TG Telegram Group Link
Channel: ቅንጭብጭብ
Back to Bottom
የታላቁ ሩጫ ቲሸርቶች አሉን

1 ፍሬ 1500
2 እና ከዛ በላይ1300

0945965456 ይደውሉ
Forwarded from Ibex Events & Hiking
ወደ ቡልጋ - የለኝ ገደል የምናደርገው ጉዞ 4 ቀናት ብቻ ቀሩት

እሁድ - ሕዳር 18

ክፍያው ምንን ያጠቃልላል?
የቁርስ፣ ምሳ፣ የታሸገ ውኃ፣ የመግቢያ ክፍያዎች፣ የአስጎብኚ፣ የፎቶግራፍ የሻይ ቡና መጠጥ... ክፍያዎችን በሙሉ

በዚህ ጉዞ ለመሳተፍ እርግጠኛ ሲሆኑ በ telegram @ibexet , @yoti27 "አለሁ" ይበሉ ወይም 0945965456 / 0928412796 ይደውሉልን።

ተጨማሪ ዝርዝር መረጃዎችን በውስጥ መስመር የምንልክ ይሆናል

በ Telegram hottg.com/ibexevents
በ facebook m./facebook.com/ibexevent ይቀላቀሉን።

መልካም ቀን!

ሰላም ለኢትዮጽያ! 💚💛
#Ethiopia #LandOfOrigins #hikinglovers #VisitAmhara #Bulga #Travel
#ቅንጭብጭብ_ኢትዮጵያ
.
.
#ከማስታዎሻየ_ማህደር!!
.
.
#ሌላ_ዓለም!!
(ክፍል አንድ)
.
.
.. ትናንት ህዳር 8/2015 ዓ.ም "አርባተንሳ" ክብረ በዓልን ልታደም ወደ ገጠራማው መንደር ካ'ንድ ወዳጄ በቀረበልኝ ጥሪ መሰረት ወርጀ ነበር። ወዳጀ ካለኝ ቦታ ደርሸ ካገኘሁት በኋላ ያው እንደተለመደው 'ቅርብ ነው ደርሰናል!' እያለ ሰፈር ለሰፈር ትንሽ ተጉዘን ከቤታቸው ደረስን የቤቱ ግቢ በላም በጥጃዎችና በእርሻ የተከበበ ነው። ግቢው በር ላይ የተቀመጡ ሰዎችን ሰላምታ ሰተን ወደ ቤቱ ዘለቅን.. የቤቱ አባወራ ከሳሎኑ ጥግ ይዘው ተቀምጠዋል..ቅድሚያ እርሳቸዉን ሰላምታ ሰተን በቤቱ ያሉ እንግዶችንም ጨበጥናቸው እና የበግ ቆዳ ከተጎዘጎዘበት መደብ ቁጭ አልን። ወዳጄ ቀልጠፍ አለና ወደ ኩሽናው ዘልቆ እህቱን ምግብ እንድታመጣ አዘዛትና "ክቡር ዘበኛ" እሚባለዉን ብርጭቆና በጆክ ጠላ ይዞ መቶ ከፊቴ ቆመ.. እኔም ከቤቴ እንደበላሁና ያው ጠላም እንደማልጠጣ በመናገር አስቤ የመጣሁት "ወተት ለመጠጣት!" እንደሆነ አስታወስኩት!😋 ቢሆንም 'ካልበላህ ወተት የለም!'😑 እሚል እይታ አሳይቶኝ ለራሱ ጠላዉን ቀድቶ ቁጭ አለ። በልቤም አንድ ቁርጥ አንስቼ እበላና ወተቴን እጠጣለሁ ብየ መጠበቅ ያዝኩ ታዲያ የወዳጄ እህት በሰሃን(ባቲ) የሰማይ ስባሪ እሚያክል እንጀራ በድንች በስጋ ወጥ ይዛ መታ አስረከበችኝ!! 'ኧረ በዝቷል ይተርፋል!' ብልም ሰሚ ስላላገኘሁ ወደ ወዳጄ አባት ፊቴን መልሸ 'አባት ይባርኩልኝ?' አላኳቸው(አክባሪ ለመባል) ምን ዋጋ አለው! 'ለወንድ አይባረክም! ዝም ብለህ ብላ!' ብለው ጨነገፉኝ።😬 ኩርኩሜን ተቀብየ ከወዳጀ ጋር የቀረበልኝን ምግብ መብላት ጀመርኩ.. ወዳጄ ምግቡን አቋርጦ ወደ ኩሽናው ተወነጨፈና በግራም ሰሃን እርጎ ይዞ መጣና እንጀራዉን መሸከም ያቃታት ሰሃን(ባቲ) ላይ እርጎዉን አጥለቀለቀው..😇 በላየላይ የወረደዉን መና እያጣጣምኩ በላሁ..😋 ታዲያ በየ መሃሉ አባወራው በመገረም ለምን ጠላ እንደማልጠጣ እየደጋገሙ ይጠይቁኛል! እኔም የተለያዩ መልሶችን እነግራቸዋለሁ.. ወዳጄና እህቱም እንጀራና ወጥ እያመጡ ጨምር እያሉ ከድንች በስጋው ወጥም ከእርጎና ከንጀራዉም ይከምሩብኛል..🙄'ኧረ በቃኝ!' ብልም የቤቱ አባዎራ ጨምሮ እንግዳቹ ሁሉ 'ትንሽ ብላ እንጅ!' እያሉ አጨናነቁኝ እኔ ግን ተሎ መሃላ ዉስጥ ገብቼ ድርቅ በማለት እጄን ታጠብኩና ቁጭ አልኩ..መቼም የገጠር ሰዎች እማይበላ እማይጠጣ አይወዱም።
.
.
ይቀጥላል..


✍️Aman😑 YTZ
@amanYTZ23

join and share
@YelbeDrset
@YelbeDrset

inbox me @amanYTZ23
✍️✍️✍️✍️✍️✍️
እወዳታለሁ ገራሚ ናት ደስስስ ትለኛለች።
ብዙ ግሩም ጊዜ አሳልፈናል አብረን ስንሆን ሰአቱ ይበርብኛል አብረን ውለን ከመቼው መሸ ትለኛለች ቶሎ ቶሎ ትናፍቀኛለች።

ቀልድ ይገባታል ኮስተር ብዬ ስኮምክ ታሽካካልኛለች፣ ነፍሳችን ይናበባል ፣ ሳናወራ እንግባባለን ።

ከስምንት ወር በፊት <<አግባኝ>> አለችኝ አልተዘጋጀሁም አልኳት፣ ጊዜ ስጪኝ ፣ ትንሽ ታገሺኝ አልኳት
<<አልችልም >>አለችኝ።

የመንደሩ ሰዎች ሽሙጥ ፤ የቤተሰቦቿ ጭቅጭቅ እና እድሜዋ አስጨነቃት ።

እኔ ደግሞ ባልተዘጋጀሁም አቋም ፀናው።

ከህይወቴ መስመር መሰስ እያለች ሄደች። እየደበረኝ ቅር እያለኝ በአቆሜ ፀናው።

አልፎ አልፎ ከአንገት በላይ ሃይ እንባባላለን።

ባለፈው ሳምንት እንገናኝ አለችኝ። ተገናኘን ፤ አይኗ ውስጥ ጉጉት፣ ተስፋ እና ደስታ ምንም አላየሁም። <<በነገራችን ላይ ቅዳሜ ሰርጌ ነው ከቻልክ ልጠራህ ነው የመጣሁት>> አለችኝ።

ትኩር ብዬ አየኋት ቅናቴን ለመደበቅ የደረቀ ፈገግታ ፈገግኩ (ደስስስ የማይል ስሜት ወረረኝ) ያሳዝናል አመለጥሺኝ አልኳት።

<<ብሽቅ ስለሆንክ ተፈላሰፍክ መጠበቅ ፈልጌ አልቻልኩም>>አለችኝ እኔን የምትወደኝን ያህል የምታገባውን ልጅ እንደማትወደው ገብቶኛል።

