TG Telegram Group Link
Channel: ጥያቄኽ ምንድነው ሳትሄድ ፈልገው
Back to Bottom
🗓Prosopon የሚለው ቃል በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ለምን ውሏል
📜 "በክርስቶስ ያለው እኔ ባይነት የመለኮት ነው" ወይም "ሥጋው እኔነት የለውም፤ ግን የመለኮትን እኔነት የራሱ አድርጎ እኔ ባይ ተባለ እንጅ የሥጋ እኔነት ገንዘቡ አልሆነም ከተባለ " የአብርዮስ ምንፍቅና ነው የሚሆነው አብርዮስ ክርስቶስ ነፍስና ልብ የለውም መለኮቱም በነፍስና በልብ ፈንታ ሆነው ይል ነበርና ። ክርስቶስ የሰውነቱ እኔ ባይነት ከሌለ ምክንያታዊ ነፍስንም አልነሳም ማለት ነው ስለዚህ ክርስቶስ ፍጹም ሰው ፍጹም አምላክ መባሉ ቀርቶ ፍጹም በድን ፍጹም አምላክ ነው ሊባል ነው የሚገባው ማለት ነው ምክንያቱም እኔ ባይነት የሌለው ሰው የለምና እኔ ባይነት የሌለው ሥጋ ደግሞ በድን ነው። እኔ ባይነት የሌለው ፍጹም ሰውም የለም ። በቤተ ክርስቲያን አባቶች ታሪክም እንድህ ብሎ ያስተማረ አንድስ እንኳን የለም አለ የሚል ካለ ግን አምጥታችሁ አሳዩን
Semagn Derese
IT & Application Development Professional | Programming Instructor
🚀 Seeking Opportunities to Train and Inspire Future Developers 🚀
Are you ready to take your programming skills to the next level? Look no further! I offer comprehensive programming courses designed to equip you with the knowledge and expertise needed to thrive in the IT industry.
Why Choose My Programming Courses?
🔹 Expert-Led Training: Learn from an experienced professional with a proven track record in IT and application development. Benefit from real-world insights and practical knowledge.
🔹 Comprehensive Curriculum: Master a wide range of programming languages and frameworks, including Python, Java, JavaScript, C#, and more. From fundamentals to advanced concepts, I've got you covered.
🔹 Hands-On Approach: Apply your skills to real-world projects and sharpen your problem-solving abilities. Build a professional portfolio that showcases your talent and sets you apart from the competition.
🔹 Flexible Learning Options: I understand the importance of flexibility in your busy schedule. Choose from in-person or online classes, allowing you to learn at your own pace and convenience.
🔹 Supportive Learning Community: Join a vibrant community of like-minded individuals passionate about programming. Engage in discussions, collaborate on projects, and expand your professional network.
Are you ready to embark on an exciting journey of learning and growth? Let's connect and discuss how my programming courses can help you achieve your career goals. Together, we'll unlock your full potential and open doors to exciting opportunities in the world of IT.
📩 Message me or visit my LinkedIn profile[https://www.linkedin.com/in/semagn-derese-34a88b140/] to learn more about the courses and how to enroll. Let's shape the future of technology together!
