Channel: HAppy Mûslimah
፡
:
ቁና ቁና እየተነፈስ የተናደደ ፊቱ ቀልቶ እግሩን እያማታ ቶሎ ቶሎ ይራመዳል ።
ልጄ የሚል ድምፅ የሰማ መስሎት ሲዞር ድቅቅ ያሉ ሽማግሌ በተለማማጭ አይነት ስሜት አይን አይኑን እያዩ እጃቸውን ዘረጉ፤
.....ምን ልስጦት አባባ ያው ባዶ ኪስ ነኝ ያለሁት ባዶ እያለ ኪሱን ገልብጦ አሳያቸው፤
..በሁኔታው ቅር አልተሰኙም."ልጄ አመስግን በአላህ እዝነት ተስፋ አይቆረጥም ባይገባህ ነው እንጂ አንተኮ ኪሱ ባዶ የሆነ ሱሪ አለህ ፡አንተ ያለህ የሌላቸው ብዙ አሉና ባለህ አልሀምዱሊላህ በል..ስታመሰግን የምታመሰግንበት ስታማርር ደግሞ ምታማርርበት ነው ሚሰጥህ "ብለው ማዝገማቸውን ቀጠሉ ።
... "ኪሱ ባዶ የሆነ ሱሪ አለህ.." የአዛውንቱ ንግግር ጆሮ ላይ አስተጋባ ። ""አልሀምዱሊላህ"ይቺ ቃል ልቡ ውስጥ ሲደጋገም ተሰማው።!
:
፡
" #ያለንን ብናውቅ የጎደለን የለም ነበር" ሚለው ንግግር እንዴት ትዝ አለኝ!
@heppymuslim29
:
ቁና ቁና እየተነፈስ የተናደደ ፊቱ ቀልቶ እግሩን እያማታ ቶሎ ቶሎ ይራመዳል ።
ልጄ የሚል ድምፅ የሰማ መስሎት ሲዞር ድቅቅ ያሉ ሽማግሌ በተለማማጭ አይነት ስሜት አይን አይኑን እያዩ እጃቸውን ዘረጉ፤
.....ምን ልስጦት አባባ ያው ባዶ ኪስ ነኝ ያለሁት ባዶ እያለ ኪሱን ገልብጦ አሳያቸው፤
..በሁኔታው ቅር አልተሰኙም."ልጄ አመስግን በአላህ እዝነት ተስፋ አይቆረጥም ባይገባህ ነው እንጂ አንተኮ ኪሱ ባዶ የሆነ ሱሪ አለህ ፡አንተ ያለህ የሌላቸው ብዙ አሉና ባለህ አልሀምዱሊላህ በል..ስታመሰግን የምታመሰግንበት ስታማርር ደግሞ ምታማርርበት ነው ሚሰጥህ "ብለው ማዝገማቸውን ቀጠሉ ።
... "ኪሱ ባዶ የሆነ ሱሪ አለህ.." የአዛውንቱ ንግግር ጆሮ ላይ አስተጋባ ። ""አልሀምዱሊላህ"ይቺ ቃል ልቡ ውስጥ ሲደጋገም ተሰማው።!
:
፡
" #ያለንን ብናውቅ የጎደለን የለም ነበር" ሚለው ንግግር እንዴት ትዝ አለኝ!
@heppymuslim29
በሰርጓ ቀን አንዷ የMakeUp ባለሞያ እቤቷ አምጥታ በጥንቃቄ MakeUp ተሰራች። በጣም ለውበቷ በመጨነቅ በዝግጅቱም ላይ ልዩ ለመሆን ፈልጋ ነበር። ነገር ግን ከዛ ሁሉ የጥንቃቄ ሥራ በኋላ ልክ ቀጠሮው ሲደርስ አንድ ነገር ረስታ ነበር። MakeUp ከመሰራቷ በፊት ውዱእ ማድረግ። ውሃው ወደ ፊቷ እንዲደርስ MakeUpuን ማንሳት ነበረባት። የዝግጅቱ ግዜው ደረሰ፤ በአዲስ ድጋሚ ለመቀባባት ጊዜ አይበቃትም። አንዳንድ ከሷ ጋር የነበሩ ቤተሰቦቿና የ(MakeUp) ባለሞያዎች ‹‹አሁን አትስገጂ.. ዝግጅቱ ካለቀ በኋላ ቀዷእ ታደርጊያለሽ›› አሏት። ነገርግን እሷ አሏህን ስለምትፈራ እነሱን ትታ ፊቷ ላይ የነበረውን በሙሉ በውሃው አንስታ ውዱእ አደረገች። ሶላቷንም መስገድ ጀመረች፤ ነገርግን በጣም ቆየች... ቤተሰቦቿ እሷን መፈለግ ጀመሩ፤ ለካ እሷ ሱጁድ ላይ እያለች ሞታለች...!
አሏህን እንፍራ...ሶላትን አንተዉ....
@heppymuslim29
አሏህን እንፍራ...ሶላትን አንተዉ....
@heppymuslim29
ቁርጥ እርሣቸዉን የምትመስል ቆንጆ ናት፣ ዉብ ዕድሜዋ ለጋብቻ ሲደርስ ብዙ ሰዎች ሊጠይቋት እርሣቸው ጋር መጡ፤ ብዙ የተከበሩና ትላልቅ ሰዎች …
አንዲት ዐሊን የምትወድ የአንሷር ሴት ዐሊ ዘንድ ሄዳ
“ፋጢማን ብዙ ሰው እንደጠየቃት ታውቃለህ ግን?” አለችው፡፡
“አዎን” አላት፡፡
“አንተሰ ለምን ሄደህ አትጠይቅም፤ ለምን ዳሩልኝ አትላቸዉም፣ ትወዳት የለ?” አለችው፡፡
አንገቱን አቀረቀረ
“ድሃ ነኝ ምን አለኝና? በምንድነው የማገባት?” አላት፣
“ዝምብለህ ሂድና ጠይቅ፤ መልካም ነገር ልትሰማ ትችላለህ አብሽር፡፡” ብላ አሳመነችው፡፡
ሄደ፡፡ ፈራቸው፤ እርሣቸው ፊት ተቀምጦ መናገር ከበደው፡፡ እናም ዝም አለ፡፡
“ምነው ዐሊ ምን ሆነህ ነው? ምንድነው ያመጣህ ጉዳይ?” አሉት፤ አከታትለው ጠየቁት፡፡
ዐሊ አሁንም ዝም አለ፡፡
“ምናልባት ፋጢማን እንድሰጥህ ለመጠየቅ መጥተህ እንዳይሆን፡፡” አሉት፡፡
አዎን በሚል ሀሳብ ራሱን ነቀነቀ፤
“ታዲያ ጥሎሽ ይኖርሃልን?” አሉት፡፡
“ምንም የለኝም” አላቸው፡፡
“የሆነ ጋሻ እንዳለህ አስታውሳለሁ፡፡” አሉት፡፡
“አዎን አለኝ፣ ግን እሱ ምን ያደርጋል፣ ምን ዋጋ ያወጣል?” አላቸው፡፡
“ይጠቅማል ሽጠዉና ...፡፡” አሉት፡፡
ቤት ገዙላቸው፤ ጋብቻው ተፈፀመ፡፡
ዐሊ እንዲህ ይላል
'ከዚያ በኋላ ፋጢማን እጅግ ወደድኳት፡፡ አንድም ቀን በስሟ ጠርቻት አላውቅም፤ “ የአላህ መልዕክተኛ ልጅ ሆይ” ነበር የምላት፡፡
ልክ እሷን ሳይ ሀሳብና ጭንቀቴ ሁሉ ይወገዳል፣ ልቤ እረፍት ይሰማዋል፣ አንድም ቀን አስቆጥቻት አላውቅም፣ አንድም ቀን አላስለቀስኳትም፣ አንድም ቀን አስቆጥታኝ፣ አንድም ቀን አስቸግራኝ አታውቅም፡፡ በአላህ አምላለለሁ አንድም ቀን ጀርባዬን ሰጥታችት አላውቅም፤ ሁሌም እጆቿን እንደሳምኳት …
ፋጢማ ከአባቷ ከአላህ መልዕክተኛ (ሶ.ዐ.ወ.) ህልፈት ከስድስት ወር በኋላ ተከተለቻቸው፡፡ በሞተችም ጊዜ ባለቤቷ ዐሊ አጠባት፣ ከፈናትም፣ ወደ ጆሮዋ ጠጋ ብሎም
“ፋጢማዬ እኔ ዐሊ ነኝ፡፡” አላት፡፡
@heppymuslim29
አንዲት ዐሊን የምትወድ የአንሷር ሴት ዐሊ ዘንድ ሄዳ
“ፋጢማን ብዙ ሰው እንደጠየቃት ታውቃለህ ግን?” አለችው፡፡
“አዎን” አላት፡፡
“አንተሰ ለምን ሄደህ አትጠይቅም፤ ለምን ዳሩልኝ አትላቸዉም፣ ትወዳት የለ?” አለችው፡፡
አንገቱን አቀረቀረ
“ድሃ ነኝ ምን አለኝና? በምንድነው የማገባት?” አላት፣
“ዝምብለህ ሂድና ጠይቅ፤ መልካም ነገር ልትሰማ ትችላለህ አብሽር፡፡” ብላ አሳመነችው፡፡
ሄደ፡፡ ፈራቸው፤ እርሣቸው ፊት ተቀምጦ መናገር ከበደው፡፡ እናም ዝም አለ፡፡
“ምነው ዐሊ ምን ሆነህ ነው? ምንድነው ያመጣህ ጉዳይ?” አሉት፤ አከታትለው ጠየቁት፡፡
ዐሊ አሁንም ዝም አለ፡፡
“ምናልባት ፋጢማን እንድሰጥህ ለመጠየቅ መጥተህ እንዳይሆን፡፡” አሉት፡፡
አዎን በሚል ሀሳብ ራሱን ነቀነቀ፤
“ታዲያ ጥሎሽ ይኖርሃልን?” አሉት፡፡
“ምንም የለኝም” አላቸው፡፡
“የሆነ ጋሻ እንዳለህ አስታውሳለሁ፡፡” አሉት፡፡
“አዎን አለኝ፣ ግን እሱ ምን ያደርጋል፣ ምን ዋጋ ያወጣል?” አላቸው፡፡
“ይጠቅማል ሽጠዉና ...፡፡” አሉት፡፡
ቤት ገዙላቸው፤ ጋብቻው ተፈፀመ፡፡
ዐሊ እንዲህ ይላል
'ከዚያ በኋላ ፋጢማን እጅግ ወደድኳት፡፡ አንድም ቀን በስሟ ጠርቻት አላውቅም፤ “ የአላህ መልዕክተኛ ልጅ ሆይ” ነበር የምላት፡፡
ልክ እሷን ሳይ ሀሳብና ጭንቀቴ ሁሉ ይወገዳል፣ ልቤ እረፍት ይሰማዋል፣ አንድም ቀን አስቆጥቻት አላውቅም፣ አንድም ቀን አላስለቀስኳትም፣ አንድም ቀን አስቆጥታኝ፣ አንድም ቀን አስቸግራኝ አታውቅም፡፡ በአላህ አምላለለሁ አንድም ቀን ጀርባዬን ሰጥታችት አላውቅም፤ ሁሌም እጆቿን እንደሳምኳት …
ፋጢማ ከአባቷ ከአላህ መልዕክተኛ (ሶ.ዐ.ወ.) ህልፈት ከስድስት ወር በኋላ ተከተለቻቸው፡፡ በሞተችም ጊዜ ባለቤቷ ዐሊ አጠባት፣ ከፈናትም፣ ወደ ጆሮዋ ጠጋ ብሎም
“ፋጢማዬ እኔ ዐሊ ነኝ፡፡” አላት፡፡
@heppymuslim29
አንድ ሰው ከአንድ መልካም ሰው ጋር ተቀምጦ
ሳላ በረካ የሚባለው ነገር የለም ሲል ሀሳብ አነሳ...!
መልካሙ ሰውም:_ ውሻና በግ ተመልክተሀል ወይ አለው...?
ሰውየውም:- አዎ አለ!
መልካሙ ሰውም:- የትኛው ብዙ ይወልዳል ሲል ጠየቀው..?
ሰውየው:- ውሾች ሰባት ይወልዳሉ በጎች እስከ ሶስት ይወልዳሉ በማለት መለሰ!
መልካሙ ሰውም:- በዙሪያህ ብትመለከት ከሁለቱ የቱ ብዙ ነው ሲል ጠየቀው...?
ሰውየውም:- በጎቹ ብዙ ሁነው እንመለከታለን አለ ...
መልካሙ ሰውም:- የሚታረደው በጎች ናቸው መቀነስ የነበረባቸው እነሱ ነበሩ አይደል?
ሰውየውም:- አዎ አለ
መልካሙ ሰውም:- እንግዲህ በረካ ማለት ይህ ነው ሲል መለሰለት !
ሰውየውም እንዴት ታዲያ ከውሾቹ በጎቹ በረካን ተሰጣቸው ሲል ጠየቀው..?
መልካሙ ሰውም :-በጎች ከለሊት መጀመሪያ ላይ ተኝተው ከፈጅር በፊት ስለሚነሱ ነው ...ውሾች ደሞ ከለሊት መጀመሪያ ጀምረው ይጮሁና ፈጅር ሲደርስ ይተኛሉ የእዝነቱ ጊዜ ያልፍቸዋል በረካም ከነሱ ላይ ይነሳል !
ለሊቱን በማይረባ ነገር ስናነጋው የለይል ረህመት የፈጅር በረካ እንዳያልፈን አደራ!!
@heppymuslim29
ሳላ በረካ የሚባለው ነገር የለም ሲል ሀሳብ አነሳ...!
መልካሙ ሰውም:_ ውሻና በግ ተመልክተሀል ወይ አለው...?
ሰውየውም:- አዎ አለ!