ያዘዘችውን ቢራ ተጎነጨች እና መጨዋወታችንን ቀጠልን።

<<በእድሜህ ማሳካት የምትፈልገው ነገርን ዛሬ ካልጀመርከው መሽቶ በነጋ ቁጥር ጭንቀትህ ይበረታል ።

ትልቅ ለመምሰል እንዳልጣርን ፤ አንድ ፍሬ ለመባል እንባክናለን።

መንደርተኞች ሳይታወቃቸው ጫና ውስጥ ይከቱሃል ። ባገኙህ ቁጥር ጨዋታ ለመፍጠር ይሆን አሳስቧቸው ይሆን ብቻ ምንጩ ባልታወቀ ምክንያት እንደቀልድ ምንድን ነው መፍዘዝ አግቢ እና ሰርግ አብይን እንጂ ይሉኛል ።

ቤተሰቦቼ ተጠርተው ስለበሉት ሰርግ ከሰርግ ሲመለሱ ይተነትናሉ ይገባኛል መልእክት እያስተላለፉ ነው

ተረድቼሃለሁ ችስታ ነህ ብታገባ ድህነት ፓራላይዝ የሚያደርግህ ይመስልሃል በልጅነት እየራበህ እንዳደክ የነገርከኝን አልረሳሁም ።

አሁን ካገባሁ የትላንት ህይወቴን እደግመዋለሁ ብለህ ትሰጋለህ።

ሁኔታህ እና የኔ ፍላጎት አራምባ እና ቆቦ ሆነ ። እንደሁኔታ በቅርቡ በቀላሉ ትዳር የሚባል ስብጥር ውስጥ እንደማትገባ እርግጠኛ ነኝ

ጌታ ይሁንህ ፤ እህቴ እንዴት ቆማ እንደቀረች አውቃለሁ .. . .. . ዘግይቶ ማግባት ለወንድም ምቾት እንደማይሰጥ ከልጅህ ጋ እየተንከባለልክ መጫወት ሲሳንህ ይገባሃል።

ብልጥ ነኝ ባዮች ቆመው የሚቀሩት እየተመራመሩ ነው ፤ ህይወት በስሌት እና በምርምር ብቻ የሚሳካ እየመሰላቹ ነው>>

ዝም አልኳት ንግግሬ ከዝምታዬ ካነሰ ለምን እናገራለሁ ። ያወራችው የቱ ነው ስህተት ?!

ከነፍ ዝምታ በኃላ አይኖን ትክ ብዬ እያየሁ ትዳርሽ የተባረከ ይሁን አልኳት ።

ፈጥኖ ከመሳሳት ዘግይቷ ትክክል መሆን በእጅጉ ይሻላል ደሞ ያልተሳካ ትዳር ቆሜ ቀረው የሚል ጥድፍያ ውጤት ነው ብዬ ተፅናናው።

© Adhanom Mitiku
@kinchebchabi @kinchebchabi
#ቅንጭብጭብ_ኢትዮጵያ

#ከማስታዎሻየ_ማህደር!!
.
.
.
#ህይወት_የመኖር_እዳ!!
.
.
.. ከተወለድኩ ጀምሮ እድሜዬ በጨመረ ቁጥር ወደ ህይወት እየመጣሁ ይሆን ወይስ ወደ ሞት እየሄድኩ እንደሆን አላዉቅም! ስለ ህይወት እያወኩ ለመኖር እየጀመርኩ ግን ወደ ሞት እየሄድኩ ይመስለኛል! መኖር ታዲያ እንዴት ስጦታ ሊሆን ይችላል?? ሐይማኖተኛ ሰዎች አንደበት ላይ እማይጠፋ ቃል "በህይወት ስላለህ ብቻ አመስግን!!" እሚለው ነው!! ግን ለኔ አይታየኝም! መፈጠሬን እንደስጦታ አይቼ ለማመስገን ህይወት በቃኝ እስክል መኖር አለብኝ! ካልሆናማ እንዲሁ ወደ ህይወት እየመጣሁ ወደ ሞት ከሄድኩ ስጦታነቱ ቀርቶ ኑሮ እዳ ይሆንብኛል!! ሳልሞት በፊት ተሽቀዳድሜ መኖር ያለብኝ እዳ ሁኖ ይሰማኛል። ሰው ሳይኖርም ይሞታል!
   ህይወት ከፈጣሪ እምትሰጠን ብድር ትመስለኛለች ብድራችን ለመክፈል ስንፈጋ ስንታገል የተሰጠን የክፍያ የቀን ገደብ አልቆ እኛም በነፃነት ሳንኖር እምንነጠቃት ናት። የሰው ልጅ ሁሉ "የህይወት ግብ ደስተኛ መሆን ነው!" በምትለው ህግ ይተዳደራል! ይሄን ህግ ሐይማኖተኞች ቢያጥላሉትም በነሱ ልብ እንደማያምኑበት ቢናገሩም እነሱም በሆነ የህይወት ዘመናቸው ይከተሉታል። ሁሉም ሰው በራሱ ዛቢያ ኑሮን ለማሸነፍ ይሽከረከራል፤ ኑሮን ማሸነፍ ያው ሀፍታም መሆን ነው! ብሎ አዕምሮው ላይ በሰቀለው ሃሳብ ይነዳል። መፈጠሩን እንደ እዳ ለማየት ወይንም እንደ ስጦታ ለመቀበል በቀላሉ በአኗኗር ዘይቤው ይወስናል፤ ብዙዉን ጊዜ ሀፍትን ካካበተ ስጦተነቱን በተቃራኒው በድህነት ከተሰቃየ ደግሞ እዳነቱን ይቀበላል፤ እዚህ ላይ አንዳንድ ነገረኛ አንባቢ "ታዲያ አንተ በድህነት ተሰቃይተህ ነው! ህይወት የመኖር እዳ ናት የምትል" ይል ይሆናል! ግን ህይወት እንዳለህ ሀብት ወይም እዉቀት የምትወሰን ናት በሚለው አልስማማም!! ምክኒያቱም ህይወት አወቅንም አላወቅን ሀፍታም ሆን ወይ ፀደቅን እስክንሞት ድረስ እዳ ናት!! አዋቂው ህይወትን ተረዳኋት ባላት መጠን ሲያብራራና ሲያወጣ ሲያወርዳት ትንሽ በተጠጋት ቁጥር እማያዉቀው እልፍ መሆኑን እየተረዳ አለማወቁን አዉቆ እንኳ እረፍት ሳያገኝ የእዉቀት ጥሙን ሳያረካ ያርፋል!! አላዋቂዉም መኖር ባለማወቅ የሰጠችዉን ሰላም ተቀብሎ መኖሩ ሳይታወቅ በሚራመድበት መሬት የሆነ መስመር የእግሩ አሻራ ሳይታይ ይሞታል!! ሀፍታሙ ሃፍቱን የደከመበትን ያህል ሳያጣጥመው ወይ ደግሞ በሀፍቱ ልክ ደስተኛነቱ የወረደ ሲሆንበት! ወይ ሀፍቱ እረፍት እንደነሳው ሌላ አስደሳች ግብ ወይ ምላሽ ሲፈልግ ያልፋል!! ፃዲቁ ደግሞ የፈጣሪው ፍርድ እያስፈራው በአካባቢው ያሉ ሰዎች ኑሯቸዉን በሐጢያታቸው እየለካ የመኖር ጣእሙን እርግፍ አድርጎ ትቶ ሞቱ እንዲቀርብለት እየፀለየ ይኖራል!? መፈጠሩ ስጦታ ነው ብሎ ግን መኖሩን ከመሞት በላይ አይወደዉም! ስጦታ ብሎ የተቀበለዉን ህይወት በሞት መነጠቅን ይናፍቃል እንደናፈቀዉም አይቀርምና ያገኘዉና ይቀበላል!!
   በነዚህ ሁሉ መሃል እኛ "ሁሉን ቀመስ!" እምንባል አይነት ሰዎች አለን!! የማህል ዳኛ ማለት ነን፤ ሌሎች በተለያየ አቅጣጫ የመኖራችን ግብ ብለው ያመኑበትን ሲያስቆጥሩ እምናጨበጭብ አንዳንዶች ደግሞ ሲደናቀፉም (ፋዎል) ሲሰሩ እምንታዘብ!! አለን። ለኛ ህይወት ጥያቄ እንጅ መልስ ሁና እማታዉቅ!! ህይወት የመኖር እዳ እንጂ ስጦታ ሁና እማትታየን!! ብዙ የገባን ይመስለናል ግን አንዳች ነገር አንፈታም! እምናምን ግን ደግሞ እማናምን! ወደ ህይወት እንመጣል ግን ደግሞ እማንደርስ! ወደ ሞት እምንሄድ!! እዉቁ ፈላስፋ.. "ያልተመረመረ ህይወት ለመኖር ያልተገባ ነው!" እንዳለው የኛ እዳ ጥያቄ የሆነ ነን። የናንተስ የመኖር እዳ ምንድን ነው?? እዳ ካልሆነ ስጦታነቱን በምን አመናቹህ? ስጦታነቱ ምኑ ላይ ነው? ተሰቶ እሚነጠቅ ስጦታ መሆኑንስ እንዴት ታዩታላቹህ? ወደ ህይወት እየመጣቹህ ነው ወይስ ወደ ሞት እየሄዳቹህ??
.
.
.
ህዳር 28/2015 ዓ.ም