ጥያቄኽ ምንድነው ሳትሄድ ፈልገው
Semagn Derese IT & Application Development Professional | Programming Instructor 🚀 Seeking Opportunities to Train and Inspire Future Developers 🚀 Are you ready to take your programming skills to the next level? Look no further! I offer comprehensive programming…
ፕሮጀክቶች ምናምን ማሠራት የምትፈልጉ ካላችሁ አዋሩኝ ድርጅት ያላችሁም ለድርጅታችሁ ወብሳይት ውይም ሞባል አፕልኬሽን ማሰራት የምትፈልጉ
📍ᴡᴀᴠᴇ Ғᴏʟᴅᴇʀ መግባት የምትፈልጉ
ቻናላችሁ ከ 10ᴋ በላይ የሆናችሁ ብቻ

አናግሩኝ ➛ @Naolviva
የአውስትራሊያው ታዋቂ የአሦሪያ ጳጳስ የግድያ ሙከራ፣ መ*ና*ፍ*ቁ ንስጥሮስ እና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች (እንደወረደ)
++++++
(ቀሲስ ኤፍሬም እሸቴ)
ሀ/ መነሻ
የሰኞ የብዙዎች መነጋገሪያ ርዕሰ ጉዳይ የነበረው በአውስትራሊያ የሚገኙ የአሲሪያ ቤተ ክርስቲያን ጳጳስ ላይ በቤተ መቅደሳቸው እንዳሉ የተፈጸመባቸው የመግደል ሙከራ ነው። ጳጳሱ በቀጥታ ሥርጭት በሚተላለፈውና በመላው ዓለም ያሉ በሺህዎች የሚቆጠሩ ተመልካቾቻቸው በሚከታተሉት ዝግጅት ላይ ነው በስለት የመግደል ሙከራ የተደረገባቸው። አንድ በወጣትነት ዕድሜ ላይ የሚገኝ ሰው ጳጳሱን በስለት ደጋግሞ ሲወጋቸው በቪዲዮው ይታያል። ከእርሳቸውም በተጨማሪ በቤተ መቅደሱ የነበሩ ሌሎች ሰዎች አደጋ ደርሶባቸዋል::
እኒህጳጳስ በፌብርዋሪ ወር 2024ም ተመሳሳይ በስለት የመግደል መኩራ ተደርጎባቸው ተርፈዋል፡፡ በፊብሩዋሪ ወንጀሉን የፈጸመው የ 15 ዓመት ወጣት እንደነበር መገለጹ ይታወሳል።
ዛሬ የተፈጸመባቸው የመግደል ሙከራ በጣም አሳዝኖኛል፣ አስደንግጦኛልም:: በርግጥ ወንጀሉን የፈጸመው ሰው ማንነት ግልጽ ባይሆንልኝም ከሊበራሉ ዓለም እስከ አክራሪ ጽንፈኞች ድረስ ጥቃት ሊያደርሱባቸው የሚችሉ ሰዎች እንዳሉ መገመት ይቻላል። በትምህርታቸው ጠንካራነት ምክንያት። በቅርቡ እንኳን እሥራኤል በጋዛ ፍልስጥኤማውያን ላይ የምትፈጽመውን ጥቃት የተቃወሙበትን ንግግር ተመልክተናል። ይህንን ጽሑፍ እስከጻፍኩበት ሰዓት ድረስ የአውስትራሊያ ፖሊስ ወንጀሉን የፈጸመውን ሰው ማንነት እና ወንጀሉን ለመፈጸም የገፋፋውን ምክንያት አልገለጸም።
ለሁሉም ግን እንኳን እግዚአብሔር አተረፋቸው፡፡ አሁንም ቶሎ አገግመው ወደር ወደሚወዱት አገልግሎት እንዲመለሱ ምኞቴ ነው።
++++
ለ/ ጳጳሱ ማር ማሪ ኢማኑኤል (Bishop Mar Mari Emmanuel) ማን ናቸው?