መልካሙ ሰውም:- የትኛው ብዙ ይወልዳል ሲል ጠየቀው..?
ሰውየው:- ውሾች ሰባት ይወልዳሉ በጎች እስከ ሶስት ይወልዳሉ በማለት መለሰ!
መልካሙ ሰውም:- በዙሪያህ ብትመለከት ከሁለቱ የቱ ብዙ ነው ሲል ጠየቀው...?
ሰውየውም:- በጎቹ ብዙ ሁነው እንመለከታለን አለ ...
መልካሙ ሰውም:- የሚታረደው በጎች ናቸው መቀነስ የነበረባቸው እነሱ ነበሩ አይደል?
ሰውየውም:- አዎ አለ
መልካሙ ሰውም:- እንግዲህ በረካ ማለት ይህ ነው ሲል መለሰለት !
ሰውየውም እንዴት ታዲያ ከውሾቹ በጎቹ በረካን ተሰጣቸው ሲል ጠየቀው..?
መልካሙ ሰውም :-በጎች ከለሊት መጀመሪያ ላይ ተኝተው ከፈጅር በፊት ስለሚነሱ ነው ...ውሾች ደሞ ከለሊት መጀመሪያ ጀምረው ይጮሁና ፈጅር ሲደርስ ይተኛሉ የእዝነቱ ጊዜ ያልፍቸዋል በረካም ከነሱ ላይ ይነሳል !
ለሊቱን በማይረባ ነገር ስናነጋው የለይል ረህመት የፈጅር በረካ እንዳያልፈን አደራ!!
@heppymuslim29
«She is ቆንጆ ናት... አፍላ .... 20 አመቷ ነው።
ጎረምሶች ሲያዩዋት አይናቸው ይጎለጎላል። ጎልማሶች አይተው ይመኛታል። ወንዶች ይከጅሏታል። ሴቶች በቅናት እንደ ሽንኩርት ይልጧታል።
🧢 አንድ ቀን እንዲህ ስል ጠየቅኳት።
<<ማግባት የምትፈልጊው ባል ምን መስፈርት እንዲያሟላ ትፈልጊያለሽ? >>
🧢በፍጥነት መለሰችልኝ
የተማረ መሆን አለበት፤ ማስተርስ ያለው ይመረጣል። ከተቻለ የግል ቢዝነስ የሚሰራ፤ ካልሆነ ግን አሪፍ ደሞዝ ሊኖረው ግድ ነው። መኖሪያ ቤቱ G+2 ቢሆን ደስ ይለኛል፤ ከG+1 በታች ግን አልፈልግም።
🧢መኪና በጣም ነው የምወደው። አሪፍ መኪኖች ቢኖሩት አሪፍ ካልሆነም ከተጋባን በኋላ እኔ እንዲገዛ አደርገዋለሁ። ሙድ የገባው ቢሆን ደስ
ይለኛል። ሁሌ ግን የሚቅም መሆን የለበትም። ጨዋታ የሚያውቅ ሁሌ የሚያስቀኝ!!!
🧢 ቁመቱ በጣም እንዲረዝም አልፈልግም። እኔ አጠር ስለምል በጣም እንዳይበልጠኝ። ደረቱ ሰፋ ያለ ሆኖ ቦርጭ የሚባል እንዲኖረው አልፈልግም።
🧢ጸጉሩ ፍሪዝ ቢሆን ደስ ይለኛል፤ ድሬድ ቢሆን ደግሞ ነፍስ ነው። አይኑ የሚያምር፤ መልኩ ጸይም መሆን አለበት በጣም ቀይ ወይም በጣም ጥቁር
ወንድ አልወድም። አለባበሱ ዘናጭ መሆን አለበት። የሚወደኝ፤የሚንከባከበኝ፤ ሮማንቲክ የሆነ፤ በሳምንት ቢያንስ ሁለቴ የሻማ እራት ያለበት ሆቴል የሚጋብዘኝ፤ ፤.ከበዓላት እና ቀን በተጨማሪ ስጦታ እያመጣ ስርፕራይዝ የሚያደርገኝ፤ ፍቅር የሚያውቅ፤ በተለያየ ቁልምጫ ስም የሚጠራኝ እና ታማኝ ከእኔ ውጪአንዲት ሴት የማያይ ...
🧢 >>ይበቃል አልኳት እንደማታቆም ስለገባኝ። እንዲህ አይነት ወንድ ኢትዮጵያ ውስጥ ቀርቶ በዩኒቨርሱ ውስጥ እንኳን አይገኝም አልኩ በውስጤ። ለሷ ግን አልነገርኳትም።
ከ5አመት በኋላ ሳገኛት 25 አመቷ ነበር። አላገባችም። ዩኒቨርስቲ ጨርሳ ስራ ይዛለች። አሁንም ታምራለች እንደድሮው ግን የሰው ሁሉ አይን ማረፊያ አይደለችም። መልሼ ያንኑ ጥያቄ ጠየቅኳት።
🧢<<ማግባት የምትፈልጊው ባል ምን አይነት ነገሮች ማሟላት አለበት?>> የማፈቅረው ሰው መሆን አለበት፤ ፍቅር ከሌለ ላገባው አልችልም።
ከማልወደው ሰው ጋር አንድ ቀን ላድር አልችልም። ታማኝ እንዲሆን እፈልጋለሁ። እንዲያከብረኝ እፈልጋለሁ። ጥሩ ስራ ቢኖረው፤ ማንበብ
የሚወድና በሃሳብ የምንግባባ ቢሆን ደስ ይለኛል። ቆንጆና ሃብታም ከሆነ ጥሩ ነው፤ ካልሆነም ግን አብረን ሰርተን መለወጥ እንችላለን። ዋናው መግባባት ነው። በተረፈ ቤተሰቡን የሚወድ እና የማይዋሽ መሆን አለበት። ወንዱ ሁሉ የማይታመን ሆነብን እኮ። ዋናው የሚታመን ከሆነ ሌላው ችግር የለውም>>
ጊዜው ይሮጣል!!! ከ5አመት በኋላ ስንገናኝ አላገባችም። 30 አመት እያለፋት ነበር። ደግሜ ያንኑ ጥያቄ ጠይቅኳት።
<<ማግባት የምትፈልጊው ባል ምን አይነት ነገሮች ማሟላት አለበት?>> ትንሽ አሰብ አደረገኝና
<<የምግባባው ሰው ከሆነ ሌላው ችግር የለውም>> አለችኝ መልኩ፤ ጸጉሩ፤ ሃብቱ፤ እውቀቱስ አልኳት።
<<ወንድ ልጅ ደግሞ መልክ ምን ያደርግለታል? ከቺምፕ (ቺምፓንዚ) መለስ ካለ ሌላው ችግር የለውም>> አለች እየሳቀች።
🧢ከ5 አመት በኋላ ሳገኛት አግብታ ሁለት ልጆች ወልዳ ነበር።ባሏ አጭር፤ ጥቁር፤ መላጣ፤ የከባዳ መኪና ሾፌር አይነት ቦርጭ ያለው፤ሱሪውን ቦርጩ መሃከል ላይ የሚታጠቅ፤ ሁልጊዜ መላጣውን የሚያልበው ነገር ነው።
<<እንዴት ነው ትወጂዋለሽ>> አልኳት
<<ምን ማለትህ ነው ትዳር አይደል?>>
<<ማለቴ ድሮ የነገርሽኝ አይነት ሰው አይደለም ብዬ ነው?>>
<<ያኔማ አየር ላይ ነበርኩ፤ እድሜ መስታወት ነው፤ ብዙ ያስተምራል፤ አሁን ተምረን ልብ ገዝተን ነው>> አለች ተከዝ ብላ።
<<በትዳርሽ ደስተኛ ነሽ?>> አልኳት እያዘንኩ
<<ደስታ አንጻራዊ ነው፤ በልጆቼ ደስ ይለኛል፤ ትዳሬን አከብራለሁ። በተረፈ ግን እየኖርኩ ነው>> አለች ፈገግ ብላ። በዛች ቅጽበታዊ ፈገግታ ውስጥ
የጊዜን ኃይለኝነት አየሁ። በስተመጨረሻም የተረዳሁት ነገር ሴት ልጅ የተጋነነ መስፈርቷ ጠላቷ እየሆነ ነው።»
@heppymuslim29
ጎረምሶች ሲያዩዋት አይናቸው ይጎለጎላል። ጎልማሶች አይተው ይመኛታል። ወንዶች ይከጅሏታል። ሴቶች በቅናት እንደ ሽንኩርት ይልጧታል።
🧢 አንድ ቀን እንዲህ ስል ጠየቅኳት።
<<ማግባት የምትፈልጊው ባል ምን መስፈርት እንዲያሟላ ትፈልጊያለሽ? >>
🧢በፍጥነት መለሰችልኝ
የተማረ መሆን አለበት፤ ማስተርስ ያለው ይመረጣል። ከተቻለ የግል ቢዝነስ የሚሰራ፤ ካልሆነ ግን አሪፍ ደሞዝ ሊኖረው ግድ ነው። መኖሪያ ቤቱ G+2 ቢሆን ደስ ይለኛል፤ ከG+1 በታች ግን አልፈልግም።
🧢መኪና በጣም ነው የምወደው። አሪፍ መኪኖች ቢኖሩት አሪፍ ካልሆነም ከተጋባን በኋላ እኔ እንዲገዛ አደርገዋለሁ። ሙድ የገባው ቢሆን ደስ
ይለኛል። ሁሌ ግን የሚቅም መሆን የለበትም። ጨዋታ የሚያውቅ ሁሌ የሚያስቀኝ!!!
🧢 ቁመቱ በጣም እንዲረዝም አልፈልግም። እኔ አጠር ስለምል በጣም እንዳይበልጠኝ። ደረቱ ሰፋ ያለ ሆኖ ቦርጭ የሚባል እንዲኖረው አልፈልግም።
🧢ጸጉሩ ፍሪዝ ቢሆን ደስ ይለኛል፤ ድሬድ ቢሆን ደግሞ ነፍስ ነው። አይኑ የሚያምር፤ መልኩ ጸይም መሆን አለበት በጣም ቀይ ወይም በጣም ጥቁር
ወንድ አልወድም። አለባበሱ ዘናጭ መሆን አለበት። የሚወደኝ፤የሚንከባከበኝ፤ ሮማንቲክ የሆነ፤ በሳምንት ቢያንስ ሁለቴ የሻማ እራት ያለበት ሆቴል የሚጋብዘኝ፤ ፤.ከበዓላት እና ቀን በተጨማሪ ስጦታ እያመጣ ስርፕራይዝ የሚያደርገኝ፤ ፍቅር የሚያውቅ፤ በተለያየ ቁልምጫ ስም የሚጠራኝ እና ታማኝ ከእኔ ውጪአንዲት ሴት የማያይ ...