✍️Aman😑 YTZ
@amanYTZ23

join 👇👇👇
@YelbeDrset
@YelbeDrset

inbox me @amanYTZ23


@kinchebchabi @kinchebchabi
Live stream started
#ቅንጭብጭብ_ኢትዮጵያ ተመልሷል። 🙏
ከ 1962 ጀምሮ እንቅልፍ ያልተኛው ሰው...
@kinchebchabi
ቅንጭብጭብ
ከ 1962 ጀምሮ እንቅልፍ ያልተኛው ሰው... @kinchebchabi
ከፈረንጆቹ 1962 ጀምሮ እንቅልፍ ያልተኛው ሰውዬ በቬትናም ትንሽዬ ከተማ ውስጥ:
በሰላም
በጤና
ከሰዎችም ሳይጣላ
ኡ ኡ ኡ ኡ እያለ ሳይጮህ
ሳያብድ
ሳይደባደብ
ስቅስቅ ብሎ ሳያለቅስ
ያዙኝ ልቀቁኝ እያለ ሳያስቸግር
ሳያቅለሸልሸው
ሳያጥወለውለው
ነገር አለሙ ሳይጠፋበት
ኧረ ወየው እያለ ሳይጮህ

ጭራሽ ትዳር ኖሮት ልጆች ወልዶ ፤ ከአንድም ሦስት ቤት በእጁ ገንብቶ ፤ በቀን ሁለት ስራ እየሰራ አለ ይኖራል።

እንዴት እንደሆነ እንጃ የሆነ ቀን ለታ ነቃ ነቃ ነቃ! በቃ እንቅልፉ ብን ብሎ ጠፋ!

ጥቂት እየተመገበ፤ ሲጃራውን እየጠጣ፤ ቤቱ የሚጠምቀውን የሩዝ አረቄ እየጠጣ ... አለ በሰላም በጤና

መቼ እንደተኛህ ትዝ ይልሃል ሲሉት: ድሮ ነው ሩቅ ጊዜ እያለ
ሚስቱን: ሲተኛ አይተሽው ታውቂያለሽ ስትባል Never እያለች
ልጁን: አንተስ ትተኛለህ ሲሉት "በሚገባ" እያለ

በዙሪያው ያሉ መንደርተኞች በሙሉ መሸ ደና ደሩ ሲሉ እሱግን ይኸው ለ 62 አመታት ቁልጭ እንዳለ አለ🧐

እናንተስ እንቅልፍ ሳትተኙ ኑሩ ብትባሉ የሚሆን ይመሥላችኋልን?

እንቅልፍ ህይወት ነው

🎶 ኦሆኦኦ መለስ አርገው ጋሜ
አይዞህ ወንድሜ🎶 ማለት ይሄኔ ነው 🧐

ሰውየው ግን የሚፈልገው ነገር ... መተኛት ነው አለ።
እውነቱን ነው .... በዚች አለም ላይ ከእንቅልፍ በላይ ምን የሚያስደስት ነገር አለ?

ብቻ: በእውነት! ታሪኩ ውስብስብ ነው።

join us
@kinchebchabi
ይግረማችሁ - የምትተኙበት ፍራሽ ምን ይመስላል?

ይመቻል? ይቆረቁራል? ወገቤን አንገቴን አስብሏችኋል? በሉ ስለዚህ ፍራሽ አንብቡ...
ቅንጭብጭብ
ይግረማችሁ - የምትተኙበት ፍራሽ ምን ይመስላል? ይመቻል? ይቆረቁራል? ወገቤን አንገቴን አስብሏችኋል? በሉ ስለዚህ ፍራሽ አንብቡ...
የምናወራው ስለ ፍራሽ ነው ለማለት ያስቸግራል ።

DeRUCCI Smart ' T 11 - Pro  ይባላል  ።  ይህ በ 8,250. ዶላር ለገበያ የቀረበው ስማርት ፍራሽ ከተገጠሙለት የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ   ቴክኖሎጂዎች መሀል . ...

በዚህ ፍራሽ ላይ የተኛ ሰው እንቅልፍ እንደተኛና እንዳልተኛ ፡ ፍራሹ በደንብ ያውቃል ። እና እንቅልፍ ካልወሰደው ፡ የመኝታ ቤቱን ብርሀን ቀስ እያለ ይቀንስና ለተኛው ሰው ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር ቅርፁን ለዋውጦ ይበልጥ ምቹ ሆኖ እንቅልፍን ለመጋበዝ ይሞክራል ።

ሰውየው በእንቅልፍ ሰአት ሙዚቃዎችን የመስማት ልምድ እንዳለው ፡ ተደርጎ ፕሮግራም ከተደረገ ፡ ከስለስ ያለ በመሳሪያ የተቀነባበረ ሙዚቃ በትንሹ ይከፍትለታል ።
እና ቀስ እያለ ፡ ማሳጅ እንደማድረግ አይነት በመጠኑ እየተንቀሳቀሰ ሰውየውን ለማስተኛት ይሞክራል ።
ከዚህ ሁሉ በኋላ ሰውየው እንቅልፍ ከተኛ ፡ የተከፈተውን ለስላሳ ክላሲካል ሙዚቃ ይዘጋና  የመኝታ ቤቱን መብራት ያጠፋል ።
.......
የዚህ ፍራሽ ስራ  ይህ ብቻ አይደለም ፡ ሰውየው እንቅልፍ ከተኛ በኋላም ፡ የልብ ምቱን ፡ የደም ዝውውሩን ፡ የሰውነቱን ሙቀት እና አጠቃላይ የጤናውን  ሁኔታ እየተከታተለ ይመዘግባል ።
.......
በዚህ አልጋ ላይ የተኛው ሰው ፡ ሰውነቱ ላይ ያልተለመደ አይነት ትኩሳት እንዳለው ፍራሹ  ካስተዋለ ፡ በተገጠመለት አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ አማካኝነት ፡ የትኩሳቱን ሁኔታ መዝግቦ .........
ማታ ስትተኛ ሙቀትህ ልክ አልነበረም ፡ ትኩሳት አለህ ፡  ሀኪም ቼክ ማድረግ ይኖርብሃል የሚል ቴክስት ጠዋት ወደሰውየው ስልክ ይልካል ።

......