----------
ማር ማሪ ኢማኑኤል በአውስትራሊያ የሚገኘው የ"Assyrian Church" ሊቀ ጳጳስ ሲሆኑ መልካም እረኛ ቤተ ክርስቲያን (Christ The Good Shepherd Church) በተባለ ሥፍራ ያገለግላሉ። በ2009 (እ.አ.አ) ቅስናን፣ በ2011 ደግሞ ጵጵስና መቀበላቸውን ታሪካቸው ያሳያል።
ጳጳሱ ማር ማሪ ኢማኑኤል በስብከቶቻቸው የሚያነሧቸው ጉዳዮች በብዙ ሰው ዓይን ውስጥ እንዲገቡ ያደረጋቸው ይመስላል። በዘመነ ኮሺድ በመላው ዓለም የተጣለውን ከቤት ያለመውጣት እግድ በጽኑዕ በመቃወማቸው ይታወቃሉ። ከዚያም ቀጥሎ በአሜሪካ እና በሩሲያ ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ የሚሰጧቸው ሐሳቦች በተለይም በሊበራሉ ዓለም "አክራሪ" አሰኝቷል። የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ባይደን "የተመረጡት በሕቡዕ ቡድኖች ይሁንታ ነው" ማለታቸው እንዲሁም "ግ*ብ*ረ ሰ*ዶ*ማ*ዊነት"ን በጽኑዕ መቃወማቸው ጠላት ያፈራባቸው ይመስላል።
ታዋቂነታቸው ከእንግሊዝኛ ተናጋሪው አልፎ ወደ ኢትዮጵያ እና ኤርትራ ኦርቶዶክሳውያን ዘንድም ደርሷል፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ ስለ ጳጳሱ ያወቅኹት ስለ ቤተ ክርስቲያኒን ጠንካራ ትችት ያቀረቡበትን እና ቤተ ክርስቲያን "ንስሐ ግቢ" የሚል መንፈስ ያለው አጭር ቪዲዮ አይቼ ነው። "እንዴ!!! ቤተ ክርስቲያን ኃጢአት የማይስማማት የክርስቶስ አካሉ መሆኗን የደፈጠጠ የምዕራቡ ዓለም ፕሮ*ቴስ*ታን*ቲዝም ትምህርት የሚናገር ጳጳስ ከየት ተገኘ?" ብዬ ተገርሜ ነበር። የግብጽ/ቅብጥ ጳጳስ መስለውኝም ነበር። ኋላ ነው የአሦር ኦርቶዶክስ ጳጳስ መሆናቸውን የተረዳኹት። ብዙ ኦርቶክሳውያን የተዋሕዶ ልጆች ስብከቶቻቸውን ሼር ሲያደርጉ "የተዋሕዶ ጳጳስ መስለዋቸው ይሆን?" እል ነበር።
+++++
ሐ/ ስለ ምሥራቅ አሦሪያ ቤተ ክርስቲያን በመጠኑ
---------
1/ ሙሉ ስማቸው:-
## The Assyrian Church of the East (ACOE)፤
## የፓትርያርኩ መቀመጫ (መንበረ ፓትርያርኩ) ሰሜን ኢራቅ ኢርቢል (Erbil) ነው።
2ኛ/ ሌሎች ሰዎች "ንስጥሮሳዊት ቤተ ክርስቲያን" (the Nestorian Church) ይሏቸዋል። በኤፌሶን ጉባዔ የተወገዘውን የንስጥሮስን አስተምህሮ የሚቀበሉ ቢሆንም ንስጥሮሳውያን መባል አይፈልጉም። ከጽርፈት (ስድብ) ይቆጥሩታል።
3ኛ/ ራሳቸውን "ኦርቶዶክስ" ብለውም አይጠሩም:: በየትኛውም ጽሑፋቸው ላይ "ኦርቶዶክስ" የሚል ቃል አይጠቀሙም። ነገር ግን ብዙ ሰዎች የኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት በተለይም የተዋሕዶዎቹ "የኦሪየንታል አብያተ ክርስቲያናት" አካል አድርገው ይቆጥሯቸዋል። ስሕተት ነው።