🧢 >>ይበቃል አልኳት እንደማታቆም ስለገባኝ። እንዲህ አይነት ወንድ ኢትዮጵያ ውስጥ ቀርቶ በዩኒቨርሱ ውስጥ እንኳን አይገኝም አልኩ በውስጤ። ለሷ ግን አልነገርኳትም።
ከ5አመት በኋላ ሳገኛት 25 አመቷ ነበር። አላገባችም። ዩኒቨርስቲ ጨርሳ ስራ ይዛለች። አሁንም ታምራለች እንደድሮው ግን የሰው ሁሉ አይን ማረፊያ አይደለችም። መልሼ ያንኑ ጥያቄ ጠየቅኳት።
🧢<<ማግባት የምትፈልጊው ባል ምን አይነት ነገሮች ማሟላት አለበት?>> የማፈቅረው ሰው መሆን አለበት፤ ፍቅር ከሌለ ላገባው አልችልም።
ከማልወደው ሰው ጋር አንድ ቀን ላድር አልችልም። ታማኝ እንዲሆን እፈልጋለሁ። እንዲያከብረኝ እፈልጋለሁ። ጥሩ ስራ ቢኖረው፤ ማንበብ
የሚወድና በሃሳብ የምንግባባ ቢሆን ደስ ይለኛል። ቆንጆና ሃብታም ከሆነ ጥሩ ነው፤ ካልሆነም ግን አብረን ሰርተን መለወጥ እንችላለን። ዋናው መግባባት ነው። በተረፈ ቤተሰቡን የሚወድ እና የማይዋሽ መሆን አለበት። ወንዱ ሁሉ የማይታመን ሆነብን እኮ። ዋናው የሚታመን ከሆነ ሌላው ችግር የለውም>>
ጊዜው ይሮጣል!!! ከ5አመት በኋላ ስንገናኝ አላገባችም። 30 አመት እያለፋት ነበር። ደግሜ ያንኑ ጥያቄ ጠይቅኳት።
<<ማግባት የምትፈልጊው ባል ምን አይነት ነገሮች ማሟላት አለበት?>> ትንሽ አሰብ አደረገኝና
<<የምግባባው ሰው ከሆነ ሌላው ችግር የለውም>> አለችኝ መልኩ፤ ጸጉሩ፤ ሃብቱ፤ እውቀቱስ አልኳት።
<<ወንድ ልጅ ደግሞ መልክ ምን ያደርግለታል? ከቺምፕ (ቺምፓንዚ) መለስ ካለ ሌላው ችግር የለውም>> አለች እየሳቀች።
🧢ከ5 አመት በኋላ ሳገኛት አግብታ ሁለት ልጆች ወልዳ ነበር።ባሏ አጭር፤ ጥቁር፤ መላጣ፤ የከባዳ መኪና ሾፌር አይነት ቦርጭ ያለው፤ሱሪውን ቦርጩ መሃከል ላይ የሚታጠቅ፤ ሁልጊዜ መላጣውን የሚያልበው ነገር ነው።
<<እንዴት ነው ትወጂዋለሽ>> አልኳት
<<ምን ማለትህ ነው ትዳር አይደል?>>
<<ማለቴ ድሮ የነገርሽኝ አይነት ሰው አይደለም ብዬ ነው?>>
<<ያኔማ አየር ላይ ነበርኩ፤ እድሜ መስታወት ነው፤ ብዙ ያስተምራል፤ አሁን ተምረን ልብ ገዝተን ነው>> አለች ተከዝ ብላ።
<<በትዳርሽ ደስተኛ ነሽ?>> አልኳት እያዘንኩ
<<ደስታ አንጻራዊ ነው፤ በልጆቼ ደስ ይለኛል፤ ትዳሬን አከብራለሁ። በተረፈ ግን እየኖርኩ ነው>> አለች ፈገግ ብላ። በዛች ቅጽበታዊ ፈገግታ ውስጥ
የጊዜን ኃይለኝነት አየሁ። በስተመጨረሻም የተረዳሁት ነገር ሴት ልጅ የተጋነነ መስፈርቷ ጠላቷ እየሆነ ነው።»
@heppymuslim29
« እንደው ግርም የሚል ነገር ነው። ያቺን የመሰለች ዓሊም እንዴት ብላ ያን ጃሂል እንዳገባች የሚደንቅ ነው! አላቸው ነገሩ ቢያብከነክነው።
ረጋ ብለው ካዳመጡት በኋላ
« ነፍሱን ካመለከ ይልቅ ስለነፍሱ ያላወቀ ይበልጥ መልካም ለመሆን ይቀርባል « አሉትና ዝም አሉ። ንግግራቸውን እንደሰማ ሀፍረትም ንዴትም ተቀላቅለውበት ተለጎመ። »
@heppymuslim29
ረጋ ብለው ካዳመጡት በኋላ
« ነፍሱን ካመለከ ይልቅ ስለነፍሱ ያላወቀ ይበልጥ መልካም ለመሆን ይቀርባል « አሉትና ዝም አሉ። ንግግራቸውን እንደሰማ ሀፍረትም ንዴትም ተቀላቅለውበት ተለጎመ። »
@heppymuslim29
አሥሩ የዙል-ሒጃ ቀናት፡፡
ከዱንያ ቀናት ሁሉ ምርጦቹ፡፡
ዛሬ ዙል-ቂዕዳ 29ኛ ቀን ላይ ነው ያለነው፡፡ ነገ የሚገባው ወር ዙልሂጃ ይባላል ‼️
- ዙል-ሒጃ እጅግ የተከበረ ወር ነው፡፡
- ጦርነት በውስጥ ከተከለከለባቸው ከአራቱ የተከበሩ ወራት ውስጥም አንዱ ናት፡፡
- ከወሩም የመጀመርያዎቹ አሥር ቀናት እጅግ የተከበሩ ናቸው፡፡
- ቀናቶቹ የዙል-ሒጃ ወር ሲጀምር ይጀምራሉ። የዒድ አል-አድሓ ቀን ያበቃሉ፡፡
- ከነኚህ ቀናት ውስጥ ከ8ኛው ቀን ጀምሮ የሐጅ ሥራዎች ይከናወናሉ።
- እነኚህ ቀናት ክቡር መሆናቸው የታወቀ ቢሆንም ብዙዎች በነኚህ ቀናት ዉስጥ ሲዘናጉ ይታያሉ፡፡
- በነኚህ ቀናት ዉስጥ የሚሠሩ መልካም ሥራዎች በየትኛዉም የዱንያ ቀናት ዉስጥ ከሚሠሩት በላይ አላህ ዘንድ ተወዳጅ ናቸው፡፡
- የዐረፋ ቀን ፆም (ዘጠነኛው ቀን) የሁለት ዓመት ኃጢኣት ያስምራል፡፡ ያለፈን አንድ ዓመት እና የሚቀጥለዉን አንድ ዓመት፡፡
- ቀንም ሆነ ሌሊት በነኚህ ቀናት ዉስጥ በዒባዳ መበርታት ይገባል፡፡
- በነኚህ ቀናት ውስጥ የሚሠሩ መልካም ሥራዎች ተወዳጅ የመሆናቸውን ያህል በውስጣቸው የሚሠራ ኃጢኣትም ጥፋቱ ክቡድ ነው፡፡
- እነ ዐብደላህ ኢብኑ ዐመር እና አቢ ሁረይራ በነኚህ ቀናት ዉስጥ ተክቢራ እያደረጉ ወደ ገበያ ይወጡ ነበር፡፡ ሰዎችም አብረዋቸው ተክቢራ (አሏሁ አክበር) ይላሉ፡፡
- በነኚህ ቀናት ዉስጥ ዚክር ማብዛት፣ አላህን ማላቅ ይወደዳል፡፡
- በነኚህ ቀናት ውስጥ ሱብሐነላህ፣ አልሐምዱ ሊላህ፣ ላ ኢላሀ ኢልለላሀ አላሁ አክበር ማለት ይወደዳል፡፡
- በዐረፋ ቀን ዱዓና ዚክር ማብዛት ይመረጣል፡፡ በተለይ ላ ኢላህ ኢልለሏህ ወሕደሁ ላ ሸሪከ ለሁ፤ ለሁልሙልኩ፣ ወለሁል ሐምዱ፣ ወሁወ ዐላ ኩልሊ ሸይኢን ቀዲር … የሚለዉን፡፡
- በነኚህ ቀናት ዉስጥ የሚሠሩ የዒባዳ ዓይነቶች ቀናቶቹን ልዩ ያደርጋቸዋል፡፡ ሶላት፣ ፆም፣ ሶደቃ፣ ሐጅ … ሁሉም የተሰባሰቡባቸው ናቸው፡፡
- ደጋጎች እነኚህን ሦስት አሥርት ልዩ ጊዜያቶች በእጅጉ ትኩረት ይሠጧቸው ነበር፡፡ የረመዷን ወር የመጨረሻዎቹ አሥር ቀናት፣ የዚል ሒጃ ወር የመጀመርያዎቹ አሥር ቀናት፣ የሙሐረም ወር የመጀመርያዎቹ አሥር ቀናት፡፡
ያስታውሱ ቀናቱ ነገ ይጀምራሉ ‼️
@heppymuslim29
ከዱንያ ቀናት ሁሉ ምርጦቹ፡፡
ዛሬ ዙል-ቂዕዳ 29ኛ ቀን ላይ ነው ያለነው፡፡ ነገ የሚገባው ወር ዙልሂጃ ይባላል ‼️
- ዙል-ሒጃ እጅግ የተከበረ ወር ነው፡፡
- ጦርነት በውስጥ ከተከለከለባቸው ከአራቱ የተከበሩ ወራት ውስጥም አንዱ ናት፡፡
- ከወሩም የመጀመርያዎቹ አሥር ቀናት እጅግ የተከበሩ ናቸው፡፡
- ቀናቶቹ የዙል-ሒጃ ወር ሲጀምር ይጀምራሉ። የዒድ አል-አድሓ ቀን ያበቃሉ፡፡
- ከነኚህ ቀናት ውስጥ ከ8ኛው ቀን ጀምሮ የሐጅ ሥራዎች ይከናወናሉ።
- እነኚህ ቀናት ክቡር መሆናቸው የታወቀ ቢሆንም ብዙዎች በነኚህ ቀናት ዉስጥ ሲዘናጉ ይታያሉ፡፡
- በነኚህ ቀናት ዉስጥ የሚሠሩ መልካም ሥራዎች በየትኛዉም የዱንያ ቀናት ዉስጥ ከሚሠሩት በላይ አላህ ዘንድ ተወዳጅ ናቸው፡፡
- የዐረፋ ቀን ፆም (ዘጠነኛው ቀን) የሁለት ዓመት ኃጢኣት ያስምራል፡፡ ያለፈን አንድ ዓመት እና የሚቀጥለዉን አንድ ዓመት፡፡
- ቀንም ሆነ ሌሊት በነኚህ ቀናት ዉስጥ በዒባዳ መበርታት ይገባል፡፡
- በነኚህ ቀናት ውስጥ የሚሠሩ መልካም ሥራዎች ተወዳጅ የመሆናቸውን ያህል በውስጣቸው የሚሠራ ኃጢኣትም ጥፋቱ ክቡድ ነው፡፡
- እነ ዐብደላህ ኢብኑ ዐመር እና አቢ ሁረይራ በነኚህ ቀናት ዉስጥ ተክቢራ እያደረጉ ወደ ገበያ ይወጡ ነበር፡፡ ሰዎችም አብረዋቸው ተክቢራ (አሏሁ አክበር) ይላሉ፡፡
- በነኚህ ቀናት ዉስጥ ዚክር ማብዛት፣ አላህን ማላቅ ይወደዳል፡፡
- በነኚህ ቀናት ውስጥ ሱብሐነላህ፣ አልሐምዱ ሊላህ፣ ላ ኢላሀ ኢልለላሀ አላሁ አክበር ማለት ይወደዳል፡፡
- በዐረፋ ቀን ዱዓና ዚክር ማብዛት ይመረጣል፡፡ በተለይ ላ ኢላህ ኢልለሏህ ወሕደሁ ላ ሸሪከ ለሁ፤ ለሁልሙልኩ፣ ወለሁል ሐምዱ፣ ወሁወ ዐላ ኩልሊ ሸይኢን ቀዲር … የሚለዉን፡፡
- በነኚህ ቀናት ዉስጥ የሚሠሩ የዒባዳ ዓይነቶች ቀናቶቹን ልዩ ያደርጋቸዋል፡፡ ሶላት፣ ፆም፣ ሶደቃ፣ ሐጅ … ሁሉም የተሰባሰቡባቸው ናቸው፡፡
- ደጋጎች እነኚህን ሦስት አሥርት ልዩ ጊዜያቶች በእጅጉ ትኩረት ይሠጧቸው ነበር፡፡ የረመዷን ወር የመጨረሻዎቹ አሥር ቀናት፣ የዚል ሒጃ ወር የመጀመርያዎቹ አሥር ቀናት፣ የሙሐረም ወር የመጀመርያዎቹ አሥር ቀናት፡፡
ያስታውሱ ቀናቱ ነገ ይጀምራሉ ‼️
@heppymuslim29
ሐጀተል ወዳእ
(የመሰናበቻው ሐጅ)
.
.
በወርሀ ዙልሒጃ ከሚነሱ እውነታዎች አንዱ የሆነው የኢስላም አምስተኛው ማእዘን ሐጅ ነው። በነብዩላህ ኢብራሂም አለይሒሰላም እና በልጃቸው ኢስማኢል አማካኝነት በተገነባው ካእባ ዙሪያ የሚደረግ አምልኮ! የቆዳ ቀለም፣ ፆታ፣ ጎሳ፣ ብሔር፣ የሰውነት ገፅታ ሳይለያያቸው አቤቱ ጌታችን የሚሉበት የእኩልነት ማሳያ ኢባዳ!