ይህ የሚሆነው የሰውየው የጤና ሁኔታ  ለክፉ የማይሰጥ ከሆነ ነው ። ነገር ግን ሰውየው በተኛበት ወቅት የአተነፋፈስና የሰውነቱ ሙቀት ወይም የልብ ምቱ  ኖርማል ካልሆነና ሰውየው በድንገት ከታመመ ፡ ይህ ስማርት ፍራሽ ፡ ከሰውየው ስልክ ጋር ባለው የኢንተርኔት ግንኙነት አማካኝነት ፡ ወዲያውኑ ለድንገተኛ ህመም ተብሎ ወደተመዘገበው የህክምና ተቋም ወይም ሀኪም ጋር ስልክ ደውሎ ፡ Mr.. እንትና. .  በድንገተኛ ህመም ላይ ስለሆነ ቶሎ ድረሱለት ሲል ይደውላል ። ቴክስት ያደርጋል ።
....
ሰላም ከሆነና ሆኖም ሰውየው እያንኮራፋ ከሆነ ፡ በሚያንኮራፋው ሰው በኩል ብቻ ያለውን  የፍራሽ ክፍል ቅርፁን በመቀየር፡ ሰውየው  አስተኛኘቱን እንዲቀይርና ትራሱን በማስተካከል  አተነፋፈሱ ኖርማል እንዲሆን  ያደርጋል ።
.....
ለሊት ላይ የአየር ንብረቱ ተለውጦ ብርድ ከመጣ ፡ ይህ ፍራሽ ወደ AC ው መልእክት በመላክ ክፍሉ እንዲሞቅ ያደርጋል ። በተቃራኒው ሙቀት ከሆነም ክፍሉ እንዲቀዘቅዝ ያደርጋል ።

... ለሊቱ በዚህ መልኩ አልፎ ሲነጋ ፡ ሰውየው ከእንቅልፍ መንቃት ያለበት ሰአት ላይ ፡ እንደተለመዱት አላርሞች ድምፅ በመልቀቅ አይረብሽም ። ይህ ፍራሽ ጨዋ ነው ።
ከዛ ይልቅ ሰውየውን የሚቀሰቅሰው ፡ የክፍሉን ብርሀን በመጨመር እና በተወሰነ መልኩ ቀስ እያለ በመንቀሳቀስ እያባበለ ነው  ።
ይህን ከማድረጉ በፊት ግን ፡ ወደቡና ማፍያው ማሽን መልእክት በመላክ ፡ ቡና እንዲፈላ ያዛል ።
......
ማታ ሰውየው ጥሩ እንቅልፍ እንዳልተኛ ካስተዋለ ፡ ሲነጋ በሰውየው ስልክ ላይ ፡ ጥሩ እንቅልፍ ለመተኛት የሚያስችሉ ጠቃሚ ምክሮችን ይልካል ።
.............
ሆኖም  የሰላማዊ እንቅልፍ ጉዳይ  በምቹ ፍራሽ ላይ ከመተኛት ጋራ የተያያዘ  ባለመሆኑ እዚህ ላይ ተኝተውም  ጥሩ እንቅልፍ ማግኘት ሊቸግር ይችላልና , ይህን መሰል መኝታ ሳያስፈልገን ስለምንተኛው  ስለ ጥሩው እንቅልፋችን እናመስግን ። ቴክኖሎጂው ግን እዚህ ደርሷል ።
© ዋስይሁን

በአብሮነት እንቆይ
hottg.com/kinchebchabi
''.....ሰው ሲታመም የምንጠይቀው ከቋጠሮ ሰሐን ጋር ነው... ሰው ሲታሰር ' እግዚአብሔር ያውጣህ ' የምንለው ከፍትፍት አገልግል ጋር ነው ....አራስ የምትጠይቀው ከፔርሙዝ አጥሚት ጋር ነው ... የክርስትና አባታችን ለፋሲካ አክፋዩን የሚጠብቀው ድፎ ዳቦ ና አረቄ ነው ...እዝንተኛ የምናስተዛዝነው ሰባት እንጀራ ከአንድ ሰሐን ወጥ ጋር ነው ...ሟች የምንሸኘው ከገንቦ ጠላና ከለምለም እንጀራ ጋር ነው ...የቅዱሳንና የመልአክታት ተራዳኢነት የሚጎበኘን በስማቸው ከዘከርን ነው...ሰዕለታችን በሬ ወይም በግ ነው ...ሰርጋችን ፣ ልደታችን፣ እርቃችን፣ ሹመታችን፣ አምልኳችን፣ የሚበላ ነገርን ሙጥኝ ያሉ ናቸው ... ...ሌላው ቀርቶ አንድ ሰው ተምሮ ሲመረቅ ይዘን የምንሄደለት ስጦታ ብዕር ወይንም መጽሐፍ አይደለም ፤ ኬክ ፣ ብርቱካን ፣ ሙዝ ...ነው ። በሽተኛ ስትጠይቅ ከብርቱካንና ከሙዝ ይልቅ መጽሐፍ መውሰድ እንደማላገጥ ይቆጠራል ። ጊዜውን ይገፋበት ዘንድ መጽሐፍ ማበርከት በሽተኛው እንዳይድን ከመመኘት እኩል ነው ። ለኛ ለኢትዮጵያውያን መጻሕፍት ከባዶ ገበታችን በስተዚያ የተቀመጡ ትርፍ ነገሮች ናቸው ። መጻሕፍት የሚያስፈልጉት ገበታችን ሞልቶ ከገነፈለ በኃላ ነው ብለን በይነናል። ገበታችንም አይሞላ ፤ መጻሕፍቱም አይነሱም ። ያልተረዳነው ቢኖር ለገበታ መትረፍረፍ ዙሪያ ጥምጥም ጉዞ መጻሕፍት አቋራጭ መንገድ መሆናቸውን ነው ።እንዴት ታዲያ ማንበብ መብላትን ይቅደም ? መቼ ይሆን ከምንኮራባቸው ባህሎቻችን በላይ ማንበብ ባህላችን ሆኖ የምንታወቅበት ናየምንኮራበት?......'''''

አለማየሁ ገላጋይ

በአብሮነት እንቆይ
hottg.com/kinchebchabi
ሳንዲ ፒርስ...
ቅንጭብጭብ
ሳንዲ ፒርስ...
ህይወት ለሳንዲ ፒርስ ፡ ደስ ትላለች. .. ሳንዲ በችካጎ ከተማ ከሚገኝ አንድ ባንክ ውስጥ ትሰራለች. .እናም እንደተለመደው በከተማዋ ዳርቻ ወደሚገኘው ቤቷ በማምራት ላይ ሳለች. .. ኩርቲስ ጃክሰንን ከርቀት ተመለከተችው. ..
..................
በዚህ ጎዳና ላይ አዘውትሮ የሚመላለስ ሰው ፡ ኩርቲስ ጃክሰንን ያውቀዋል ።
ይህ ሰው ለአመታት በዚህ ጎዳና ላይ አዘውትሮ በሚቀመጥበት ቦታ ላይ ሆኖ ፡ የሰወችን ደግነት ይጠባበቃል ። ኑሮው በሰወች ልግስና ላይ የተመሰረተ ነው ። እናም ዛሬም እንደተለመደው " ቤት አልባ ነኝ እርዱኝ " የሚል ፅሁፍ ደረቱ ላይ አድርጎ መብራት ይዟቸው የቆሙ ሰወችን እየለመነ ነው ።
.............
ሳንዲ ፒርስ ይሄ ጥቁር አሜሪካዊ ያሳዝናታል ፡ እናም አቅሟ በፈቀደ መጠን ሁሌም ትረዳዋለች ፡ ጥቂት ደቂቃ ወስዳም ታወራዋለች ፡ ይህ ለአንድ የጎዳና ተዳዳሪ ሰው ትልቅ ነገር ነበር ። እናም ዛሬ ፡ መብራት የያዛቸውን ሰወች ለምኖ ፡ ወደዘወትር ቦታው ሲመለስ ፡ ያችን ደግ ሴት ቆማ ስትጠብቀው ተመለከተ. . ሃይ ሳንዲ እንዴት ነሽ ፡ ልጅሽ ደህና ነው አላት ፡ የአስር አመት ልጅ እንዳላት ነግራዋለች እናም ሁሌ እሷን ሲያገኝ ይህንን ይጠይቃታል ።
.........
ሳንዲ ፒርስ ሁሉም ሰላም እንደሆነ ነግራው ፡ ህይወት አንድ ቀን መልካም ይሆናልና ተስፋ እንዳይቆርጥ አፅናንታው ፡ ጥቂት ብሮች ሰጥታው ሄደች ።
............
ኩርቲስ ጃክሰን በዚህች ሴት ደግነት ሁሌ ይገረማል ፡ ለሱ ይህች ሴት ዝም ብሎ ሳንቲም ሰጥተውት እንደሚያልፉት አይነት አይደለችም ፡ ፈጣሪ እንድታፅናናው የላከለት እህቱ ትመስለዋለች. . እናም በሳምንት የተወሰነ ጊዜ መጥታ ሰላም ብላው ስትሄድ በህይወት ላይ ተስፋ ያደርጋል ።
................
ሰሞኑን ግን ይህች መልካም ሴት ወደሱ መጥታ አታውቅም ፡ ቢያንስ በሳምንት አንዴ እንኳን ትመጣ የነበረችው ሳንዲ ፒርስ በዛ ጎዳና ማለፍ ከተወች ፡ አንድ ወር ሆናት. ..,በዚህ ጊዜ ኩርቲስ ጃክሰን አንድ ነገር አሰበና ፡ ወደምትሰራበት ባንክ ሄዶ ጠየቀ ። ለአንድ ወር ያህል ገብታ ስራ ገብታ እንደማታውቅ ነገሩት ።
.............
የጎዳና ተዳዳሪው ጃክሰን ይህን ሲሰማ በጣም አዘነ ፡ አዝኖ ብቻ አልተወም ፡ እኖርበታለሁ ወዳለችው ወደከተማዋ ዳርቻ ያሉ መንደሮች ሄዶ ለመፈለግ ወደዚያው ተጓዘ ።

