎቅ

☎️ ለበለጠ መረጃ፦ 0942280000

Website: https://cloudbridgeacademy.com/
Instagram: https://www.instagram.com/cloudbridgetraining/
Telegram: https://hottg.com/cbmtraininginstitute
TikTok: https://www.tiktok.com/@cloudbridge_traning

#DigitalMarketing #TrainingInstitute #CloudBridge
በአምስት የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ እጅግ ዘመናዊ የሆነ የመልቲ ሚዲያ ስቱዲዮ ግንባታ ተከናውኗል፡፡

መልቲ ሚዲያ ስቱዲዮ

ስቱዲዮቹ በትምህርት ሚኒስቴር፣ ማስተርካርድ ፋውንዴሽን፣ አሪዞና ስቴት ዩኒቨርሲቲ እና ሻያሾኔ ኩባንያ ትብብር በተተገበረ e-SHE የተባለ ፕሮግራም አማካኝነት የተገነቡ ናቸው።

ስቱዲዮቹ በ'ሪሶርስ ማዕከልነት' የሚያገለግሉ ሲሆን የዲጂታል ትምህርትን ለማጠናከር ትልቅ ፋይዳ ይኖራቸዋል።

ስቱዲዮቹ በየትኞቹ ዩኒቨርሲቲዎች ይገኛሉ?

ስቱዲዮቹ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ ጅማ ዩኒቨርሲቲ፣ ባህርዳር ዩኒቨርሲቲ፣ ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ እና ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ መቋቋማቸው ተገልጿል።

እነዚህ ስቱዲዮች የከፍተኛ ትምህርት ሽግግርን በአምስቱ ዩኒቨርሲቲዎች እንዲሁም በቅርብ ርቀት በሚገኙ አስር ክላስተር ዩኒቨርሲቲዎች ለማምጣት እንደሚያስችሉ ይጠበቃል።

የስቱዲዮቹ ሌሎች ጠቀሜታዎች

መምህራን ስቱዲዮቹን በመጠቀም ለe-learning የሚጠቀሟቸውን ኮርሶች ማዘጋጀት ይችላሉ። እነዚህ ዩኒቨርሲቲዎች የተዘጋጁትን ኮርሶች ለመደበኛ እና የርቀት ትምህርት ፕሮግራሞች መጠቀም ይችላሉ።

ስለ e-SHE ፕሮግራም

e-SHE 'ኢ-ለርኒግ ከፍተኛ ትምህርትን ለማጎልበት' የአምስት ዓመት ፕሮጀክት ሲሆን በኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የዲጂታል ትምህርትን ተቋማዊ ለማድረግና ለማጎልበት ግብ ያደረገ ነው።

በፕሮጀክቱ የአምስት ዓመት ቆይታ 35 ሺህ መምህራን እና 800 ሺህ ተማሪዎች የዲጂታል ትምህርት አቅም ግንባታ ስልጠናዎችን እንደሚወስዱ ይጠበቃል።

@tikvahuniversity
#Update

2016 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና መርሐግብር ይፋ ሆኗል፡፡

መርሐግብሩ ከትግራይ ክልል ውጪ በሁሉም ክልሎች እና በሁለቱም የከተማ አስተዳደሮች በወረቀት እና በበይነ መረብ ፈተናውን ለሚወስዱ ተፈታኞች እንደሚያገለግል የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።

2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ከሐምሌ 3-5/2016 ዓ.ም ለማኅበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች፤ ከሐምሌ 9-11/2016 ዓ.ም ለተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ይሰጣል።

(መርሐግብሩ ከላይ ተያይዟል።)

@tikvahuniversity
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray #Exam

የትግራይ ክልል በቀድሞ ስርዓተ ትምህርት የተማሩና በ2013 እና በ2014 የትምህርት ዘመን መፈተን የነበረባቸው ተፈታኞ በ2016 ትምህርት ዘመን በወረቀትና በበይነ መረብ የሚፈተኑበት መርሃ ግብር ከላይ ተያይዟል።