ወቅቱ አስረኛው አመተ ሒጅራ ወርሀ ዙልቃኢዳ ሐያ ስድስተኛው ቀን ቅዳሜ ነበር። ረሱሉ ሰለላሁ አለንሒ ወሰለም በይፋ ለሐጅ መነሳታቸውን ካወጁ በኋላ የመዲና ነዋሪዎች (የቻሉት በሙሉ) ከረሱሉ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ጋር በመጣመር ስንቃቸውን ቋጥረውና ለጉዞ ተዘገጃጅተው ወደ መካ ጉዞ ጀመሩ። አቡበከር አስሲዲቅ እየመሩ በዘጠነኛው የሒጅሪያ አመት ወደ መካ ካቀኑ በኋላ ቀጣዩ የጉዞ ቅፍለት መሆኑ ነው። እኚህ መቶ ሺህ የሚደርሱ አስሐቦች ገላቸውን ተጣጥበውና ሐርመው (ኢህራም አድርገው) ጉዞ ተጀመረ።
ረሱሉ ሰለላሁ አለይሒወሰለም ውድ ግመላቸው የሆነችው ቀስዋህ ላይ ከወጡ ጀምሮ መዲና በተልቢያ ተናወጠች።
<<ለበይከላሁመ ለበይክ ለበይከ ላሸሪከ ለከ ለበይክ ኢነል ሐምዳህ ወንኒእመተህ ለከወልሙልክ ላሸሪከለክ>>
<<አላህ ሆይ! (ታዛዥ ሆኜ መጥቻለሁ) አቤት። አንተ ተጋሪ የለሕም አቤት ምስጋናና ፀጋ ያንተ ነው። ንግስናም ያንተ ነው። ተጋሪ የለህም።" ሲሉ በአንድ ድምፅ ያስተጋባሉ።
የመጀመሪያው የጉዞ ማረፊያ አል አሪጅ ሆነ። ቀጣይ አል አብዋእ፣ አስፋን፣ ዚጡዋህ በቅደም ተከተል የሰፈሩባቸው ስፍራቸው ናቸው። ዚጡዋህ ሲደርሱ ዙልሒጃህ አራተኛው ቀን ነበር። ገላቸውን ተጣጥበው በሰሜን የመካ መግቢያ ወደ ካእባ አቀኑ።
ከነብይነታቸው በፊት ወደቦታው እንዲመልሱ የተመረጡለትን ሐጀር አል አስወድን ስመው ወደ ጠዋፍ ስነስርአት አመሩ። የመጀመሪያዎቹ ሶስት ዙሮች በፍጥነት ቀጣዮቹን አራት ዙሮች ደግሞ እየተራመዱ ካእባን ዞሩ። ከዚህ በኋላ መቃሙ ኢብራሒም ላይ ቆመው የበቀራህን መቶ ሐያ አምስተኛ አያ (አንቀፅ) አነበቡ።
<<ቤቱንም ለሰዎች መመለሻና ጸጥተኛ ባደረግን ጊዜ (አስታውስ)፣ ከኢብራሂምም መቆሚያ መስገጃን አድርጉ፤ ወደ ኢብራሂምና ወደ ኢስማዒልም ቤቴን ለዘዋሪዎችና ለተቀማጮቹም ለአጎንባሾች ሰጋጆቹም አጥሩ ስንል ቃልኪዳን ያዝን፡፡” [አል-በቀራህ፡ 125]
ከዚያም ከመቃሙ ኢብራሒም ትይዩ ሑለት ረከአ ሰላትን ሰግደው ለሁለተኛ ጊዜ ሐጀር አል አስወድን ሳሙት። ሶፋና መርዋ ጋር የሔዱት ከዚህ በኋላ ነበር። ሰፋ ተራራ አጠገብ ሲደርሱ የሚቀጥለውን የቁርአን አንቀፅ አነበቡ።
<<ሰፋ እና መርዋህ ከአላህ ትእዛዝ መፈፀሚያ ምልክቶች ውስጥ ናቸው። ቤቱን (ከእባን) በሐጅ ወይም በኡምራህ ስራ የጎበኘ ሰው በሁለቱ መሀከል በመመላለሱ በርሱ ላይ ሐጢአት የለበትም። መልካምንም ስራ በፈቃደኝነት የሰራ ሰው አላህ ይመነዳዋል። አላህ አመስጋኝ አዋቂ ነውና።>>
[አል በቀራህ:158]
በሰፋና መርዋ መሐል ሰዕይ ካደረጉ በኋላ መስዋእት ያመጡ ሲቀሩ ከኢህራማቸው እንዲፈቱ አዘዙ። መስዋእት ያላመጡት ፀጉራቸውን በማሳጠር ኡምራ ብቻ እንዲያደርጉ ሲታዘዙ ቀሪዎቹ በኢህራማቸው ቆዩ። ረሱሉ ሰለላሁ አለይሒ ወሰለምና ባልደረቦቻቸው መካ ውስጥ ከእሑድ ጀምሮ አራት ቀናትን ቆይተው ሐሙስ ጠዋት ሚና ሰፈሩ። በማግስቱም ከዚህ በፊት ቁረይሾን ከሌላው ተነጥለው ከሚያርፉበት መእሸር አል ሐረምና ሙዝደሊፋ በተቃራኒ ከአረፋህ ተራራ በደቡብ በኩል ባለው ነሚራህ የተሰኘው ቦታ ላይ ቁባ የሚመስል ድንኳን አስተክለው አረፉ።
ነብያችን ሰለላሁ አለይሒ ወሰለም ፀሐይ ወደ ምእራብ ስትገሰግስ ወደ ኡረናህ ሸለቆ አመሩና ከ120 ሺህ ለሚልቀው የሐጅ ታዳሚ ኹጥባ ማድረግ ጀመሩ።
<<ሰዎች ሆይ ንግግሬን አድምጡ። ምናልባት ከዚህ አመት በኋላ በዚህ ቦታ ላይ ዳግም ላንገናኝ እንችላለን። በዚህ በሀገራችሁ በዚህ ወራችሁ የዛሬው ቀን ክቡር እንደሆነ ሁሉ ደማችሁና ሐብታችሁ የተከበረና የማይደፈር ነው። የመሐይምነት ዘመን የደም ብቀላ ውድቅ ሆኗል። መጀመሪያ ውድቅ የሚደረገው የኢብን ረቢአ ኢብን አል ሐሪስ ደም ነው። እርሱ በበኑ ሰዕድ ጎሳ ውስጥ የገባ ሲሆን በሁዘይል ጎሳ ተገድሏል። የቅድመ ኢስላም አራጣ ውድቅ ተደርጓል። መጀመሪያ ውድቅ የተደረገው የዐባስ ኢብኑ አብዱልሙጠሊብ አራጣ ነው።
★በሴቶች ጉዳይ አላህን ፍሩ። የወሰዳችኋቸው በአላህ አደራ ሲሆን ብልቶቻችሁንም ሐላል ያደረጋችሁት በአላህ ቃል ነው። እናንተ በነርሱ ላይ የምትጠሉትን ሰው በፍራሻችሁ ላይ እንዳያስቀምጡ የማድረግ መብት አላችሁ። ይህን ከጣሱ የማይጎዳ ምት ምቷቸው። እነርሱ በእናንተ ላይ ያላቸው መብት ቀለባቸውንና አልባሳታቸውን ልታቀርቡላቸው ነው።
በሚገባ ከያዛችሁት የማትጠምሙበትን ነገር ትቼላችኋለሁ። የአላህን መፅሐፍ! ስለኔ ብትጠየቁ ምን ብላችሁ ትመልሳላችሁ?>> ሲሉ ንግግራቸውን በጥያቄ አሳረጉ።
ሰሐቦችም <<መልእክቱን በሚገባ ማድረስዎትንና እኛንም ከልብ መምከርዎን እንመሰክራለን።>> አሉ። ረሱላችን አለይሒሰላምም እጃቸውን ከፍ አድርገው ወደ ህዝቦቻቸው እየተመለከቱ <<አላህ ሆይ ምስክሬ ሁን፣ አላህ ሆይ ምስክሬ ሁን፣ አላህ ሆይ ምስክሬ ሁን>> በማለት ተናገሩ።
ንግግራቸውን ሲቋጩ የሚከተለው የቁርአን አያ ወረደ። <<ዛሬ ሐይማኖታችሁን ሞላሁላችሁ።ጸጋዬንም በናንተ ላይ ፈፀምኩ። ለእናንተም ኢስላምን ከሐይማኖት በኩል ወደድኩ።>> [አል-ማኢዳህ:3]
ቢላል አዛን አድርጎ ነብያችን ሰለላሁ አለይሒ ወሰለም እና ባልደረቦቻቸው የዙህርን ሁለት ረከአ ሰላት ሰገዱ። ከዚያም ቢላል ሌላ ኢቃም አድርጎ የአስርን ሁለት ረከአ ሰገዱ። ፀሐይ ከገባች በኋላ ወደሙዝደሊፋ በማቅናት በሁለት ኢቃም የመግሪብንና የኢሻን ሰላት ሰግደው ተኙ። ከሱብሒ ስግደት በኋላ ወደ መእሸረል ሐረም ጋለቡ። ወደቂብላ ዞረው ዱአ አደረጉ። ለፀጋው አመሰገኑ።
ከዚህ በኋላ የነበረው ጀምረተል ኩብራ (የጠጠር ውርወራ) ነበር። በእያንዳንዱ ጠጠር ተክቢራ እያደረጉ ሰባቱንም ጠጠር ወረወሩ። የእርድ ስርአቱ ቀጠለ። ስልሳ ሶስቱን ረሱላችን ሰለላሁ አለይሒ ወሰለም ሲያርዱ ሰላሳ ሰባቱን ሰይዱና አሊይ ረዲየላሁ አንሁ አርደው ለሚቀርቧቸው ሰዎች አከፋፈሉ።
ጠዋፈል ኢፋዳን(የመጨረሻ ጠዋፍ) ለመፈፀም ሲሉ ወደመካ ተመለሱ። በዚያው 'ለት ወደሚና ተመልሰው ካደሩ በኋላ ማግስቱን ጀመራት ላይ ጠጠር ጣሉ። በዚህ መልኩ ለተከታታይ ሶስት የዙልሒጃ ቀናት ጠጠር እየወረወሩ ከቆዩ በኋላ ወደ መዲና ጉዞ ጀመሩ። ጁሕፋ አቅራቢያ ሲደርሱ እንዲህ ሲሉ ተናገሩ፣
<<ሰዎች ሆይ እኔ ሰው ነኝ። ምናልባትም የጌታዬ መልእክተኛ(መለከል መውት) ወደኔ ይመጣና መልስ እሰጥ ይሆናል። በመካከላችሁ ሁለት ከባድ ነገሮችን ትቻለሁ። የመጀመሪያው የአላህ መፅሀፍ ነው። ሁለተኛው ደሞ የኔ ቤተሰቦች(አህሉል በይት) ናቸው። የእኔን ቤተሰብ በተመለከተ አላህን እንድትፈሩ እጠይቃችኋለሁ።>>
የመዲና ድባብ ከሩቅ በታያቸውም ጊዜ እንዲህ አሉ። << ከአላህ በስተቀር ሌላ አምላክ የለም። ብቸኛ ነው። አጋርም የለውም። ንግስና የርሱ ነው። ምስጋና የሚገባውም ለርሱ ነው። እሱ በሁሉም ነገር ላይ ቻይ ነው። ንስሐ ገብተን ለአላህ ተገዢዎች፣ ሰጋጆችና አመስጋኞች ሆነን ተመልሰናል። አላህ ቃሉን አረጋገጠ። ባሪያውን ረዳ። ብቻውንም አህዛብን ድል ነሳ።>>
ይህ ነበር የረሱሉ ሰለላሁ አለይሒ ወሰለም የመጨረሻ ሐጅ፣ ለኡማው ፈር የቀደዱለት ከጃሒሊያ በኋላ የነበረ የመጀመሪያው ሐጅ🕋
@heppymuslim29
(የመሰናበቻው ሐጅ)
.
.
በወርሀ ዙልሒጃ ከሚነሱ እውነታዎች አንዱ የሆነው የኢስላም አምስተኛው ማእዘን ሐጅ ነው። በነብዩላህ ኢብራሂም አለይሒሰላም እና በልጃቸው ኢስማኢል አማካኝነት በተገነባው ካእባ ዙሪያ የሚደረግ አምልኮ! የቆዳ ቀለም፣ ፆታ፣ ጎሳ፣ ብሔር፣ የሰውነት ገፅታ ሳይለያያቸው አቤቱ ጌታችን የሚሉበት የእኩልነት ማሳያ ኢባዳ!
ወቅቱ አስረኛው አመተ ሒጅራ ወርሀ ዙልቃኢዳ ሐያ ስድስተኛው ቀን ቅዳሜ ነበር። ረሱሉ ሰለላሁ አለንሒ ወሰለም በይፋ ለሐጅ መነሳታቸውን ካወጁ በኋላ የመዲና ነዋሪዎች (የቻሉት በሙሉ) ከረሱሉ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ጋር በመጣመር ስንቃቸውን ቋጥረውና ለጉዞ ተዘገጃጅተው ወደ መካ ጉዞ ጀመሩ። አቡበከር አስሲዲቅ እየመሩ በዘጠነኛው የሒጅሪያ አመት ወደ መካ ካቀኑ በኋላ ቀጣዩ የጉዞ ቅፍለት መሆኑ ነው። እኚህ መቶ ሺህ የሚደርሱ አስሐቦች ገላቸውን ተጣጥበውና ሐርመው (ኢህራም አድርገው) ጉዞ ተጀመረ።
ረሱሉ ሰለላሁ አለይሒወሰለም ውድ ግመላቸው የሆነችው ቀስዋህ ላይ ከወጡ ጀምሮ መዲና በተልቢያ ተናወጠች።
<<ለበይከላሁመ ለበይክ ለበይከ ላሸሪከ ለከ ለበይክ ኢነል ሐምዳህ ወንኒእመተህ ለከወልሙልክ ላሸሪከለክ>>
<<አላህ ሆይ! (ታዛዥ ሆኜ መጥቻለሁ) አቤት። አንተ ተጋሪ የለሕም አቤት ምስጋናና ፀጋ ያንተ ነው። ንግስናም ያንተ ነው። ተጋሪ የለህም።" ሲሉ በአንድ ድምፅ ያስተጋባሉ።
የመጀመሪያው የጉዞ ማረፊያ አል አሪጅ ሆነ። ቀጣይ አል አብዋእ፣ አስፋን፣ ዚጡዋህ በቅደም ተከተል የሰፈሩባቸው ስፍራቸው ናቸው። ዚጡዋህ ሲደርሱ ዙልሒጃህ አራተኛው ቀን ነበር። ገላቸውን ተጣጥበው በሰሜን የመካ መግቢያ ወደ ካእባ አቀኑ።
ከነብይነታቸው በፊት ወደቦታው እንዲመልሱ የተመረጡለትን ሐጀር አል አስወድን ስመው ወደ ጠዋፍ ስነስርአት አመሩ። የመጀመሪያዎቹ ሶስት ዙሮች በፍጥነት ቀጣዮቹን አራት ዙሮች ደግሞ እየተራመዱ ካእባን ዞሩ። ከዚህ በኋላ መቃሙ ኢብራሒም ላይ ቆመው የበቀራህን መቶ ሐያ አምስተኛ አያ (አንቀፅ) አነበቡ።
<<ቤቱንም ለሰዎች መመለሻና ጸጥተኛ ባደረግን ጊዜ (አስታውስ)፣ ከኢብራሂምም መቆሚያ መስገጃን አድርጉ፤ ወደ ኢብራሂምና ወደ ኢስማዒልም ቤቴን ለዘዋሪዎችና ለተቀማጮቹም ለአጎንባሾች ሰጋጆቹም አጥሩ ስንል ቃልኪዳን ያዝን፡፡” [አል-በቀራህ፡ 125]