..............
ኩርቲስ ጃክሰን ከብዙ ፍለጋ በኋላ ፡ የሳንዲ ፒርስን መኖሪያ ቤት አገኘ ፡ ነገር ግን በውስጡ ማንም አልነበረም ። ቤቱ በራፍ ላይ የሚከራይ የሚል ፅሁፍ ተለጥፎ ጭር ብሏል ። ያቺ ደግነቷን ሳትነፍግ ትረዳው የነበረችው ሴት ከነልጇ ቤቱን ለቀው ሄደዋል ።

............
ምን እንደተፈጠረ ማወቅ ፈልጎ አንድ ጎረቤቷን ጠየቀ
ሳንዲ ፒርስ ከአንድ ወር በፊት በማታውቀው ሁኔታ ከስራዋ እንደተባረረች ፡ ለተወሰነ ጊዜም ፡ በአቅራቢያ በሚገኝ ሆቴል ክፍል እየተከራየች መቆየቷንና ፡ ያላትን ጥቂት ገንዘብ ጨርሳ የሆቴል መክፈል ሲያቅታት ፡ ከአስር አመት ልጇ ጋር መኪናዋ ውስጥ መኖር እንደጀመረች ነገሩት ።
.........
የጎዳና ተዳዳሪው ኩርቲስ ጃክሰን ይህን ነገር እንደሰማ ፡ መኪናዋን አቁማ ወደምትኖርበት ቦታ ሄደ ፡ እንዳሰበው ፡ የ39 አመቷ ፡የቀድሞ የባንክ ሰራተኛ ከነልጇ መኪና ውስጥ ሆና ፡ ከሰወች ጋር ስትነጋገር ደረሰ ፡ ሰወቹ ከማህበራዊ አገልግሎት የመጡ ደንብ አስከባሪዎች ነበሩ ። እናም ከ10 አመት ልጇ ጋር መኪና ውስጥ መኖር እንደማትችል በተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያ ቢሰጧትም ፡ መተው ስላልቻለች ፡ መንግስት ልጇን በሃይል ነጥቆ ፡ ወደህጻናት ማሳደጊያ ወስዶ እንደሚያሳድገው ለመጨረሻ ጊዜ እያስጠነቀቋት ነበር ።

..............
ኩርቲስ ጃክሰን ይህን ሲሰማ አዘነ ፡ ሰወቹ ጥለዋት እንደሄዱም ቀርቦ ሰላም አላት ፡ ሳንዲ ፒርስ ፡ ይህ ሰው እሷን ፍለጋ መምጣቱን ስትሰማ አለቀሰች ፡ ህይወት እንደጨለመባት ዳግም እዚህ ብትገኝ መንግስት ልጇን እንደሚነጥቃት ነገረችው ። ኩርቲስ ይህችን ህይወት ፊቷን ያዞረችባትን ስታጽናናው ፡ በቻለችው መጠን ስትረዳው የነበረችውን ሴት በተራው ማፅናናት ያዘ ።
............

ከዚያም ፡ ታርፍበት ወደነበረው ሆቴል እንድትመለስ ፡ ክፍያውንም እሱ እንደሚችልላት ነገራት ፡ ሳንዲ ይህንን ስትሰማ ከዚህ ሰው ላይ የሆቴል መውሰድ ቢከብዳትም ፡ ልጇ ከሷ ጋር እንዲኖር ለማድረግ ያላት ብቸኛ ምርጫ በመሆኑ የኩርቲስን ሃሳብ ተቀብላ ፡ ታርፍበት ወደነበረው ሆቴል አመራች ፡ኩርቲስ ለምኖ ካገኘው ብር የጥቂት ቀን የሆቴል ክፍያ ሰጥቷት ወደተለመደው ቦታው አመራ
............
ሳንዲ ፒርስ ስራ ለመፈለግ ብትሞክርም ምንም ሊሳካላት አልቻለም ፡ እናም ለወራት ፡ በዚህ መልኩ ቆየች ፡ ኩርቲስ ጃክሰን ፡ ከወትሮው የበለጠ ፡ ብዙ ሰወችን እየለመነ ፡ ለምግብ ብቻ የሚበቃውን ይቀንስና ፡ በየእለቱ ወደ ሳንዲ ወደተከራየችው ሆቴል በመሄድ ፡ ክፍያውን ይፈፅምላታል ። ኑሮ መልካም በሆነላት ሰአት ደግነቷን ፡ ላልነፈገችው ሴት ከልጇ ጋር ሳትነጣጠል እንድትኖር በማድረጉ ደስተኛ ነው ።
................
እናም ለወራት እየተመላለሰ ፡ ዘጠኝ ሺህ ዶላር በየጊዜው ሰብስቦ ለሳንዲ ፒርስ ሰጥቷታል ። እናም ግን አንድ ቀን እንደተለመደው ክፍያውን ሊሰጣት ሲሄድ ሳንዲ ፒርስ ትልቅ የምስራች ይዛ ጠበቀችው ።
የስራ ማመልከቻ ያስገባችበት ባንክ ቤት ፡ ከዚህ በፊት ታገኝ ከነበረው ደሞዝ እጥፍ ክፍያ በመክፈል ሊቀጥራት በመወሰኑ ዛሬ ውል እንደፈፀመች ። እናም ከነገ ጀምሮ ቅድሚያ ብድር ወስዳ ፡ ጥሩ ቤት መያዝ እንዳሰበች ነገረችው ።
................
ያንን የጨለማ ጊዜ ፡ ከሰወች እየለመነ ያሳለፋትን ደግ ሰው መቼም እንደማትረሳው ፡ የሱም ህይወት የሚሻሻልበትን መንገድ እንደምትፈልግ ነገረችው ። ኩርቲስ ጃክሰን ደግነቷን ሳትነፍግ መልካም ስታደርግለት የነበረችው ሴት በሆነላት መልካም ነገር ሁሉ ተደሰተ ።
..............
በቻልነው መጠን መልካም እናድርግ መልካምነት መልሶ ይከፍላል ።

© ዋስይሁን
ቢላል ለምን ሞተ?
* * *

ስምንት ቀን ስንት አመት ነው? ሃዘን ያጠላበት አንድ ቀን በስንት አመት ይመነዘራል? ፍስሃ ከተቀላቀለው ግማሽ ዘላለም እና ሃዘን ከደቆሰው አንድ ሳምንት ረዥሙ የቱ ነው?
ሰቆቃ ቀንን ዘልዛላ ያደርጋል፤ ህይወት ምሬት ሲጫናት የሰኣት አጋማሽ ከአእላፍ ቀናት ይልቅ ይረዝማል።

አይሻ ከሳምንት በፊት ወጣት ነበረች። ሃዘን ሲደቁሳት በቀናት እድሜ አሮጊት መሰለች። ቀይ መልኳ ጠቆረ፥ ፊቷ በማዲያት ተወረረ፥ ሃዘን አጎሳቆላት፥ መጎሳቆሏ አጎበጣት፥ ከናፍሮቿ ተሰነጣጠቁ፥ በረዶ መሳይ ጥርሶቿ ዝገት ያገኛቸው መሰሉ።
ከስምንት ቀናት በፊት ከነ አይሻ ቤት አቅጣጫ በተሰማ ከባድ ጩኸት ሰፈሩ ተናወጠ። ተሯሩጠን ቤታቸው ስንደርስ አይሻ በድንጋጤ በድን ሆና ቆማለች። ልጇ ዲና ቀሚሷን ጨምድዳ ይዛ በሃይል ታለቅሳለች።

"ምንድነው የተፈጠረው?" ግራ ገባኝ
"ቢላል... ቢላል... ቢ ላ ል" ያቤፅ ተንተባተበ
"ቢላል ምን ሆነ?"
"ቢ... ላል...." ትንፋሽ አጠረው
"ቢላል ምን ሆነ?" ትዕግሥት አጣኹ
"ቢላል...... ራሱን አጠፋ"
"ኢናሊላሂ..."