@tikvahethiopia
ጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ የአክሰስ ሚኒ-ስኮላርሺፕ ፕሮግራም ተማሪዎችን አስመርቋል።

ተማሪዎቹ በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ እና በጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ ትብብር ላለፉት ሁለት ዓመታት የተሰጠውን ትምህርት ተከታትለው አጠናቀዋል።

50 የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች የእንግሊዝኛ ቋንቋ ስልጠናቸውን አጠናቀው ሰርተፊኬት እነደተበረከተላቸው ተገልጿል።

@tikvahuniveristy
#TopTrainingInstitute

በሁለቱም ቅርንጫፎቻችን (ሜክሲኮ እና መገናኛ) እንዲሁም በኦንላይን በምንሰጣቸው ስልጠናዎች ላይ ታላቅ የዋጋ ቅናሽ አድርገናል!

🔔 አሁኑኑ ይመዝገቡ!

🌟 ከትምህርትና ስልጠና ጥራትና ቁጥጥር
ባለስልጣን ሙሉ ዕውቅና ያለው!

የብዙ ዓመት ልምድ እና ብቃት ባላቸው አሰልጣኞች!

🎯 Graphics Design
🎯 Interior Design
🎯 Digital Marketing
🎯 Adobe photoshop
🎯 Website Design
🎯 Programming Language
🎯 Video Editing
🎯 Database
🎯 Basic Computer
🎯 Accounting Softwares
(Peachtree/ Queeck books)
🎯 Engineering Softwares (Autocad, Etabs, Civil 3d, Reviet, solid work, software engineering courses ...)
🎯 SPSS & STATA
🎯 MS-Project
🎯  Foreign & Local Languages

☎️ 0991929303 / 0991929304
#TVTI

የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት የስቴም ስልጠና ማዕከል አስመርቋል።

STEMpower በኢትዮጵያ 61ኛ የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ኢንጂነሪንግ እና ሒሳብ የስልጠና ማዕከሉን በፌዴራል የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ውስጥ አስመርቋል።

STEMpower በኢትዮጵያ በሁሉም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ማዕከላት ያሉት ሲሆን፤ በቴክኒክና ሙያ ተቋም የመጀመሪያ የሆነውን ማዕከል ሥራ ማስጀመሩ ተገልጿል።

ድርጅቱ በኢንስቲትዩቱ ውስጥ ባስመረቀው ማዕከል እስከ ሁለት ዓመት ስልጠናዎችን እየሰጠ አንዳንድ ወጪዎችንም ድጋፍ እያደረገ የሚቆይ መሆኑ ተጠቁሟል።

@tikvahuniversity
#MoE

ትምህርት ሚኒስቴር በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ለሚወስዱ ተማሪዎች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት ለመስጠት የሚያስችል ሀገር አቀፍ ንቅናቄ ይፋ አድርጓል።

በንቅናቄው ተፈታኝ ተማሪዎችን ለፈተና ለማዘጋጀት ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት መርሐግብር በትምህርት ቤቶች ይሰጣል።

በማጠናከሪያ ትምህርቱ የተማሪዎችን የመማር ብቃትና የሥነ-ልቦና ዝግጅት ለማሳደግ እንደሚሠራ የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ አየለች እሸቴ ገልፀዋል።

ይህን ሥራ አንዳንድ ክልሎች ቀደም ብለው መጀመራቸው የሚያበረታታ ተግባር መሆኑን ጠቅሰዋል።

ንቅናቄው ውጤታማ እንዲሆን የክልል ትምህርት ቢሮዎች ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ በጎ ፈቃደኞች፣ የተቋማት ባለሙያዎች፣ ወዘተ በማሳተፉ እንዲሠሩ ጥሪ አድርገዋል።