ከዚያም ከመቃሙ ኢብራሒም ትይዩ ሑለት ረከአ ሰላትን ሰግደው ለሁለተኛ ጊዜ ሐጀር አል አስወድን ሳሙት። ሶፋና መርዋ ጋር የሔዱት ከዚህ በኋላ ነበር። ሰፋ ተራራ አጠገብ ሲደርሱ የሚቀጥለውን የቁርአን አንቀፅ አነበቡ።
<<ሰፋ እና መርዋህ ከአላህ ትእዛዝ መፈፀሚያ ምልክቶች ውስጥ ናቸው። ቤቱን (ከእባን) በሐጅ ወይም በኡምራህ ስራ የጎበኘ ሰው በሁለቱ መሀከል በመመላለሱ በርሱ ላይ ሐጢአት የለበትም። መልካምንም ስራ በፈቃደኝነት የሰራ ሰው አላህ ይመነዳዋል። አላህ አመስጋኝ አዋቂ ነውና።>>
[አል በቀራህ:158]
በሰፋና መርዋ መሐል ሰዕይ ካደረጉ በኋላ መስዋእት ያመጡ ሲቀሩ ከኢህራማቸው እንዲፈቱ አዘዙ። መስዋእት ያላመጡት ፀጉራቸውን በማሳጠር ኡምራ ብቻ እንዲያደርጉ ሲታዘዙ ቀሪዎቹ በኢህራማቸው ቆዩ። ረሱሉ ሰለላሁ አለይሒ ወሰለምና ባልደረቦቻቸው መካ ውስጥ ከእሑድ ጀምሮ አራት ቀናትን ቆይተው ሐሙስ ጠዋት ሚና ሰፈሩ። በማግስቱም ከዚህ በፊት ቁረይሾን ከሌላው ተነጥለው ከሚያርፉበት መእሸር አል ሐረምና ሙዝደሊፋ በተቃራኒ ከአረፋህ ተራራ በደቡብ በኩል ባለው ነሚራህ የተሰኘው ቦታ ላይ ቁባ የሚመስል ድንኳን አስተክለው አረፉ።
ነብያችን ሰለላሁ አለይሒ ወሰለም ፀሐይ ወደ ምእራብ ስትገሰግስ ወደ ኡረናህ ሸለቆ አመሩና ከ120 ሺህ ለሚልቀው የሐጅ ታዳሚ ኹጥባ ማድረግ ጀመሩ።
<<ሰዎች ሆይ ንግግሬን አድምጡ። ምናልባት ከዚህ አመት በኋላ በዚህ ቦታ ላይ ዳግም ላንገናኝ እንችላለን። በዚህ በሀገራችሁ በዚህ ወራችሁ የዛሬው ቀን ክቡር እንደሆነ ሁሉ ደማችሁና ሐብታችሁ የተከበረና የማይደፈር ነው። የመሐይምነት ዘመን የደም ብቀላ ውድቅ ሆኗል። መጀመሪያ ውድቅ የሚደረገው የኢብን ረቢአ ኢብን አል ሐሪስ ደም ነው። እርሱ በበኑ ሰዕድ ጎሳ ውስጥ የገባ ሲሆን በሁዘይል ጎሳ ተገድሏል። የቅድመ ኢስላም አራጣ ውድቅ ተደርጓል። መጀመሪያ ውድቅ የተደረገው የዐባስ ኢብኑ አብዱልሙጠሊብ አራጣ ነው።
★በሴቶች ጉዳይ አላህን ፍሩ። የወሰዳችኋቸው በአላህ አደራ ሲሆን ብልቶቻችሁንም ሐላል ያደረጋችሁት በአላህ ቃል ነው። እናንተ በነርሱ ላይ የምትጠሉትን ሰው በፍራሻችሁ ላይ እንዳያስቀምጡ የማድረግ መብት አላችሁ። ይህን ከጣሱ የማይጎዳ ምት ምቷቸው። እነርሱ በእናንተ ላይ ያላቸው መብት ቀለባቸውንና አልባሳታቸውን ልታቀርቡላቸው ነው።
በሚገባ ከያዛችሁት የማትጠምሙበትን ነገር ትቼላችኋለሁ። የአላህን መፅሐፍ! ስለኔ ብትጠየቁ ምን ብላችሁ ትመልሳላችሁ?>> ሲሉ ንግግራቸውን በጥያቄ አሳረጉ።
ሰሐቦችም <<መልእክቱን በሚገባ ማድረስዎትንና እኛንም ከልብ መምከርዎን እንመሰክራለን።>> አሉ። ረሱላችን አለይሒሰላምም እጃቸውን ከፍ አድርገው ወደ ህዝቦቻቸው እየተመለከቱ <<አላህ ሆይ ምስክሬ ሁን፣ አላህ ሆይ ምስክሬ ሁን፣ አላህ ሆይ ምስክሬ ሁን>> በማለት ተናገሩ።
ንግግራቸውን ሲቋጩ የሚከተለው የቁርአን አያ ወረደ። <<ዛሬ ሐይማኖታችሁን ሞላሁላችሁ።ጸጋዬንም በናንተ ላይ ፈፀምኩ። ለእናንተም ኢስላምን ከሐይማኖት በኩል ወደድኩ።>> [አል-ማኢዳህ:3]
ቢላል አዛን አድርጎ ነብያችን ሰለላሁ አለይሒ ወሰለም እና ባልደረቦቻቸው የዙህርን ሁለት ረከአ ሰላት ሰገዱ። ከዚያም ቢላል ሌላ ኢቃም አድርጎ የአስርን ሁለት ረከአ ሰገዱ። ፀሐይ ከገባች በኋላ ወደሙዝደሊፋ በማቅናት በሁለት ኢቃም የመግሪብንና የኢሻን ሰላት ሰግደው ተኙ። ከሱብሒ ስግደት በኋላ ወደ መእሸረል ሐረም ጋለቡ። ወደቂብላ ዞረው ዱአ አደረጉ። ለፀጋው አመሰገኑ።
ከዚህ በኋላ የነበረው ጀምረተል ኩብራ (የጠጠር ውርወራ) ነበር። በእያንዳንዱ ጠጠር ተክቢራ እያደረጉ ሰባቱንም ጠጠር ወረወሩ። የእርድ ስርአቱ ቀጠለ። ስልሳ ሶስቱን ረሱላችን ሰለላሁ አለይሒ ወሰለም ሲያርዱ ሰላሳ ሰባቱን ሰይዱና አሊይ ረዲየላሁ አንሁ አርደው ለሚቀርቧቸው ሰዎች አከፋፈሉ።
ጠዋፈል ኢፋዳን(የመጨረሻ ጠዋፍ) ለመፈፀም ሲሉ ወደመካ ተመለሱ። በዚያው 'ለት ወደሚና ተመልሰው ካደሩ በኋላ ማግስቱን ጀመራት ላይ ጠጠር ጣሉ። በዚህ መልኩ ለተከታታይ ሶስት የዙልሒጃ ቀናት ጠጠር እየወረወሩ ከቆዩ በኋላ ወደ መዲና ጉዞ ጀመሩ። ጁሕፋ አቅራቢያ ሲደርሱ እንዲህ ሲሉ ተናገሩ፣
<<ሰዎች ሆይ እኔ ሰው ነኝ። ምናልባትም የጌታዬ መልእክተኛ(መለከል መውት) ወደኔ ይመጣና መልስ እሰጥ ይሆናል። በመካከላችሁ ሁለት ከባድ ነገሮችን ትቻለሁ። የመጀመሪያው የአላህ መፅሀፍ ነው። ሁለተኛው ደሞ የኔ ቤተሰቦች(አህሉል በይት) ናቸው። የእኔን ቤተሰብ በተመለከተ አላህን እንድትፈሩ እጠይቃችኋለሁ።>>
የመዲና ድባብ ከሩቅ በታያቸውም ጊዜ እንዲህ አሉ። << ከአላህ በስተቀር ሌላ አምላክ የለም። ብቸኛ ነው። አጋርም የለውም። ንግስና የርሱ ነው። ምስጋና የሚገባውም ለርሱ ነው። እሱ በሁሉም ነገር ላይ ቻይ ነው። ንስሐ ገብተን ለአላህ ተገዢዎች፣ ሰጋጆችና አመስጋኞች ሆነን ተመልሰናል። አላህ ቃሉን አረጋገጠ። ባሪያውን ረዳ። ብቻውንም አህዛብን ድል ነሳ።>>
ይህ ነበር የረሱሉ ሰለላሁ አለይሒ ወሰለም የመጨረሻ ሐጅ፣ ለኡማው ፈር የቀደዱለት ከጃሒሊያ በኋላ የነበረ የመጀመሪያው ሐጅ🕋
@heppymuslim29
🔻ተክቢራ🔻
〰〰〰〰
በነዚህ አስር ቀናቶች ከሚፈፀሙ ኢባዳዎች ውስጥ አንዱ ተክቢራ ነው። ዙል ሂጃ ከገባበት ሰአት ጀምሮ እስከ ዙልሂጃ አስራ ሶስተኛው ቀን ድርስ ተክቢራ ማለት የተወደደ ተግባር ነው። ስንተኛ፣ ስንነሳ፣ ስራ ላይ ስንሆን በማንኛውም ሰአት ወንዶች ድምፃችን ከፍ ሴቶች ዝቅ በማድረግ ተክቢራ ልንል ይገባል።
الله أكبر الله أكبر لا إله إلا الله الله أكبر الله أكبر ولله الحمد
@heppymuslim29
〰〰〰〰
በነዚህ አስር ቀናቶች ከሚፈፀሙ ኢባዳዎች ውስጥ አንዱ ተክቢራ ነው። ዙል ሂጃ ከገባበት ሰአት ጀምሮ እስከ ዙልሂጃ አስራ ሶስተኛው ቀን ድርስ ተክቢራ ማለት የተወደደ ተግባር ነው። ስንተኛ፣ ስንነሳ፣ ስራ ላይ ስንሆን በማንኛውም ሰአት ወንዶች ድምፃችን ከፍ ሴቶች ዝቅ በማድረግ ተክቢራ ልንል ይገባል።
الله أكبر الله أكبر لا إله إلا الله الله أكبر الله أكبر ولله الحمد
@heppymuslim29
አባባን ሐጅ ወስደዋቸው ነው.... ሐጁ እየተከወነ ሶፋና መርዋ መካከል የሚሮጥበት ሰአት ደረሰ። እናም ሰዎች አንዲሮጡ ነገሯቸው ....« አባባ ዱብ ዱብ በሉ » አሏቸው
.... «የእስማኤል እናት ብትሮጥ ለልጇ ውሃ ፍለጋ ነው እኔ ምን ገዶኝ እሮጣለሁ» አሉ ይባላል ።
ወላጆችን ሐጅ ለማስደረግ መቋመጥ የሁሉም መልካም ልጅ ምኞት ነው።ነገር ግን ሐጅ ዒባዳህ እንጂ የቱሪዝም መዳረሻ አይደለምና ልክ እንደ ሶላት አፈፃፀሙን መማርና ማስተማር ግዴታ ነው።
ሐጅ የምታስደርጋቸው ጀነትን በመፈለግ እንጅ መካን ለማሳየት አይደለም። ረሱለላህ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦ «ኩልል ያለ ሐጅ ጀነት እንጅ ክፍያ የለውም» (ቡኻሪይ 1773)
ኩልል ያለ ሐጅ ማለት ፦
① ከወንጀል የፀዳ
② ከይዩልኝና ይስሙልኝ የፀዳ (ኻሊስ)
③ ማእዘናቱና ዋጂቦቹ የተረጋገጡበት ማለት ነው።
ከነርሱ ጋር ካዕባ ዘንድ ሰልፊ መነሳትኮ ሀጅ አይደለም! ማስደሰት ከሆነ የፈለግከው በዚያው ወጪ በሌላ ነገር ማስደሰት ይቻላል። አላህ ለኛም ለቤተሰቦቻችንም ኩልል ያለን ሐጅ ይወፍቀን!!
@heppymuslim29
.... «የእስማኤል እናት ብትሮጥ ለልጇ ውሃ ፍለጋ ነው እኔ ምን ገዶኝ እሮጣለሁ» አሉ ይባላል ።
ወላጆችን ሐጅ ለማስደረግ መቋመጥ የሁሉም መልካም ልጅ ምኞት ነው።ነገር ግን ሐጅ ዒባዳህ እንጂ የቱሪዝም መዳረሻ አይደለምና ልክ እንደ ሶላት አፈፃፀሙን መማርና ማስተማር ግዴታ ነው።
ሐጅ የምታስደርጋቸው ጀነትን በመፈለግ እንጅ መካን ለማሳየት አይደለም። ረሱለላህ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦ «ኩልል ያለ ሐጅ ጀነት እንጅ ክፍያ የለውም» (ቡኻሪይ 1773)
ኩልል ያለ ሐጅ ማለት ፦
① ከወንጀል የፀዳ
② ከይዩልኝና ይስሙልኝ የፀዳ (ኻሊስ)
③ ማእዘናቱና ዋጂቦቹ የተረጋገጡበት ማለት ነው።
ከነርሱ ጋር ካዕባ ዘንድ ሰልፊ መነሳትኮ ሀጅ አይደለም! ማስደሰት ከሆነ የፈለግከው በዚያው ወጪ በሌላ ነገር ማስደሰት ይቻላል። አላህ ለኛም ለቤተሰቦቻችንም ኩልል ያለን ሐጅ ይወፍቀን!!
@heppymuslim29
የዐረፋ ቀን ታላቁ የአላህ ቀን ነው። ኃጢኣት ይሰረዝበታል። በእለቱ ዱዓ ተቀባይነት ያገኛል። ከምንም ጊዜ በበለጠ የአላህ እዝነት ለባሮቹ ቅርብ ይሆናል።
:
የተውበት ቀን ነው። ምህረት የሚታደልበት ቀን ነው። ለአላህ የሚዋደቁበት የዱዓ ቀን ነው። የለቅሶና የተስፋ ቀን ነው።
ሰዎች በብዛት ከእሳት ነጃ የሚባሉበት፡ ኢብሊስም አንሶና አፍሮ የሚውልበት ዕለት ነው።
የአላህ መልክተኛ [ﷺ] እንዲህ ብለዋል: ‐ «የዐረፋ ቀን ጾም ያለፈውን እና የሚመጣውን ዓመት ኃጢኣት ያስምራል ብዬ አምናለሁ።»
ዙል-ሂጃ 9 ነገ ነውና ዕለቱን በፆም፣በዚክርና መልካም በተባሉ ስራዎች እናጅበው።
እኔንም በዱዓ አትርሱኝ ‼️
@heppymuslim29
:
የተውበት ቀን ነው። ምህረት የሚታደልበት ቀን ነው። ለአላህ የሚዋደቁበት የዱዓ ቀን ነው። የለቅሶና የተስፋ ቀን ነው።
ሰዎች በብዛት ከእሳት ነጃ የሚባሉበት፡ ኢብሊስም አንሶና አፍሮ የሚውልበት ዕለት ነው።
የአላህ መልክተኛ [ﷺ] እንዲህ ብለዋል: ‐ «የዐረፋ ቀን ጾም ያለፈውን እና የሚመጣውን ዓመት ኃጢኣት ያስምራል ብዬ አምናለሁ።»
ዙል-ሂጃ 9 ነገ ነውና ዕለቱን በፆም፣በዚክርና መልካም በተባሉ ስራዎች እናጅበው።
እኔንም በዱዓ አትርሱኝ ‼️
@heppymuslim29
ሳንሰለች እንደጋግማት!