4ኛ/ Assyrian Church of the East (branch of Syriac Christianity) ከሚባሉት ውስጥ በ1870 የተለዩት/ የተገነጠሉት "The Chaldean Catholic Church" ከሮማ ካቶሊክ ጋራ ውሕደት ፈጽመዋል። በ1994 ባደረጉት ውሳኔ በነገረ ክርስቶስ ላይ ያላቸውን አስተምህሮም ከሮማ ካቶሊክ ጋራ አንድ አድርገዋል። መንበረ ፓትርያርካቸውም ኢራቅ ባግድዳ ነው። የቅዳሴ ቋንቋቸው ግን ልክ እንደሌሎቹ የሲሪያክ ይትበሐል አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ አሁንም "አራማይክ" ነው።
መ/ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶዎቹ የሦሪያ ክርስቲያኖች
—-------------
ሙሉ ስማቸው The Syriac Orthodox Church ይባላል፤
West Syriac Church ወይም West Syrian Church ይባላሉ፣
በመደበኛው (official) አጠራራቸው ደግሞ the Syriac Orthodox Patriarchate of Antioch and All the East ይባላሉ፤
በኢመደበኛ (informal) አነጋገርም ቢሆን (the Jacobite Church) ያዕቆባዊት ቤተ ክርስቲያን ይባላሉ። በትምህርቱ እና በተቀበለው ሰማዕትነት ቤተ ክርስቲያኗን በተዋሕዶ እምነቷ ባጸናት በሊቀ ጳጳሱ በቅዱስ ያዕቆብ ዘእልበረዲ (Jacob Baradaeus ወይም Jacob bar Addai) ስም ይጠራሉ።
የቅዳሴ ቋንቋቸው አራማይክ ሆኖ ይትበሐሉ ግን "የምዕራብ አራማይክ (West Syriac)" ነው።
ንስጥሮሳውያኑ "የምሥራቅ አራማይክ" ይትበሐል ተከታዮች መሆናቸውን ከላይ መግለጻችንን ልብ ይሏል።
የሕንድ ማላንካራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶዎች የነዚሁ የያዕቆባውያን ኦርቶዶክሶች አካል ናቸው።
++++++
ሠ/ መ*ና*ፍ*ቁ ንስጥሮስ እና የኤፌሶን ጉባኤ (431 ዓ.ም)
—------
ጉባኤ ኤፌሶን በ431 ዓ.ም በኤፌሶን ከተማ በ200 ሊቃውንት የተካሄደ ታላቅ ጉባዔ ነው፡፡ የስብሰባው መሪ ቅዱስ ቄርሎስ ነበር፡፡
የስብሰባው ዋና ምክንያት የንስጥሮስ ክህደት ነው፡፡
የንስጥሮስ ክህደቱም "ቃል ከሥጋ ጋር አልተዋሐደም። ሰው አልኾነም። አምላክም ሰው የሆነው በኅድረት ነው፡፡ ኅድረት ማለትም እመቤታችን የወለደችው ሰውን ብቻ ነው፡፡ ማርያም በወለደችው ሰው ላይ የእግዚአብሔር ቃል አደረበት (ሕድረት)፤ ስለዚህ እርሷም ወላዲተ አምላክ አትባልም" የሚል ነው፡፡
ንስጥሮስን ተከራክሮ የረታውና መልስ ያሳጣው እስክንድርያዊው ሊቀ ጳጳስ ቅ/ቄርሎስ ነው፡፡
የንስጥሮስን የክህደት ትምህርት በመሠረዝ እመቤታችን "እመአምላክ ወላዲተ አምላክ፣ እመ እግዚአብሔር (Mother of God, Theotokos)" መሆኗን እናምናለን፣ እናሳምናለን፣ እናስተምራለን።
ንስጥሮሳውያን እና የነርሱን ትምህርት የሚከተሉ አንዳንድ ፕ*ሮ*ቴስ*ታንቶች ዛሬም ድረስ Mother of Jesus እንጂ Mother of God አይሉም።