@tikvahuniversity
Tikvah-University
23 ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች በዩናይትድ ስቴትስ እየተካሔደ በሚገኘው ዓለም አቀፍ የሮቦፌስት ውድድር ላይ እየተሳተፉ ነው፡፡ አብርሆት ቤተ-መፃሕፍት ከአቦጊዳ የሮቦቲክስ ቴክኖሎጂ ማዕከል ጋር በመተባበር እና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ድጋፍ በውድድሩ እየተሳተፉ መሆኑ ተሰምቷል፡፡ በዩናይትድ ስቴትስ ሚችጋን ላውረንስ ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እየተካሔደ በሚገኘው ውድድር 23 ታዳጊዎች ኢትዮጵያን ወክለው…
በዩናይትድ ስቴትስ በተካሔደ ዓለም አቀፍ የሮቦፌስት ውድድር ታዳጊዎቹ ኢትዮጵያውያን የሮቦቲክስ ተወዳዳሪዎች አሸናፊ ሆነዋል።

በውድድሩ 23 ታዳጊ ኢትዮጵያውያን በተለያዮ ዘርፎች የተሳተፉ ሲሆን ከ10 ዓመት በታች በሮቦፓሬድ ምድብ የተወዳደረው ታዳጊ ማሸነፉ ተሠምቷል።

ሌላኛው ታዳጊ ተወዳዳሪ ከ 14-16 ዓመት ምድብ ተሳትፎ ስፔሻል አዋርድ ሽልማትን ማግኘት ችሏል።

በየውድድሩ ከ 1-3 ለወጡ ተወዳዳሪዎች የሜዳሊያ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

@tikvahuniversity
"የ2016 ዓ.ም የሪሚዲያል ተማሪዎች ፈተና መቼ ይሰጣል" የሚሉ በርካታ ጥያቄዎች ደርሰውናል፡፡

የሪሚዲያል ፈተና በሰኔ ወር መጀመሪያ በመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ብቻ እንደሚሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር ከዚህ ቀደም መግለፁ ይታወሳል፡፡

ቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ባደረገው ማጣራት የሪሚዲያል ፈተና ከሰኔ 1-7/2016 ዓ.ም ወይም ከሰኔ 8-14/2016 ዓ.ም ይሰጣል፡፡

ዘንድሮ ከ78 ሺህ በላይ ተማሪዎች በመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የሪሚዲያል ትምህርታቸውን ከታህሳስ ወር ጀምሮ እየወሰዱ ይገኛሉ፡፡

ይሁን እንጂ ባህርዳር ዩኒቨርሲቲ የተመደቡ የሪሚዲያል ተማሪዎች እስካሁን ጥሪ አልተደረገላቸውም፡፡ ተማሪዎቹ ወደሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ተዘዋውረው የሚማሩበት ዕድል እንዲሁም አማራጭ የፈተና ጊዜ የሚዘጋጅላቸው ስለመሆኑ በባህርዳር ዩኒቨርሲቲም ሆነ በትምህርት ሚኒስቴር የተባለ ነገር የለም፡፡

@tikvahuniversity
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ዓመታዊ የምርምር፣ የቴክኖሎጂ እና የሥራ አውደ-ርዕይ ተከፍቷል።

አውደ ርዕዩ ዛሬን ጨምሮ ለአምስት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ሲሆን በተለያዩ መምህራን እና ተማሪዎች የተሠሩ የምርምር ውጤቶች ይቀርባሉ ተብሏል።

አውደ ርዕዩ ተመራቂዎችን ወደፊት ከሚቀጥሯቸው ተቋማት ጋር የሚያገናኝ መድረክ እንደሚሆንም ተገልጿል።

ዩኒቨርሲቲው በቀጣይ አምስት ዓመታት ተግባራዊ በሚያደርገው ስትራቴጂክ ዕቅድ ለምርምርና ቴክኖሎጂ ልማት ከፍተኛ ትኩረት መሰጠቱን የተቋሙ ተ/ፕሬዝዳንት ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) ገልፀዋል።

@tikvahuniversity
HTML Embed Code:
2024/05/13 23:30:09
Back to Top