اللّٰہ أڪبَر .. اللّٰہ أڪبَر .. اللّٰہ أڪبَر
لاَ إلہ إلاّ اللّٰہ
اللّٰہ أڪبَر .. اللّٰہ أڪبَر .. اللّٰہ أڪبَر
وللّٰہ الحمّد
አብዛኞቻችን በነዚህ አስሩ የዙልሂጃ ቀናቶች ተክቢራን ዘንግተናል እና ሁላችንም በነዚህ የተወደዱ ከዱንያ በላጭ በሆኑ ቀናቶች ተክቢራን እንደጋግም።
@heppymuslim29
اللّٰہ أڪبَر .. اللّٰہ أڪبَر .. اللّٰہ أڪبَر
لاَ إلہ إلاّ اللّٰہ
اللّٰہ أڪبَر .. اللّٰہ أڪبَر .. اللّٰہ أڪبَر
وللّٰہ الحمّد
አብዛኞቻችን በነዚህ አስሩ የዙልሂጃ ቀናቶች ተክቢራን ዘንግተናል እና ሁላችንም በነዚህ የተወደዱ ከዱንያ በላጭ በሆኑ ቀናቶች ተክቢራን እንደጋግም።
@heppymuslim29
የኡዱሕያ መስፈርቶች
1ኛ, ከቤት እንስሳት መሆን አለበት።
እነርሱም ፡- ግመል ከብት በግ እና ፍየል
2ኛ, በሸሪዓ ለተገደበው እድሜ መድረስ አለበት።
ግመል ከኾነ 5 ዓመት
ከብት ከኾነ 2 ዓመት
ፍየል ከኾነ 1 ዓመት
በግ ከኾነ 6 ወር የሞላው
3ኛ, ከነውር (ከዓይብ) የጠራ መሆን አለበት።
አንድ ሰው ኡዱሕያ ማረድ ከፈለግ በሚያርደው እንስሳ ላይ የተጠቀሱት ነገሮች መሟላት አለባቸው።
🛖ቅርጫ ማድረግ የፈለገ ሰው
በግ ወይም ፍየል ከኾነ ለ1 ሰው ብቻ
በሬ ወይም ግመል ከኾነ ለ7 ሰው መካፈል ይቻላል
👉 እንስሳቶችን ስናርድ ደግሞ አስተራረዳችንን ማሳመር አለብን። እነሱም ነፍስ አላቸው አይናገሩም ብሎ እነሱን ማሰቃየት ተገቢ አይደለም።
ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
﴿إِنَّ اللَّهَ كَتَبَ الْإِحْسَانَ عَلَى كُلِّ شَيْءٍ، فَإِذَا قَتَلْتُمْ فَأَحْسِنُوا الْقِتْلَةَ، وَإِذَا ذَبَحْتُمْ فَأَحْسِنُوا الذَّبْحَ، وَلْيُحِدَّ أَحَدُكُمْ شَفْرَتَهُ فَلْيُرِحْ ذَبِيحَتَهُ﴾
👉አላህ ኢኽሳንን (ማሳመርን) በሁሉም ነገሮች ላይ ፅፏል። የገደላችሁ እንደሆነ አገዳደልን አሳምሩ። አንዳችሁ ባረደ ግዜ አስተራረዱን ያሳምር ማረጃውን ይሳል። የሚታረደውንም እንስሳም ያሳርፍ። 📚 ሙስሊም ዘግበውታል: 1955
@heppymuslim29
1ኛ, ከቤት እንስሳት መሆን አለበት።
እነርሱም ፡- ግመል ከብት በግ እና ፍየል
2ኛ, በሸሪዓ ለተገደበው እድሜ መድረስ አለበት።
ግመል ከኾነ 5 ዓመት
ከብት ከኾነ 2 ዓመት
ፍየል ከኾነ 1 ዓመት
በግ ከኾነ 6 ወር የሞላው
3ኛ, ከነውር (ከዓይብ) የጠራ መሆን አለበት።
አንድ ሰው ኡዱሕያ ማረድ ከፈለግ በሚያርደው እንስሳ ላይ የተጠቀሱት ነገሮች መሟላት አለባቸው።
🛖ቅርጫ ማድረግ የፈለገ ሰው
በግ ወይም ፍየል ከኾነ ለ1 ሰው ብቻ
በሬ ወይም ግመል ከኾነ ለ7 ሰው መካፈል ይቻላል
👉 እንስሳቶችን ስናርድ ደግሞ አስተራረዳችንን ማሳመር አለብን። እነሱም ነፍስ አላቸው አይናገሩም ብሎ እነሱን ማሰቃየት ተገቢ አይደለም።
ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
﴿إِنَّ اللَّهَ كَتَبَ الْإِحْسَانَ عَلَى كُلِّ شَيْءٍ، فَإِذَا قَتَلْتُمْ فَأَحْسِنُوا الْقِتْلَةَ، وَإِذَا ذَبَحْتُمْ فَأَحْسِنُوا الذَّبْحَ، وَلْيُحِدَّ أَحَدُكُمْ شَفْرَتَهُ فَلْيُرِحْ ذَبِيحَتَهُ﴾
👉አላህ ኢኽሳንን (ማሳመርን) በሁሉም ነገሮች ላይ ፅፏል። የገደላችሁ እንደሆነ አገዳደልን አሳምሩ። አንዳችሁ ባረደ ግዜ አስተራረዱን ያሳምር ማረጃውን ይሳል። የሚታረደውንም እንስሳም ያሳርፍ። 📚 ሙስሊም ዘግበውታል: 1955
@heppymuslim29
ኢዱን ሰዒድ…… የቀናት ምርጦችን አንድ ሁለት እያልን አስረኛው ላይ አገባደድን ። የኢብራሂምን ቆራጥነት ፣ የኢስማዒልን ታዛዥነት ፣ የሀጀራን ፅናት ና ተወኩል እያወሳን ለህይወታችን ማጣፈጫ እና መመሪያ ይሆነን ዘንድ ጣርን ። የጌታዬን ቤት ካዕባ ፣ የውዱን ነብይ ትውልድ ፣ የሀይማኖት አባት የሆኑት የኢብራሂምን ሱና አላህ ያደላቸው እዝነቱን ያንቧቧላቸው በቦታው ተገኝተው የእድሜ ዘመናቸውን ህልም በእነዚህ ቀናት አሸበረቁበት ። በሚና ተራራ ላይ ፣ በሙዝደሊፋ እድረት ፣ በአረፋ ተራራ ዱዐ ፣ በታላቁ የአረፋና የጁምዐ ኹጥባ ፣ በኡድሂያ እርድ ፣ በዒድ አልአደሀ ሰላት …ለበይክ ያአላህ እያሉ ፣ ምንኛ መታደልን ታደሉ በቤትህ የከተሙ ። መካን መምጣት ባይችሉ መዲናንም ባይጎበኙ በፆም በዱዐ ፣ በአዝካሩ ነገን ተስፋ ያደረጉ ምርጥ የአላህ ባሪያዎች አለምን በዒድ ሰላት በተክቢራ ድምፅ አሳምረዋት ዋሉ ። የተራራቀ ዘመድ የተረሳሳ ወዳጅ ታላቅ ዒድ ነውና ሲዘያየር ሲተዋወስ ዋለ ። ለህፃናት መቦረቂያ ለአዋቂውም የቀልቡ መደሰቻ ነው ዒድ አልአደሃ …… የዘመናት ታሪክ ፣ የህይወት ዘመን ተምሳሌት ፣ የቤተሰብ ፅናት …… አደም(ዐ.ሰ)…… ኢብራሂም(ዐ.ሰ)…… ኢስማዒል(ዐ.ሰ)…… የሴትነት ተምሳሌት ሀጀራ…… ዉዱ ነብያችን ሙሀመድ (ሰ.ዐ.ወ)የአለማት እዝነት…… እና እኛ የአለማቱ እዝነት ዑማ የሆንን…… ሁሌም ታሪክ ያነሳናል።
ኢድ ሙባረክ
@heppymuslim29
ኢድ ሙባረክ
@heppymuslim29
"በሕይወታችን የሚጎዱን ከባድ ነገሮች ምን ይመስሉሻል?" በጫወታችን መሀከል ድንገት ከጓደኛዬ የመጣ ጥያቄ ነበር
"እንደዚህ አይነት ድንገተኛ ጥያቄ" አልኳት.. ፈገግ አለችና "አልቀለድኩም አንቺ ደሞ" አለችኝ.. "እምም እሺ ቆይ" ብያት ትንሽ አወጣው አወረድኩና እንዲህ አልኳት..
"በሕይወታችን የሚጎዱን ከባዶቹ ነገር የራሳችን ጉጉት Expectation እና የፍላጎታችን መብዛት ይመስለኛል" አልኳት። ማብራርያ የፈለገች ትመስላለች በተመስጦ እያየችኝ "like how?"አለችኝ
"እንዴት መሰለሽ For example አንድን ሰው እንደማታገኝው እያወቅሽ.." ስላት ሳታስጨርሰኝ "Oww የሞተን ሰው ምናምን ነው እንዴ" አለችኝ
"No No የሰውን ልጅ የማታገኝው ስለሞተ ብቻ ነው እንዴ ?Ofc አይደለም አጠገብሽ ሆኖ ሀሳቡ ልቡ ሌላ ጋር የሆነን ሰው መናፈቅ ፣በራሱ የዓለም ባህር ውስጥ የሰመጠን ሰው መናፈቅ ፣መቼም እንደማትገናኙ የምታቂውን ሰው መናፈቅ አየሽ እንደዚህ አይነት ሰዎችን አብረሻቸው ለመሆን እነሱን ያንቺ ዓለም ውስጥ ለማስገባት መጓጓት የሕይወትሽ ከባዱ ነገር ነው።መጓጓት መጥፎ ነው ከጓጓሽ ትጠብቂያለሽ ጠብቀሽ ካላገኘሽ ደሞ ውስጥሽ፣ቅስምሽ ላይጠገን ይሰበራል ድብርት ውስጥ ትዘፈቂያለሽ ሕይወት ማታጓጓው ስልቹ እና careless ሰው ትሆኛለሽ እንደዚ ከሆንሽ ደሞ ምንም motive የሌለው ሰነፍ ሰው ትሆኛለሽ..። በግርምት እያየችኝ "እንዴት እንዴት አድርገሽ አገናኘሽው አንቺ" ብላ ሳቀች።
እንዴት እንዳገናኘሁት እኔም አልገባኝም ግን ይሄ የሁላችንም ትክክለኛ ስሜት መሰለኝ ዝም ብያት ፈገግ አልኩኝ "So መፍትሄውስ አለችኝ" "መፍትሄውማ ከባድ ነው ይሄን ያነሳውልሽ ለምሳሌ ያክል ነው የሰው ልጅ ስትሆኚ በሆነ means የሆነ ነገር ላይ መጠበቅሽ መጓጓትሽ አይቀርም ግን መፍትሔው ለፍላጎትሽ ገደብ መስጠት እና ለበጎ ነው የሚለውን ብሂል አለመረሳት እና ለበጎ መሆኑን አምኖ እንዲቀበል ራስሽ ላይ መስራት ነው" አልኳት። አተኩራ አየችኝ እና ማክያቶዋን በአንድ ትንፋሽ ጭልጥ አደረገችው እና "አዋ ለበጎ ነው" ብላ በውስጧ እያጉረመረመች ፈገግ አለች ባትነግረኝም ለጥያቄዋ መልስ እንዳገኘች ከface expressionዋ ተረዳውና እኔም ሁፈይይ አልኩ።
@heppymuslim29
"እንደዚህ አይነት ድንገተኛ ጥያቄ" አልኳት.. ፈገግ አለችና "አልቀለድኩም አንቺ ደሞ" አለችኝ.. "እምም እሺ ቆይ" ብያት ትንሽ አወጣው አወረድኩና እንዲህ አልኳት..
"በሕይወታችን የሚጎዱን ከባዶቹ ነገር የራሳችን ጉጉት Expectation እና የፍላጎታችን መብዛት ይመስለኛል" አልኳት። ማብራርያ የፈለገች ትመስላለች በተመስጦ እያየችኝ "like how?"አለችኝ
"እንዴት መሰለሽ For example አንድን ሰው እንደማታገኝው እያወቅሽ.." ስላት ሳታስጨርሰኝ "Oww የሞተን ሰው ምናምን ነው እንዴ" አለችኝ
"No No የሰውን ልጅ የማታገኝው ስለሞተ ብቻ ነው እንዴ ?Ofc አይደለም አጠገብሽ ሆኖ ሀሳቡ ልቡ ሌላ ጋር የሆነን ሰው መናፈቅ ፣በራሱ የዓለም ባህር ውስጥ የሰመጠን ሰው መናፈቅ ፣መቼም እንደማትገናኙ የምታቂውን ሰው መናፈቅ አየሽ እንደዚህ አይነት ሰዎችን አብረሻቸው ለመሆን እነሱን ያንቺ ዓለም ውስጥ ለማስገባት መጓጓት የሕይወትሽ ከባዱ ነገር ነው።መጓጓት መጥፎ ነው ከጓጓሽ ትጠብቂያለሽ ጠብቀሽ ካላገኘሽ ደሞ ውስጥሽ፣ቅስምሽ ላይጠገን ይሰበራል ድብርት ውስጥ ትዘፈቂያለሽ ሕይወት ማታጓጓው ስልቹ እና careless ሰው ትሆኛለሽ እንደዚ ከሆንሽ ደሞ ምንም motive የሌለው ሰነፍ ሰው ትሆኛለሽ..። በግርምት እያየችኝ "እንዴት እንዴት አድርገሽ አገናኘሽው አንቺ" ብላ ሳቀች።
እንዴት እንዳገናኘሁት እኔም አልገባኝም ግን ይሄ የሁላችንም ትክክለኛ ስሜት መሰለኝ ዝም ብያት ፈገግ አልኩኝ "So መፍትሄውስ አለችኝ" "መፍትሄውማ ከባድ ነው ይሄን ያነሳውልሽ ለምሳሌ ያክል ነው የሰው ልጅ ስትሆኚ በሆነ means የሆነ ነገር ላይ መጠበቅሽ መጓጓትሽ አይቀርም ግን መፍትሔው ለፍላጎትሽ ገደብ መስጠት እና ለበጎ ነው የሚለውን ብሂል አለመረሳት እና ለበጎ መሆኑን አምኖ እንዲቀበል ራስሽ ላይ መስራት ነው" አልኳት። አተኩራ አየችኝ እና ማክያቶዋን በአንድ ትንፋሽ ጭልጥ አደረገችው እና "አዋ ለበጎ ነው" ብላ በውስጧ እያጉረመረመች ፈገግ አለች ባትነግረኝም ለጥያቄዋ መልስ እንዳገኘች ከface expressionዋ ተረዳውና እኔም ሁፈይይ አልኩ።
@heppymuslim29
"ስልችት ብሎኛል!"
