ያሬዳዊ ግጥም) ያሬድ ከበደ
መንቶ
*
ሼሁም ቆቡን ደፋ የእምነት አባት ቄሱም
መስቀሉን አንግቦ ሻሹን ሲጠመጥም
*
ሙስሊም ክርስትያኑ ፆማቸው ሲገጥም
**
ከመስጅዱ ቅጥር ከበተስኪያን አፀድ
አሀዱ ቅዳሴ ማልዶ ሲባል አዛን
****
የፍቅርን ማዕድ ተቋድሰን ባንድነት
አላህም እግዜር ነው የሚል ቃል ሲገዛን
**
የተሰቀለውን ህማሙን ለማሰብ
አርብ የሚሏት ግብዣ ስታቀጣጥረን
****
እንደየ እምነታችን ስንለማመነው
በፆም በስግደቱ ባንድነት አፍጥረን
*
ዱአ ፀሎታችን ካምላክ ዘንድ ቀርባ
ለልባችን መሻት ፍቅር አስተምራን
**
በዥንጉርጉር ዓለም
####
አንድ እውነት አግባብቶን
እኩል ይሰበካል ወንጌልና ቁራን
>>Click here to continue<<
![](https://photo.hottg.com/u/cdn4.cdn-telegram.org/file/mZCxl-Jtapf7YBI6KxlHo-7IV8m_RZ0t2axVc7M8F-6je2YS5b_-KHhyxh4AWEzQZWQjF-k8s25-zeVtczNhsmxE8HLvDEX7fLG0Rba5frwUxn0QGDfKMIQ2LV2UMIv4W5o4mGhQBBrUKhlk-DT3i9SnK0uPM3jqMI4KYo-QldHM_7Nh8m7EURF0Uu2LVVjTXTZYq-Y9VCjq30LPlKhWCkM91lx961VTR88hVpypAQ8rwNG9t5hKzNS6j4WknLDfJkt8KPKFmli-Vpt0JPXdKZaCrovr4EXlzOgX6y_Y8iSMFFmJjQDStGfwVTuLjfDGeaR95xoP945MvD32bWxG7g.jpg)