የትምህርት ሚኒስቴር ወደ መንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የሚገቡ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ ምርጫቸውን
እንዲያስተካክሉ የሰጠው የጊዜ ገደብ ዛሬ ተጠናቋል።
የዩኒቨርሲቲዎችን የቅበላ አቅም፣ የተማሪዎች አማካይ ውጤት አፈፃጻጸም፣ ወዘተ ከግንዛቤ በማስገባት ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ ምርጫቸውን እስከ መጋቢት 13/2014 ዓ.ም ድረስ በ Portal.neaea.gov.et ገብተው እንዲያስተካክሉ መጋቢት 08/2014 ዓ.ም ማሳወቁ አይዘነጋም።
ከምደባ በኋላ የሚቀርብ ምንም አይነት የምደባ ለውጥ የማያስተናግድ መሆኑን ሚኒስቴሩ መግለጹ ይታወሳል።
በዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ላይ በርካታ ቅሬታዎች በተለይ ከአማራ ክልል መነሳታቸው ይታወቃል።
ሚኒስቴሩ በቅሬታዎቹ ላይም ሆነ በዩኒቨርሲቲ ምርጫ ማስተካከያው ላይ ያለው አዲስ ነገር የለም።
@minesterofeducation
>>Click here to continue<<