"ምኑ?"
"የሚመረጥ የለውም... መኖር አሰልችቶኛል?"
"ጓዝ አበዛሽ እንዴ?"
"የምን ጓዝ?"
"ተጥሎ መረሳት የነበረበትን ያለፈ ታሪክ ዛሬም ያለ እና የሚኖር እስኪመስልሽ ተሸክመሻል?"
"እንዴ? ... ወዴት ይጣላል? የኔ እኮ ነው። የኖርኩት። ማንነቴ የተገነባበት ነው። ወደ የት ነው የምጥለው? አያስፈልገኝም ልጣለው ብልስ ግማሽ አያስቀረኝም?"
"ወጣት ነሽ አይደል? ህፃን እያለሽ የነበሩሽን የምትወጃቸውን እና በምርጫሽ የተገዙልሽ የነበሩ የምትምነሰነሽባቸው ልብሶችሽን ፤ ያለ ምርጫሽ የተገዙልሽ የነበሩ የለበስሻቸውን ሁሉ አሁንም ትለብሻቸዋለሽ?"
"አይሆኑኝም እኮ ልኬ አይደሉም እንዴት እለብሳቸዋለሁ? በየጊዜው እየተካካሁ አስወግጃቸዋለሁ"
"ያለፈ ታሪክም እኮ እንደዛ ነው ለዛሬው አንቺነትሽ ያዋጣው ነገር ይኖራል እንጂ ለዛሬው አንቺነትሽ ግን ላይበቃሽ ይችላል። ልክ እንደልብሶችሽ በጊዜ ሂደት ወደሚሆንሽ እየተቀየረ በአዲስ መተካት ይኖርበታል!"
"የማይጠቅመኝን ያለፈ ነገር ማስወገድ ከመሰላቸት የሚያድነኝ ከሆነ በደስታ አደርገዋለሁ! ቀላል ይመስልሻል ግን?"
"ለአመታት በወጉ ያልተያዘን ቤት በደቂቃዎች ውስጥ ማሳመር ቀላል ነው?"
"እንዴት ቀላል ይሆናል?"
" ይሄም ቀላል አይደለም። ለመሞከር መነሳት ግን በግማሽ መንገዱን ይጠርገዋል!"
"በጉጉት መኖር ምን እንደሚመስል ማወቅ እና መኖር እፈልጋለሁ።"
"እንዲሆንልሽ ምኞቴ ነው።"
@heppymuslim29
"ምኑ?"
"የሚመረጥ የለውም... መኖር አሰልችቶኛል?"
"ጓዝ አበዛሽ እንዴ?"
"የምን ጓዝ?"
"ተጥሎ መረሳት የነበረበትን ያለፈ ታሪክ ዛሬም ያለ እና የሚኖር እስኪመስልሽ ተሸክመሻል?"
"እንዴ? ... ወዴት ይጣላል? የኔ እኮ ነው። የኖርኩት። ማንነቴ የተገነባበት ነው። ወደ የት ነው የምጥለው? አያስፈልገኝም ልጣለው ብልስ ግማሽ አያስቀረኝም?"
"ወጣት ነሽ አይደል? ህፃን እያለሽ የነበሩሽን የምትወጃቸውን እና በምርጫሽ የተገዙልሽ የነበሩ የምትምነሰነሽባቸው ልብሶችሽን ፤ ያለ ምርጫሽ የተገዙልሽ የነበሩ የለበስሻቸውን ሁሉ አሁንም ትለብሻቸዋለሽ?"
"አይሆኑኝም እኮ ልኬ አይደሉም እንዴት እለብሳቸዋለሁ? በየጊዜው እየተካካሁ አስወግጃቸዋለሁ"
"ያለፈ ታሪክም እኮ እንደዛ ነው ለዛሬው አንቺነትሽ ያዋጣው ነገር ይኖራል እንጂ ለዛሬው አንቺነትሽ ግን ላይበቃሽ ይችላል። ልክ እንደልብሶችሽ በጊዜ ሂደት ወደሚሆንሽ እየተቀየረ በአዲስ መተካት ይኖርበታል!"
"የማይጠቅመኝን ያለፈ ነገር ማስወገድ ከመሰላቸት የሚያድነኝ ከሆነ በደስታ አደርገዋለሁ! ቀላል ይመስልሻል ግን?"
"ለአመታት በወጉ ያልተያዘን ቤት በደቂቃዎች ውስጥ ማሳመር ቀላል ነው?"
"እንዴት ቀላል ይሆናል?"
" ይሄም ቀላል አይደለም። ለመሞከር መነሳት ግን በግማሽ መንገዱን ይጠርገዋል!"
"በጉጉት መኖር ምን እንደሚመስል ማወቅ እና መኖር እፈልጋለሁ።"
"እንዲሆንልሽ ምኞቴ ነው።"
@heppymuslim29
ዐሹራ (عاشوراء)
.
➊አሹራ ሚባለው ምን ቀን ነው?
.
➪አብዛኛዎቹ ኡለሞች ባሉበት አቋም መሰረት አሹራ የሚባለው ከሙሀረም አስረኛው ቀን ነው። አሹራም የተባለበት ምክንያት አስረኛው ቀን ለማለት ተፈልጎበት ነው።ልክ እንደዚሁ ዘጠናኛው ቀን ታሱአ ይባላል።
.
➦አንዳንድኡለሞች የሙሀረምን ዘጠነኛው ቀን ነው አሹራ ሚባለው ቢሉም ከቋንቋ አንፃር እንኳን ስናየው ትክክል አለመሆኑን እንረዳለን።
.🏷የዘንድሮ የዐሹራ ቀን (ሙሐረም10) ቅዳሜ ሰኔ 28 /2017 ላይ ይውላል። አሏህ በሰላም ያድርሰን
.
❷አሹራ ሚፆመው ለምንድነው?
.
➪የአሹራ ቀን የሚፆምበት ዋነኛ ምክንያት አላህ ሙሳን እና በኒ ኢስራኢሎችን ከፊርአው ነፃ ያወጣበት ቀን ስለሆነ ነው።
.
▩ማስረጃው
ኢብንአባስ እንዲህ ይላል
((የአላህ መልእክተኛ ﷺ መዲና ሲገቡ አይሁዶች የአሹራን ቀን ሲፆሙ አዯቸውና
"ይህ ምንድነው?"ብለው ጠየቋቸው ከዛም የሁዶች ሲመልሱ
" ይህ ደግ ቀን ነው አላህ በኒ ኢስራኢሎችን ከጠላታቸው ነፃ ያወጣበት ቀን ነው። ሙሳ ለምስጋና ፆሞታል" አሉ
የአላህ መልእክተኛም ﷺ "እኔ በሙሳ ከናንተ ይበልጥ ተገቢ ነኝ" አሉና ፆሙት በመፆምም አዘዙ
❸የአላህ መልእክተኛ ﷺ ፆመውታል?
➩አዎ የአላህ መልእክተኛ ﷺ የአሹራ ፆምን ይፆሙት ነበር
.
▩ማስረጃው
አኢሻ እንዲህ ትላለች
(የአሹራቀን ቁረይሾች በጃሂሊያ ግዜ ይፆሙት ነበር የአላህ መልእክተኛም ﷺ ይፆሙት ነበር...)
📚ቡኻሪናሙስሊም ዘግበውታል
.
❹ከሙስሊሞች ውጪ ይህን ቀን ሚፆሙት አሉ?
.
➪አዎ ከሙስሊሞች ውጪም ይህን ቀን ሚፆሙት ነበሩ እነሱም
.
➀ሙሽሪኮች ፦ማስረጃው ከላይ በተራ ቁጥር ❸ ላይ ያሳለፍነው የአኢሻ ሀዲስ ነው
.
➁አይሁዶች ፦ማስረጃው ከላይ በተራ ቁጥር ❷ ላይ ያሳለፍነው የኢብን አባስ ሀዲስ ነው
❺ ግዴታ ነው ወይስ ሱና?
.
➪ረመዳን ከመደንገጉ በፊት የአሹራ ፆም ሙስሊሞች ላይ በግዴታነት መልኩ ተደንግጎ እንደነበር የሚጠቁሙ ሀደሶች አሉ ከነዛህ መሀከል ኢማም ቡኻሪ የዘገቡት የሰለማ ቢን አውከአ ሀዲስ አንዱ ነው። በዛ ሀዲስ ላይ መልእክተኛው ﷺ ሳያቅ ጠዋቱን የበላ ሰው የተቀረውን የቀን ክፍለ ግዜ እንዲፆም አዘዋል።
.
➪ይህ የግዴታነት ትእዛዝ ግን በሗላ ላይ ተሽሮ በበርካታ ሀዲሶች ላይ እንደመጣው የአላህ መልእክተኛ ﷺ የፈለገ ሰው ይፁም ብለው ተናግረዋል።
.
▩በመሆኑም የአሹራ ፆም የጠነከረ ሱና እንጂ ግዴታ አደለም።
.
❻አስረኛው ቀን ብቻ ነው ሚፆመው?
.
➪የአሹራን ቀን ብቻውን ነጥሎ ከመፆም ይልቅ ከሱ በፊት አንድን ቀን አስቀድሞ ፆሞ የአሹራንም ቀን አንድ ላይ መፆሙ የተወደደ ነው።
.
➦ይህ ማለት ዘጠነኛውንና አስረኛውን ቀን ማለት ነው።
.
➦ወይ ደግሞ አስራ አንደኛውንም ቀን አስከትሎ መፆሙ ይወደዳል።
.
▩ማስረጃውም
.
አብደላህኢብን አባስ ባወራው ሀዲስ የአላህ መልእክተኛ እንዲህ ብለዋል
"አላህ ካለ የሚመጣው አመት ዘጠነኛውን ቀን እንፆማለን"
ነገር ግን የሚቀጥለው አመት ሳይመጣ መልእክተኛው ሞቱ
📚 ሙስሊም ዘግቦታል
.
▤አንድ ቀን አስቀድሞ ወይም ደግሞ አንድ ቀን አስከትሎ መፆሙ የተደነገገበት ምክንያትን ኡለሞች ሲያብራሩ ብዙ የሚጠቅሷቸው ነገሮች ቢኖሩም በዋነኝነት ግን ከአህለል ኪታቦች ለመለየት ሲባል የሚለው ይበልጥ ሚዛን ይደፍል።ምክንያቱም የአላህ መልእክተኛ ሚቀጥለው አመት ብደርስ ዘጠነኛውን ቀን ጨምሬ እፆማለው ያሉት አስረኛውን ቀን አህለል ኪታቦች እንደሚያልቁት ሲነገራቸው ነው።
.
➪አንዳንድ ኡለሞች አስረኛውን ቀን ብቻ ነጥሎ መፆሙ የተጠላ እንደሆነ ይገልፃሉ።
.
➦ነገር ግን ሸይኹል ኢስላም ዘጠነኛውን ወይም አስራ አንደኛውም መፆም ላልቻለ ሰው አስረኛውን ብቻ ቢፆምም እንደማይጠላ ይገልፃል። የሚችል ሰው ግን አስረኛውን ብቻ መነጠሉ ተገቢ እንዳልሆነ ይጠቅሳል።
.
❼የሚወደደው አፇፇም
.
➪የሚወደደው አፇፇም በቅደም ተከተል ሲቀመጥ
.
⓵ዘጠነኛውን አስረኛውንና አስራ አንደኛውን ቀን ሶስቱን በተከታታይ መፆም (3ቀኖች)
.
⓶ዘጠነኛውንና አስረኛውን መፆም (2ቀኖች)
.
⓷አስረኛውን ቀን ብቻ መፆም (1ቀን)
.
📚ይህንንቅደም ተከተል ኢብኑል ቀይም ዛደል መአድ ላይ እንዲሁም ኢብን ሀጀር ፈትሀል ባሪ ላይ መርጠውታል። ኢብን ተይሚያም ኢቅቲዳ ኪታቡ ላይ ከኢማም አህመድ የዚህን አምሳያ ጠቅሷል።
.
➦በርግጥ ሌሎች ኡለሞች የመረጣቸው ሌሎች ቅደም ተከተሎች ቢኖሩም ከመጡ ሀዲሶች አንፃር ከላይ የጠቀስነው ቅደም ተከተል ይበልጥ አመዛኙ አቋም ነው።
.
❽የአሹራ ፆም ያለው ትሩፍት
.
➪ ኢማሙ ነሳኢ በዘገቡት ሀዲስ የአላህ መልእክተኛ የአሹራ ፆም ያለፈውን አመት ወንጀል ያስምራል ብለዋል።
.