ዲና በሃይል ጮኸች።

ዲና፥ መልከመልካሟ፥ ትንሿ አበባ፥ ፍልቅልቋ ኮከብ ከፍ ባለ ድምፅ አለቀሰች።
ይህ ከሆነ ሳምንት አለፈው።

ወዳጃችን ቢላል፥ ታታሪው ሰራተኛ፥ የአባትነት ተምሳሌቱ፥ እውነተኛው አፍቃሪ፥ ከልግስና የማይጎድለው፥ ለዲኑ የሚታመነው..... ወንድማችን ቢላል ላይመለስ አንቀላፋ፥ከራሱ ተጣላ፥ በገዛ እጁ ራሱን አጠፋ።

ከአንድ አሏህ በቀር ማንም ቢሆን በሰው ነብስ ላይ የመወሰን ስልጣን እንደሌለው ቢያውቅም ከመርህ አፈነገጠ። ከሚታመንለት እውነት ጋር ተላለፈ።

"ስራ ጠፍቷል። ቤተሰብ ለማስተዳደር እየተቸገረ ነበር" ያቤፅ ከቀብሩ ማግስት ሃዘን በሰበረው መንፈስ ሆኖ አናገረኝ።
"መተጋገዝ እንችል ነበር፥ ራሱ ላይ መፍረድ አልነበረበትም"
"የሰውን እጅ ማየት ያታክታል። እንደቢላል አይነት ኩሩ እና ታታሪ ሰው ራሱን ለጥገኝነት አሳልፎ መስጠት አይሆንለትም። እርሱ መለገስን እንጂ የሰውን እጅ ማየትን አያውቅበትም፥ ከጎዶሎው ላይ ቀንሶ ለሌሎች ቸርነትን ያደርጋል እንጂ ለጎደለው ነገር የሰው እጅ አያይም"
"ቢሆንም ..." ሃሳቤን በእንጥልጥል ተውኩት
ሳምንት አለፈ። ወጣቷ አይሻ አረጀች፥ ፅጌሬዳዋ ጠወለገች፥ ሃዘን አጎሳቆላት፥ ውበቷ ከሸፈ፥ በሳምንት እድሜ ከወጣትነት ወደ እርጅና ተሸጋገረች።

* * *
"ይኼ ቆሻሻ መንግስት ቢላልን ነጠቀን" ያቤፅ ደነፋ
"ምን አልክ?" የሰማሁትን ማመን አልሆነልኝም። ጆሮዬን በአጭበርባሪነት ጠረጠርኩት
"ቢላልን የቀማን መንግስት ነው"
አሁንም ጆሮዬን ማመን ስላልቻልኩ 'ሰልሰው እስቲ' ማለት ቃጥቶኝ ነበር። 'ያቤፅ አብዶ ይሆን' የቅፅበት ጥያቄ አቃጨለብኝ።
"ቢላል ለምን የሞተ ይመስልሃል?" ጠየቀኝ
"ኑሮ ስለከበደው" መለስኩ
"ኑሮ ለምን ከበደው?" ተኮሳተረ
"ሲሚንቶ ስለተወደደ፥ የግንባታ እቃዎች ዋጋ ስለናረ፥ የኮንስትራክሽን ዘርፉ ክፉኛ ስለተጎዳ፥ የግንባታ እንቅቃሴ መቋረጥ ስለጀመረ ፥ ግንበኛው ጓደኛችን ላይ ስራ አጥነትን አመጣበት። ስራ ማጣቱ ኑሮውን አከበደው። ይኸው ነው" ሁለታችንም የምናውቀውን ነገርኩት
"ይኽ ለምን ሆነ?"

....

ነገን ፍለጋ
ተስፋአብ ተሾመ
ኤጭ! ...ይኼ እሁድ መጣ ደ'ሞ!
°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°

"አንተ!"

"የፈጣሪ ያለኽ! ...ምን ያስጮኽሻል? ...አስደነገጥሽኝ እኮ!"

"ይኼ ምንድን ነው?"

"ምኑ እናቴ?"

"ይኼ!"

"እስኪ መነጽሬን አቀብዪኝ፤ ምንድን ነው?"

"አታሹፍ!"

"ኣ? ...ምን? ...ምኑ? ...የቱ? ...የማን ነው?"

"ከምትንተባተብ ራስኽ ንገረኝ እንጂ!"

"በ ለ ው! ...እነዚኽ ከይሲ ልጆች ከየት አግኝተው አምጥተውት ነው!? ...ትናንት ከቤት ወጥተው ነበር እንዴ?"

"ዝጋ! ...ልጆቼን ያለ ኀጢአታቸው አትስደባቸው! ...የተገኘው ትናንት ለብሰኸው የዋልኸው ጃኬት ውስጥ ነው!"

"ተረጋጊ እናቴ! ...ተረጋጊ! ...መቸም በዚኽ ትዳር የማይቀናብኝ የለም። አንዷ ምቀኛ! ...ኦ! ይቅርታ! አንዱ ምቀኛ መስክሬን ዐይቶ ኪሴ ውስጥ ከትቶብኝ ይኾናል እንጂ፣ እኔም ይኸው ካንቺ እኩል ማየቴ ነው!"

"ዝ..ም በል እኮ ነው የምልኽ!"

"እንዴ! ...እንዴ! ጥፊው ታዲያ ምንድን ነው? ...አበድሽ እንዴ?"

"ማበድ ይነሰኝ!? በዚኽ ልክስክስ አመልኽ ጨርቄን መጣል ይነሰኝ!?"

"ግዴለም እናቴ! ተረጋጊ! ...ትዳር መቼም እንደዚኽ ነው። አንዳችን እሳት ስንኾን አንዳችን ውኃ መኾን አለብን! ...ተረጋጊ! ...የሚጠጣ ውኃ ላምጣልሽ?"

"ቆይ እሺ ምን ልኹን!? ...ትዳሬን ባልኹ! ልጆቼን ባልኹ! ኑሬዬን ባልኹ! እድሜ ልክ ያንተ መጫወቻ ኾኜ ልቅር!?"

"ቀስ! ኧረ ቀስ! ...ልቅሶውን ምን አመጣው ታዲያ!? ...ልጆቹም ይተኙበት!"

"የራሳቸው ጉዳይ!"

"ቀስስስስ... ! ይኸውልሽ እናቴ! ...ነገሩን በማስተዋል ብታዪው እኮ ይኼን ያኽል የሚያበሳጭ አይደለም!"

"ተው እንጂ! ...እ!"

"ጤናዬን ለመጠበቅ! ...ያንቺን የሚስቴን፣ የልጆቼን እናት ጤና ለመጠበቅ እንደምጠቀም፣ ኦ! ይቅርታ! ማለቴ እንደገዛኹት ብታስቢው ጥሩ ነው!"

"እስከ ዛሬስ በሽታ ላይ እንዳልጣልኸኝ በምን አውቃለኹ!?"

"በስማም በዪ አንቺ! ...የሰይጣን ጆሮ ይደፈን! ...ሆ!"

"በቃኝ! በቃኝ! በቃኝ!"

"ምኑ?"

"ይኼ ኑሮ! ...ካንተ ጋር የምኖረው የተልከሰከሰ ሕይወት! ...ከዚኽ በላይ በደል የምሸከምበት ጫንቃ የለኝም!"

"ኮንዶም ባሌ ኪስ ተገኘ ብሎ ይኽን ያኽል ምሬት!? ...ኧረ ተዪ! ፈጣሪን በጦር አትውጊ!?"

"ዝ...ም በል አንተ ልክስክስ ሴሰኛ! ...ዝም በል!"

"እሺ! ...እሺ! ...በዪኝ ግዴለም! ...አጋጭኝ! ...እችለዋለኹ! ...እጅሽ ደግሞ ማቃጠሉ!"

"ቆይ ከእኔ ምን አጥተኽ ነው? ...ምን አጎደልኹብኽ!?"

"ያገኘሽው ኮንዶም እኮ ዐዲስ ነው። አገልግሎት ላይ አልዋለም!'

"ኡኡይ! ዝ...ም በል እኮ ነው የምልኽ! ...ሰይጣኔን አታምጣው!"

"የምን አታምጣው ነው? ...መጥቷል እኮ! ...መጥተዋል። አብራችኹ ናችኹ እኮ! ...ጥፊውን ብቻ አስቀሪልኝ! ...ሌላውን እችለዋለኹ።"

"ውሻ ነኽ እሺ!"

"ነኝ! ...ለዛሬ ነኝ! ...ይኹን! ብቻ አንቺ ተረጋጊ!"

እ ፎ ይ! ኼደች።

"ኧረ ቀስ በሩን! ...ያን የጸሎት መጽሐፍ የት ነው ያደረግሽው? ...በ ለ ው! ደኅና የኼደችልኝን እጠራታለኹ እንዴ! ...እውነት የት ነው ያደረግኹት!? ...ወይኔ! በእኩለ ጾም እንዲኽ ልነጀስ!? ...አይ አንተ ሰይጣን ለዛሬ ተሳኽቶልኻል። ...ቆይ ግዴለም! ...አኹን ጸሎቴ ላይ ድፍት ስል የቤቱ ሰላም ይመለሳል። ...ኤጭ! ይኼ መጽሐፍ የት ኼደ ደ'ሞ!?

© በኃይሉ ገብረእግዚአብሔር

በአብሮነት እንቆይ
@kinchebchabi
አፍሪካን በ 352 ቀናት...

አፍሪካን በ352 ቀን ሮጦ የጨረሰው 🌍

ይህ ሰው ከባድ ፈተናዎችን ሲጋፈጥ የመጀመሪያው አይደለም፡፡ ከዚህ በፊት ከቱርኳ ኢስታንቡል እስከ እንግሊዟ ለንደን ድረስ ሮጧል፡፡ ለአንድ ሳምንት በህይወት ተቀብሯል፡፡ መኪና እየጎተተም ማራቶን ለመሮጥ ሞክሯል፡፡ ይሁን እንጂ የአፍሪካን ርዝመት መሮጥ የህይወቱ ከባዱ ፈተና ነበር ተብሏል፡፡

ረስ ኩክ ይባላል፡፡ እንግሊዛዊ ነው፡፡ ከ352 ቀናት በፊት በደቡብ አፍሪካ ከሚገኘው የመጨረሻው ደቡባዊ ጫፍ ላይ ነበር የሚገኘው፡፡ ቦታዋ ደሞ የደቡብ አፍሪካዋ ኬፕ አጉላስ ናት፡፡ ታዲያ ማድረግ አይደለም ለማሰብ የሚከብደውን ተግባር አንድ ብሎ ጀመረ፡፡ በሩጫ አፍሪካን መጨረስ፡፡ በሩጫ ከደቡብ እስከ ሰሜን ጫፍ ማቋረጥ፡፡ መንገዱ ግን አልጋ በአልጋ አልነበረም፡፡

ከፍተኛ የሆነ የጤና እክል ገጥሞት ያውቃል፣ መሳርያ ተደግኖበት ተዘርፏል፣ ቪዛ ለማግኘት ተቸግሯል፣ በሰሃራ በረሃ ሙቀት ነዷል፣ የተለያዩ አስፈሪና ከባድ ተራራዎችን እንዲሁም ጥቅጥቅ ደኖችን አቋርጧል፡፡

ለዚህም እንደ አብነት ጉዞውን ከጀመረ በኋላ በ200ኛ ቀኑ ላይ በጤና ችግር ምክንያት ናይጄሪያ ውስጥ በሚገኝ ጤና ተቋም ገብቷል፡፡ ከምርመራው በኋላም በቀን የሚጓዘውን ርቀት መጠን ቀንሶ በማስታገሻዎች ጉዞውን ቀጠለ፡፡

እንዲህ እንዲህ እያለ ኩክ መነሻውን ከደቡብ አፍሪካ ደቡባዊ ጫፍ / ኬፕ አጉላስ / እስከ ከሰሜን አፍሪካ ሰሜናዊ ጫፍ ቱኒዚያ /ራስ አንጀላ/ ድረስ ሮጠ፡፡ የማይታሰበውን አሳካ፤ ሊደረግ አይችልም ተብሎ የታመነውንም አደረገ፡፡ በዚህም 16 ሀገራትን አቋርጧል፤ 16 ሺሕ ኪሎ ሜትሮችን አካሏል፡፡ ጠቅላላ የሮጠው በማራቶን ቢቀየር ደሞ 376 ማራቶን የመሮጥ ያህል ነው ይለናል የዘጋርዲያን ዘገባ፡፡ የሆነው ሆኖ ኩክ የመጀመሪያው የአፍሪካን አህጉር ርዝመት የሮጠ ሰው ሆኗል፡፡

ኩክ በሩጫው ጊዜያት ከ756 ሺሕ ዶላር በላይ መሰብሰብ የቻለ ሲሆን ይህንን ገንዘብም በሚያስገርም ሁኔታ ለሁለት የበጎ አድራጎት ድርጅቶች እንደሚያውለው ገልጿል፡፡

ኩክ ጉዞውን በማጠናቀቂያው ምዕራፍ ላይ ለጋዜጣው እንደገለጸው ከቤተሰብ ተለይቶ ይህንን ከባድ ጉዞ መጀመር ከባድ እንደነበር ገልጾ በዛ ላይም ህመም ይሰማው እንደነበርና ሌሎች ችግሮችም እንዳጋጠሙት ተናግሯል፡፡ ነገር ግን ህልሙን ሳያሳካ መቆም እንዳልፈለገ ጠቁሟል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም ሌሎች ሰዎች ህልማቸውን ማሳካት እንደሚችሉ ማሳያ ለመሆን ጉዞውን እንደጀመረ ጠቅሶ በመጨረሻም እንዳለው ተሳክቶለት የጽናት ምሳሌ ለመሆን ችሏል፡፡

በአብሮነት እንቆይ
@kinchebchabi
ከ112 ዓመታት በፊት በዛሬው ዕለት የሰጠመችው ግዙፏ የታይታኒክ መርከብ

ታይታን (ታይታኒክ) - Unsinkable Ship ...
ቅንጭብጭብ
ከ112 ዓመታት በፊት በዛሬው ዕለት የሰጠመችው ግዙፏ የታይታኒክ መርከብ ታይታን (ታይታኒክ) - Unsinkable Ship ...
#Ethiopia | ታይታኒክ የተገነባችው ሰሜን አይርላንድ ውስጥ “White Star Line” በተባለ ካምፓኒ ነው፡፡

ታይታኒክ 269 ሜትር ርዝመት፣ 28 ሜትር ስፋት፣ 32 ሜትር ቁመት እንዲሁም ከ47 ሚሊዮን ኪ.ግራም በላይ ክብደት ነበራት፡፡

ታይታኒክ የተሰራችው በ7.5 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ነው፡፡ እ.አ.አ በ1997 ለእይታ የበቃው የጀምስ ካሜሮን ፊልም ታይታኒክ 200 ሚሊዮን ዶላር ወጥቶበታል፡፡