* ቅዱስ ቄርሎስ ለንስጥሮስ ሲመልስ፦ "ወልድ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በማይመረመር ተዋሕዶ ሰው የኾነ አምላክ ነውና ቀዳሚ ሲኾን ከዘመናት አስቀድሞ ከአብ የተወለደ ነው! ዳግመኛም ከድንግል ማርያም በሥጋ የተወለደ ነው" ብሏል /ሃይማኖተ አበው 73፣4 ገጽ 271)
+++++
ረ/ ቃል ሥጋ ሆነ፤ ዘእንበለ ሕድረት (ያለማደር)
==============
የንስጥሮስ ክህደት የሆነው "ሕድረት" የሚለው ነው።
ሕድረት ማለት አንድ አካል በሌላ አካል ውስጥ ገብቶ ማደር ማለት ነው። ለምሳሌ መጽሐፍ ማሕደር ውስጥ ያድራል፤ ሰይፍ ሰገባ ውስጥ ያድራል።
በሕድረት ጊዜ አዳሪውና ማደሪያው በባሕርይ አይዋሐዱም።
ቃል ሥጋ የሆነው ግን በሕድረት አይደለም። ቃል ሥጋ ውስጥ አደረ ከተባለ ሥጋ ለቃል ማሕደሩ፤ ልብሱ፤ መቅደሱ ሆነ እንደማለት ነው። ይህ ማለት ደግሞ ባሕርያዊ ተዋሕዶ አልተፈጸመም እንደማለት ነው።
ቃል ግን ሥጋ ሲሆን የቃል ገንዘቡ ሁሉ ለሥጋ፤ የሥጋም ገንዘብ ሁሉ ለቃል ሆኗል። ስለዚህም ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም በፍጹም ተዋሕዶ ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነሥቶ ፍጹም ሰው ፍጹም አምላክ ሆነ እንላለን።
ሰ/ የኢንተርኔት ላይ ክርስትና
—-----
ኢንተርኔቱ በጠቅላላው በተለይ ማኅበራዊ ሚዲያው ሃይማኖታችንን ለማወቅ፣ ለመጠበቅና ለማስፋፋት ይረዳል። ነገር ግን በነባራዊው ዓለም እንዳለው ሕይወታችን ተመልካች፣ መሪ፣ ተቆጪ፣ ተጠያቂ ስለሌለበት ለሃይማኖታዊ ፈተና ሊያጋልጠን ይችላል። ኑ*ፋ*ቄዎች ትክክለኛ ትምህርት፣ የተሳሳቱ መምህራንም ቀና እምነት የሚያስተምሩ መስለው ብዙዎችን ሲያሳስቱ እናያለን። ስለዚህ ራሳችንን ከቀጥተኛዋ የተዋሕዶ ትምህርት ውጪ ሆነን እንዳናገኘው ጥንቃቄ እናድርግ።
ይቆየን!!!!በ Ephrem Eshete Ephrem ከስህተት ትምህርታቸው ውስጥ አንዱን እታች በvideo እለቅላችሁ አለሁ
በዚህ vidoe ይሄ ሰው አብ ከእኔ ይበልጣል ያለው የሰው ልጅ እንጅ የእግዚአብሔር ልጅ አይደለም ይላል አሁንም ክርስቲያን ነው?😁ገና እቀጥላሉሁ ብዙ ምንፍቅናውን
Mar Mari Emmanuel ምንፍቅና ክፍል 3 ለምን ሕጻናትን እንደሚያጠምቁ ሲናገሩ ሰው ሲወለድ በእናቱ ማህጸን ኃጢያተኛ ሁኖ እንደሚወልድ ከአዳም እና ከሄዋን ኃጢያትን እንደሚወረስ ይናገራሉ ይሄ ትምህርት ክርስቶስንም ኃጢያተኛ የሚያደርግ ነው ። እንግድህ ኃጢያት የባሕርይ ስለሆነች ከሰው ልጆች ጋር ተቆራኝታ ስለምትወለድ ክርስቶስም የእኛን ባሕርይ ባሕሪው አድርጎ ስለተወለደ ክርስቶስም ኃጢያተኛ ነው ወደሚል ይወስዳል ። ኃጢያት ይወረሳል የሚል ሰው ክርስቶስ የአዳም ልጅ አይደለም ሊል ግድ ይለዋል ስለዚህ የክርስቶስን ሰው መሆን የሚቃወሙ ናቸው። https://www.tiktok.com/@felgehaggnew/video/7359092137348173088?is_from_webapp=1&sender_device=pc&web_id=7341272909975946758
HTML Embed Code:
2024/05/03 03:25:02
Back to Top