✍🏾ኻሊድ ሙሀመድ (አቡሱለይማን)
@heppymuslim29
.
➊አሹራ ሚባለው ምን ቀን ነው?
.
➪አብዛኛዎቹ ኡለሞች ባሉበት አቋም መሰረት አሹራ የሚባለው ከሙሀረም አስረኛው ቀን ነው። አሹራም የተባለበት ምክንያት አስረኛው ቀን ለማለት ተፈልጎበት ነው።ልክ እንደዚሁ ዘጠናኛው ቀን ታሱአ ይባላል።
.
➦አንዳንድኡለሞች የሙሀረምን ዘጠነኛው ቀን ነው አሹራ ሚባለው ቢሉም ከቋንቋ አንፃር እንኳን ስናየው ትክክል አለመሆኑን እንረዳለን።
.🏷የዘንድሮ የዐሹራ ቀን (ሙሐረም10) ቅዳሜ ሰኔ 28 /2017 ላይ ይውላል። አሏህ በሰላም ያድርሰን
.
❷አሹራ ሚፆመው ለምንድነው?
.
➪የአሹራ ቀን የሚፆምበት ዋነኛ ምክንያት አላህ ሙሳን እና በኒ ኢስራኢሎችን ከፊርአው ነፃ ያወጣበት ቀን ስለሆነ ነው።
.
▩ማስረጃው
ኢብንአባስ እንዲህ ይላል
((የአላህ መልእክተኛ ﷺ መዲና ሲገቡ አይሁዶች የአሹራን ቀን ሲፆሙ አዯቸውና
"ይህ ምንድነው?"ብለው ጠየቋቸው ከዛም የሁዶች ሲመልሱ
" ይህ ደግ ቀን ነው አላህ በኒ ኢስራኢሎችን ከጠላታቸው ነፃ ያወጣበት ቀን ነው። ሙሳ ለምስጋና ፆሞታል" አሉ
የአላህ መልእክተኛም ﷺ "እኔ በሙሳ ከናንተ ይበልጥ ተገቢ ነኝ" አሉና ፆሙት በመፆምም አዘዙ
❸የአላህ መልእክተኛ ﷺ ፆመውታል?
➩አዎ የአላህ መልእክተኛ ﷺ የአሹራ ፆምን ይፆሙት ነበር
.
▩ማስረጃው
አኢሻ እንዲህ ትላለች
(የአሹራቀን ቁረይሾች በጃሂሊያ ግዜ ይፆሙት ነበር የአላህ መልእክተኛም ﷺ ይፆሙት ነበር...)
📚ቡኻሪናሙስሊም ዘግበውታል
.
❹ከሙስሊሞች ውጪ ይህን ቀን ሚፆሙት አሉ?
.
➪አዎ ከሙስሊሞች ውጪም ይህን ቀን ሚፆሙት ነበሩ እነሱም
.
➀ሙሽሪኮች ፦ማስረጃው ከላይ በተራ ቁጥር ❸ ላይ ያሳለፍነው የአኢሻ ሀዲስ ነው
.
➁አይሁዶች ፦ማስረጃው ከላይ በተራ ቁጥር ❷ ላይ ያሳለፍነው የኢብን አባስ ሀዲስ ነው
❺ ግዴታ ነው ወይስ ሱና?
.
➪ረመዳን ከመደንገጉ በፊት የአሹራ ፆም ሙስሊሞች ላይ በግዴታነት መልኩ ተደንግጎ እንደነበር የሚጠቁሙ ሀደሶች አሉ ከነዛህ መሀከል ኢማም ቡኻሪ የዘገቡት የሰለማ ቢን አውከአ ሀዲስ አንዱ ነው። በዛ ሀዲስ ላይ መልእክተኛው ﷺ ሳያቅ ጠዋቱን የበላ ሰው የተቀረውን የቀን ክፍለ ግዜ እንዲፆም አዘዋል።
.
➪ይህ የግዴታነት ትእዛዝ ግን በሗላ ላይ ተሽሮ በበርካታ ሀዲሶች ላይ እንደመጣው የአላህ መልእክተኛ ﷺ የፈለገ ሰው ይፁም ብለው ተናግረዋል።
.
▩በመሆኑም የአሹራ ፆም የጠነከረ ሱና እንጂ ግዴታ አደለም።
.
❻አስረኛው ቀን ብቻ ነው ሚፆመው?
.
➪የአሹራን ቀን ብቻውን ነጥሎ ከመፆም ይልቅ ከሱ በፊት አንድን ቀን አስቀድሞ ፆሞ የአሹራንም ቀን አንድ ላይ መፆሙ የተወደደ ነው።
.
➦ይህ ማለት ዘጠነኛውንና አስረኛውን ቀን ማለት ነው።
.
➦ወይ ደግሞ አስራ አንደኛውንም ቀን አስከትሎ መፆሙ ይወደዳል።
.
▩ማስረጃውም
.
አብደላህኢብን አባስ ባወራው ሀዲስ የአላህ መልእክተኛ እንዲህ ብለዋል
"አላህ ካለ የሚመጣው አመት ዘጠነኛውን ቀን እንፆማለን"
ነገር ግን የሚቀጥለው አመት ሳይመጣ መልእክተኛው ሞቱ
📚 ሙስሊም ዘግቦታል
.
▤አንድ ቀን አስቀድሞ ወይም ደግሞ አንድ ቀን አስከትሎ መፆሙ የተደነገገበት ምክንያትን ኡለሞች ሲያብራሩ ብዙ የሚጠቅሷቸው ነገሮች ቢኖሩም በዋነኝነት ግን ከአህለል ኪታቦች ለመለየት ሲባል የሚለው ይበልጥ ሚዛን ይደፍል።ምክንያቱም የአላህ መልእክተኛ ሚቀጥለው አመት ብደርስ ዘጠነኛውን ቀን ጨምሬ እፆማለው ያሉት አስረኛውን ቀን አህለል ኪታቦች እንደሚያልቁት ሲነገራቸው ነው።
.
➪አንዳንድ ኡለሞች አስረኛውን ቀን ብቻ ነጥሎ መፆሙ የተጠላ እንደሆነ ይገልፃሉ።
.
➦ነገር ግን ሸይኹል ኢስላም ዘጠነኛውን ወይም አስራ አንደኛውም መፆም ላልቻለ ሰው አስረኛውን ብቻ ቢፆምም እንደማይጠላ ይገልፃል። የሚችል ሰው ግን አስረኛውን ብቻ መነጠሉ ተገቢ እንዳልሆነ ይጠቅሳል።
.
❼የሚወደደው አፇፇም
.
➪የሚወደደው አፇፇም በቅደም ተከተል ሲቀመጥ
.
⓵ዘጠነኛውን አስረኛውንና አስራ አንደኛውን ቀን ሶስቱን በተከታታይ መፆም (3ቀኖች)
.
⓶ዘጠነኛውንና አስረኛውን መፆም (2ቀኖች)
.
⓷አስረኛውን ቀን ብቻ መፆም (1ቀን)
.
📚ይህንንቅደም ተከተል ኢብኑል ቀይም ዛደል መአድ ላይ እንዲሁም ኢብን ሀጀር ፈትሀል ባሪ ላይ መርጠውታል። ኢብን ተይሚያም ኢቅቲዳ ኪታቡ ላይ ከኢማም አህመድ የዚህን አምሳያ ጠቅሷል።
.
➦በርግጥ ሌሎች ኡለሞች የመረጣቸው ሌሎች ቅደም ተከተሎች ቢኖሩም ከመጡ ሀዲሶች አንፃር ከላይ የጠቀስነው ቅደም ተከተል ይበልጥ አመዛኙ አቋም ነው።
.
❽የአሹራ ፆም ያለው ትሩፍት
.
➪ ኢማሙ ነሳኢ በዘገቡት ሀዲስ የአላህ መልእክተኛ የአሹራ ፆም ያለፈውን አመት ወንጀል ያስምራል ብለዋል።
.
✍🏾ኻሊድ ሙሀመድ (አቡሱለይማን)
@heppymuslim29
Forwarded from 𝑰𝑺𝑳𝑨𝑴𝑰𝑪 𝑭𝑶𝑹𝑼𝑴
✅ቁርኣን ላለመቅራታችን ምንም ምክንያት የለንም‼️
በዱንያ ላይ እያለን ሌሎች ነገሮችን
ማንበብ ችለን የአላህ ቃል(ቁርኣንን)
ጊዜ ሰጥተን ባለመማራችን እና
ባለመቅራታችን አላህ ዘንድ ምክንያታችን ምን ይሆን⁉️
🎙🎙 ታላቅ ብስራት ለቁርአን እውቀት ፈላጊዎች በሙሉ !!
¶📖 አል-ነጃሺ ኦንላይን የቁርአን ንባብ ማዕከል ⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻
በስራ ፣ በጊዜ ፣ በቦታ ምክንያት ቁርኣን አለመቅራትዎ አሳስቦታል?
ጊዜና ቦታ ሳይገድብዎ ባሉበት ሆነው በሚመችዎ ሰዓት ኦንላይን ማስቀራት ጀምረናል።
አል-ነጃሺ የቁርኣን ማዕከል
ዘመኑ ባፈራቸው ቴክኖሎጂዎች በመታገዝ ልምድ ባላቸው የቁርኣን ሃፊዞች
ቁርአንን ባሉበት ቦታ ሆነው በተመቾት ሰአት የእጅ ስልኮን ብቻ በመጠቀም ይማሩ። በየትኛውም የእድሜ እና የቂርአት ደረጃ ላይ ቢሆኑም ይስተናገዳሉ።
⚡️ ቃኢደቱ ኑራኒያ ለጀማሪዎች
⚡️ ነዘር ከመሰረታዊ ተጅዊድ ጋር
⚡️ የተሟላ የተጅዊድ ትምህርት
⚡️ የቁርዐን ሂፍዝ ከሙራጀዐ ጋር።
𒊹︎︎︎ የቁርዐን ትምህርት አሰጣጥ ሁኔታ
አንድ ተማሪ ከተመዘገበ በኋላ የተመደበለት ኡስታዝጋ
☞︎︎︎ በዙም አፕልኬሽን
☞︎︎︎ በቴሌ ግራም
☞︎︎︎ በዋትስ አፕ
☞︎︎︎ በኢሞ እንዲሁም
☞︎︎︎ በተጨማሪ መንገዶች የሚሰጥ ይሆናል።
𒊹︎︎︎ የቁርአን ቂረአት የሚሰጥበት ጊዜ
☞︎︎︎ በሳምንት 5 ቀን
☞︎︎︎ በሳምንት 3 ቀን
☞︎︎︎ በቀን ለ 30 ደቂቃ ለአንድ ተማሪ
☞︎︎︎ ተማሪው በሚመቸው ሰአት
ልብ ይበሉ ማዕከላችን በአላህ ፍቃድ በአጭር ግዜ ብቻ ቁርኣንን ማንበብ እንዲችሉ ያደርጋል
📋 ለመመዝገብ እነዚህን መንገዶች ይጠቀሙ
☞︎︎︎ @Besam21
በዱንያ ላይ እያለን ሌሎች ነገሮችን
ማንበብ ችለን የአላህ ቃል(ቁርኣንን)
ጊዜ ሰጥተን ባለመማራችን እና
ባለመቅራታችን አላህ ዘንድ ምክንያታችን ምን ይሆን⁉️
🎙🎙 ታላቅ ብስራት ለቁርአን እውቀት ፈላጊዎች በሙሉ !!
¶📖 አል-ነጃሺ ኦንላይን የቁርአን ንባብ ማዕከል ⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻
በስራ ፣ በጊዜ ፣ በቦታ ምክንያት ቁርኣን አለመቅራትዎ አሳስቦታል?
ጊዜና ቦታ ሳይገድብዎ ባሉበት ሆነው በሚመችዎ ሰዓት ኦንላይን ማስቀራት ጀምረናል።
አል-ነጃሺ የቁርኣን ማዕከል
ዘመኑ ባፈራቸው ቴክኖሎጂዎች በመታገዝ ልምድ ባላቸው የቁርኣን ሃፊዞች
ቁርአንን ባሉበት ቦታ ሆነው በተመቾት ሰአት የእጅ ስልኮን ብቻ በመጠቀም ይማሩ። በየትኛውም የእድሜ እና የቂርአት ደረጃ ላይ ቢሆኑም ይስተናገዳሉ።
⚡️ ቃኢደቱ ኑራኒያ ለጀማሪዎች
⚡️ ነዘር ከመሰረታዊ ተጅዊድ ጋር
⚡️ የተሟላ የተጅዊድ ትምህርት
⚡️ የቁርዐን ሂፍዝ ከሙራጀዐ ጋር።
𒊹︎︎︎ የቁርዐን ትምህርት አሰጣጥ ሁኔታ
አንድ ተማሪ ከተመዘገበ በኋላ የተመደበለት ኡስታዝጋ
☞︎︎︎ በዙም አፕልኬሽን
☞︎︎︎ በቴሌ ግራም
☞︎︎︎ በዋትስ አፕ
☞︎︎︎ በኢሞ እንዲሁም
☞︎︎︎ በተጨማሪ መንገዶች የሚሰጥ ይሆናል።
𒊹︎︎︎ የቁርአን ቂረአት የሚሰጥበት ጊዜ
☞︎︎︎ በሳምንት 5 ቀን
☞︎︎︎ በሳምንት 3 ቀን
☞︎︎︎ በቀን ለ 30 ደቂቃ ለአንድ ተማሪ
☞︎︎︎ ተማሪው በሚመቸው ሰአት
ልብ ይበሉ ማዕከላችን በአላህ ፍቃድ በአጭር ግዜ ብቻ ቁርኣንን ማንበብ እንዲችሉ ያደርጋል
📋 ለመመዝገብ እነዚህን መንገዶች ይጠቀሙ
☞︎︎︎ @Besam21
HTML Embed Code: