ሰበር አሳዛኝ ዜና ፦ በአዲስአበባ መሳለሚያ ሻንቅላ ወንዝ አካባቢ የሚገኘዉ ኑርጋ መስጂድ መንግሥት ለመንገድ ልማት ይፈለጋል በሚል የመንግሥት ፀጥታ አካላት በተገኙበት ህጋዊ ካርታ ያለዉ መስጂድ ፍፁም ኢ ፍትሐዊ በሆነ መልኩ መፍረሱ የአካባቢው ነዋሪዎች ገልፀዋል ፡፡ የአካባቢው ማህበረሰብ በህገወጡ ሱልጣን አማን ለሚመራዉ ለአዲስ አበባ መጅሊስ ሄደዉ ያመለከቱና ያሳወቁ ቢሆንም ሪያድ ጀማል የተባለ ግለሰብ ግን ምንም ማድረግ አንችልም ሲል እንደመለሰላቸዉም ከደረሰን መረጃ ለመረዳት ችለናል።
በሌላ ዜና የአዲስአበባ መጅሊስ የሚቃወም ሰልፍ በአል አንሲ መስጂድ ተካሄደ ስድስት ኪሎ አካባቢ በሚገኘዉ አል አንሲ መስጂድ በቅርቡ ከህዝቡ እዉቅና ዉጪ በአዲስ አበባዉ ሱልጣን አማንና መሀመድ አባተ አማካይነት ለመስጂዱ ናዚርና አስተዳደር በማድረግ የወሰኑት ህገወጥ ዉሳኔ በዛሬው ዕለት ከጁምአ ሰላት በሗላ የመስጅዱ ተጠቃሚዎ ማህበረሰብ ተቃዉሞዎቹን በዚህ መልኩ አሰምተዋል።
የአዲስ አበባው ጠንካራው መጅሊስ በዚህ 3ትወር ውስጥ ብቻ የህዝበ ሙስሊሙን መብትና ጥቅም አሳልፎ እንደሰጠ እንዲሁም የመብት ተሟጋቾችን በማስፈራራትና በማሳሰር የሰራው ግፍና በደል ለታሪክ ይቀመጥ፡፡ ይህን ሁሉ ሲፈፀም ዝም ያለው ኡስታዝና አክቲቪስት በመጅሊስ ሰበብ ሲጮህ የነበረው ፍላጎቱ ምን እንደሆነ በዚህ አጭር ጊዜ ህዝበ ሙስሊሙ መረዳቱን መረጃ ሰጭችን ትዝብቱን በሚያሳዝን መልኩ ገልፆልናል።
በእነ ሙፍቲ ወቅት ቢሆን ኑሮ እንኳን መስጅድ ፈርሶ በሚናገሩት ንግግር እንኳ ቃላት እየተሰነጠቀ ምን ይባሉ እንደነበር አሏህ ይወቀው!!
SHARE SHARE SHARE ያድርጉ
LIKE LIKE LIKE LIKE በማድረግ የእርስወን ድርሻ ለሌሎች በማዳረስ ይወጡ
በቴሌግራም ይከታተሉን
https://hottg.com/stop_wahababizm
#እኔ_ኡለሞቸን_ተቋሜን_መስጅዴን_የምጠብቀው_ጀግናው_የሙፍቲ_ትውልድ_ነኝ
>>Click here to continue<<