ታይታኒክ በቀን 600 ሺህ ኪ.ግራም ከሰል ትጠቀም ነበር፡፡

ታይታኒክ ከእንግሊዝ ሳውዝ ሀምፕተን ከተማ ወደ ኒውዮርክ ጉዞ የጀመረችው እ.አ.አ ሚያዚያ 10 ቀን 1912 ነው፡፡

መርከቧ ለ4 ቀናት የተሳካ ጉዞ ካደረገች በኃላ 30 ሜትር ቁመት ካለው የበረዶ ግግር ጋር የተላተመችው ሚያዚያ 14 ቀን 1912 ከሌሊቱ 5 ሰዓት ከ40 አካባቢ ነው፡፡ መርከቧ ሙሉ በሙሉ ለመስጠም 2 ሰዓት ከ40 ደቂቃ ፈጅቶባታል፡፡

በአደጋው ወቅት ከ2 ሺህ 200 በላይ ሰዎች መርከቧ ውስጥ ነበሩ፡፡ ከእነዚህ ውስጥ በህይወት የተረፉት 706 ሰዎች ብቻ ናቸው፡፡

ታይታኒክ ውስጥ 20 ህይወት አድን ጀልባዎች ነበሩ፡፡ ጀልባዎቹ እያንዳንዳቸው እስከ 64 ሰው የመያዝ አቅም ቢኖራቸውም መርከቧ ውስጥ በተፈጠረው ትርምስ ጥቂት ሰዎችን ብቻ ነበር እየያዙ የወረዱት፡፡

በታይታኒክ አደጋ የሞቱት አብዛኞቹ ወንዶች ናቸው፡፡ ይህም የሆነው ወደ ማምለጫ ጀልባዎች እንዲገቡ ቅድሚያ ለሴቶች እና ለህጻናት በመሰጠቱ ነው፡፡

ከሟቾች ውስጥ 26ቱ ጫጉላ ላይ የነበሩ ጥንዶች ናቸው፡፡

የታይታኒክ የሙዚቃ ባንድ አባላት መርከቧ እስክትሰጥም ድረስ ሙዚቃ መጫወት አላቆሙም ነበር፡፡

መርከቧ ውስጥ የነበሩ አንድ ቄስ ሁለት ጊዜ ወደ ህይወት አድን ጀልባዎች እንዲገቡ ተጠይቀው እሺ ሳይሉ ቀርተዋል፡፡ ቄሱ እስኪሰጥሙ ድረስ ከሞት ጋር የተፋጠጡ ክርስቲያኖችን ኑዛዜ (ንስሐ) ሲሰሙ እና ስርየት ሲለምኑ ነበር፡፡
የታይታኒክ ዋና ካፒቴን ኤድዋርድ ስሚዝ ለመርከቧ ሰራተኞች ያስተላለፉት የመጨረሻ መልዕክት እንዲህ የሚል ነበር፡፡ “ወድ ሰራተኞች የሚጠበቅባችሁን ሁሉ አድርጋችሁል፡፡ ከዚህ በላይ እንድታደርጉ የምጠይቃችሁ ምንም ነገር የለም፡፡ የባህር ላይ ህግን ታውቃላችሁ፡፡ አሁን ሁሉም ሰው ለራሱ ነው፡፡ ፈጣሪ ይባርካችሁ”፡፡

ታይታኒክ ከባህር በታች በ3 ሺህ 840 ሜትር ጥልቀት ነው የሰጠመችው፡፡

ታይታኒክ ከመስጠሟ ከ14 ዓመታት በፊት በ1898 ሞርጋን ሮበርትሰን የተባለ እውቅ ደራሲ ‘ሊሰጥም የማይችለው መርከብ (unsinkable ship) ከበረዶ ግግር ጋር ተላትሞ ሰጠመ’ የሚል ጭብጥ ያለው መጽሐፍ ለንባብ አብቅቶ ነበር፡፡ ደራሲው በምናብ ለፈጠራት መርከብ የሰጣት መጠሪያም “ታይታን” የሚል ነበር፡፡

የታይታኒክ መርከብ ፍርስራሽ የተገኘው አደጋው ከደረሰ ከ73 ዓመታት በኋላ ዶ/ር ሮበርት ባላርድ በተባለ አሜሪካዊ የስነ ውቅያኖስ ተመራማሪ ነበር፡፡ ጊዜውም እ.አ.አ 1985 ዓ.ም ነበር፡፡

የታይታኒክ ፊልም መሪ ተዋናይት ኬት ዊንስሌት “ማይ ኸርት ዊል ጎ ኦን” የተሰኘውን የፊልሙን ማጀቢያ ሙዚቃ እንደምትጠላው ተናግራ ነበር፡፡ ኬት “ሙዚቃውን ስሰማው ሊያስመልሰኝ ይደርሳል“ ነበር ያለችው፡፡

ታይታኒክ ፊልም በ11 ዘርፎች ኦስካር (አካዳሚ አዋርድ) አሸንፏል፡፡ ከሽልማቶቹ ውስጥ ግን አንዱም በተውኔት ዘርፍ የተገኘ አይደለም፡፡ የፊልሙ መሪ ተዋናዮች ኬት ዊንስሌት እና ሊዮናርዶ ዲ ካፔሪዮ በምርጥ ትወና አልተሸለሙም፡፡

© ኢዮብ መንግስቱ - በአብሮነት እንቆይ
@kinchebchabi
የማባልጋት ባለትዳር ነበረች ።

ዋና ተግባራችን ወሲብ ነው ። የምንቀጣጠረው ለወሲብ ብቻ ነው ። የምናወራው ስለ ወሲብ ነው ። አንዳችን አንዳችንን የምንፈልገው ወሲብ ሲያምረን ነው ።

አጠገቤ ሆና ባሏ ደውሎ ያውቃል: "ሰውዬሽ ደወለ" ብዬ ስልኳን አቀብያት አቃለሁ ። ምንም እንዳልተፈጠረ ስታወራው እርቃኗን አትመስልም ነበር። ይገርመኛል ድድብናችን ።

ነውራችን ስለተደጋገመ ተግባራችን ብልግና መሆኑ ተሰወረብን ።

ቢሮዋ እሄዳለሁ፣ ቢሮዬ ትመጣለች ። ጓደኛዬ ቤት፣ እኔ ቤት፣ የሆነ ኮስመን ያለ ሰዋራ ቦታ ፣የሆነ ድብቅ ፅድት ያለ ስፍራ ፣ መኪና ውስጥ ... ብዙ ብዙ ቦታ ትመጣለች እንዋሰባለን ። የታሪካችን መነሻ እና መድረሻው ወሲብ ነው ።
አንድ ቀን በደነገጠ: ተስፋ በቆረጠ ድምፅ "ባሌ አወቀብን" አለችኝ .....ደነገጥኩ ።

ጠፋሁኝ ...ጠፋች

ከአስራ ሰባት ቀን በኋላ ጓደኞቼ "ገኒ ሃዘን ላይ ነች፣ ሙሉ ከላይ እሰከታች ጥቁር ለብሳለች፣ ከስታለች" አሉኝ

"ምን ሆነች?" አልኩ

"ባሏ ሞቶባት ነው፤ ራሱን አጥፍቶ ነው የሞተው" አሉ።

ስደነግጥ፣ ፊቴ ሲቀያየር ፣ እምባዬ ሲያመልጠኝ አዝኜለት ነው የመሰላቸው ። እኔ እንደገደልኩት አልጠረጠሩም ።

የጥፋተኝነት ስሜት ሊገለኝ ሲል ማምለጫ መፅሃፍ ቅዱስ ገለጥኩ።

"ሰው የሚዘራውን ሁሉ ያንኑ ደግሞ ያጭዳል " የሚለው ከሁሉም ጎልቶ ተነበበኝ ።
..
ሰው ይዞ መውደቅ ፤ ማስተካከል የማይቻል አወዳደቅ ፣ ሲያስታውሱት የሚያስነክስ አይነት አወዳደቅ፣ እነሳለሁ የማይሉት አወዳደቅ ፣ ወድቄ ነበር የማይሉት አወዳደቅ። በግዜ ምክንያት የማይደበዘዝ አወዳደቅ ...
እንደዚህ አይነት መውደቅ ሲ..ያ...ስ..ጠ..ላ !! !

© አድኃኖም
HTML Embed Code:
2024/04/19 05:01:02
Back to Top