TG Telegram Group Link
Channel: ✞ ደጓ እናቴ ማርያም ✞
Back to Bottom
Watch "ድንግል ማርያም #ማርያም #shorts ##subscribe #ማኀቶት" on YouTube
https://youtu.be/IZDg9MeQ7CQ
🎬 ©ንስሀ" ሐና ዳኘው |Niseha| Hana dagnew

⭕️ሊደመጥ ሚገባ⭕️

👤 ኪነ ተዋህዶ ቲዩብ

⚠️ ለማዳመጥ ከስር ባስቀመጥነው LINK ያገኙታል!
🛑👇👇🛑
https://youtu.be/QzrSmQi4Qp0
https://youtu.be/QzrSmQi4Qp0
https://youtu.be/QzrSmQi4Qp0
🎬 ©ፈፅሞ ልትረሳቸው ማይገቡ ጉዳዮች" ሐና ዳኘው | Hana dagnew

👤 ኪነ ተዋህዶ ቲዩብ

⚠️ ለማዳመጥ ከስር ባስቀመጥነው LINK ያገኙታል!
https://youtu.be/cb164bbwcKU
https://youtu.be/cb164bbwcKU
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
የመስቀል ደመራ በዓል ታሪክና አከባበር

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሰውን ልጅ ከወደቀበት መርገም ያድነው ዘንድ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ተወልዶ በ33 ዓመቱ በራሱ ፈቃድ በመስቀል ላይ ተሰቀለ፡፡ በመገረፉ ቁስል እኛ ተፈወስን (1ጴጥ 2፥24):: በስቅለቱም ዲያብሎስን ድል ነሥቶ በወህኒ /በሲዖል/ ለነበሩ ነፍሳት ነጻነትን ሰበከላቸው (1ጴጥ 3፥18-19):: የሰው ልጅ በሙሉ ከዲያብሎስ ባርነት ፍጹም ነጻ ወጣ:: ሰላምንም ያደርግ ዘንድ ጥልንም በመስቀሉ ገድሎ ሕዝብና አሕዛብን በአንድ አካል ከራሱ ከእግዚአብሔር ጋር አስታረቀ (ኤፌ 2፥16)፡፡ ከፍተኛ ወንጀል የሠሩ ሰዎች ብቻ ይሰቀሉበት የነበረው መስቀል ከጌታ ስቅለት በኋላ የመዳን ምልክት ሆነ::
ዳሩ ግን ጌታ የተሰቀለበት መስቀል ተአምራትን በማድረጉ የታወኩ አይሁድ መስቀሉን ከሰዎች እይታ ለመሠወር ወሰኑ:: ጉድጓድ ቆፍረው ቀበሩት:: መስቀሉ የተቀበረበትን ቦታ ለ300 ዓመታት ያህል የቆሻሻ መጣያና ማከማቻም አደረጉት:: ምንም እንኳን አይሁድ ለጊዜው መስቀሉን ከዐይን ለመሰወር ቢችሉም ከክርስቲያኖች ልቡና ግን ሊያወጡት አልቻሉም:: የመስቀሉ ብርሃን በልቡናቸው የሚያበራ ክርስቲያኖች እየበዙ መጡ:: መስቀሉንም መፈለግ ጀመሩ::

#ለወዳጆ_ሼር_ያድርጉ
╔═★══════════📄══╗
         @Zemaryan         
         @Zemaryan         
         @Zemaryan         
╚══📃══════════★═╝
የንግሥት እሌኒ ድካምና ፍሬ

ንግሥት እሌኒ ልጇን ቆስጠንጢኖስን ከልጅነቱ ጀምሮ ስለ ክርስትና ሃይማኖትና ስለ ክርስቲያኖች መከራ ታስተምረው ስለነበር በክርስቲያኖች ላይ የነበረው አመለካከት በሮም ከነገሡት ቄሣሮች ሁሉ የተሻለ ነበር፡፡ ቆስጠንጢኖስ የሮም ንጉሠ ነገሥት ከሆነ በኋላ በ300 ዓመታት ውስጥ ለመጀመርያ ጊዜ ለክርስቲያኖች የነጻነት ዐዋጅ ዐወጀ፡፡ ክርስትናም ብሔራዊ ሃይማኖት ሆነች፡፡ ንግሥት እሌኒም የተፈጠረውን አመች ሁኔታ በመጠቀም የጌታችንን መስቀል ከተቀበረበት ለማውጣት በ327 ዓ/ም ወደ ኢየሩሳሌም ሔደች፡፡
ንግሥት እሌኒ ልጇ ቆስጠንጢኖስ ክርስቲያን ከሆነላት ወደ ኢየሩሳሌም ሔዳ መስቀሉን ለመፈለግ እንዲሁም በኢየሩሳሌም ያሉ ቅዱሳት መካናትንና አብያተ ክርስቲያናትን ለማሳነፅ ለእግዚአብሔር ተሳለች፡፡ ከዚህ በኋላ ቆስጠንጢኖስ አምኖ በ337 ዓ/ም ተጠመቀ፡፡ ቅድስት እሌኒም ወደ ኢየሩሳሌም ሔደች እንደደረሰችም ስለ ክብረ መስቀል መረመረች ጠየቀች፡፡ ቦታውን የሚያስረዳት ግን አላገኘችም፡፡ አይሁድ የተቀበረበትን ቦታ ለማሳየት ባይፈልጉም በኋላ ባደረገችው ጥረት አረጋዊው ኪራኮስ የጎልጎታን ኮረብታ አመላከታት ዳሩ ግን ኪራኮስ ዘመኑ ከመርዘሙ ጋር ተያይዞ በአካባቢው ከነበሩት ከሦስቱ ተራሮች ውስጥ መስቀሉ የሚገኝበት የትኛው እንደሆነ ለይቶ ማወቅ አልቻለም፡፡
ንግሥት እሌኒ ከሦስቱ ተራሮች የቱ እንደሆነ ለመለየት በእግዚአብሔር መልአክ እርዳታ ደመራ አስደምራ ብዙ እጣንም በመጨመርና በማቃጠል ጸሎት ተያዘ፡፡ የእጣኑ ጢስ ወደ ሰማይ በመውጣት በቀጥታ ተመልሶ መስቀሉ ባለበት ተራራ ላይ በማረፍና በመስገድ መስቀሉ ያለበትን ትክክለኛ ስፍራ አመለከታት፡፡ ቅዱስ ያሬድም ጢሱ ሰገደ ብሎታል፡፡ ከዚያም መስከረም 16 ቀን ቁፋሮው እንዲጀመር አዘዘች፡፡ ሰባት ወር ያህል ከተቆፈረ በኋላ መጋቢት 10 ቀን ሦስት መስቀሎች በአንድነት ተገኙ፡፡የክብር ባለቤት ጌታችን የተሰቀለበት የትኛው እንደሆነ ለማወቅ ተቸገሩ፡: መስቀሎቹን ወስደው በሞተ  ሰው በተራ ቢያስቀምጡ ጌታችን የተሰቀለበትና በዕለተ ዐርብ ተሰቅሎ የዋለበትና በደሙ መፍሰስ የተቀደሰው መሰቀል የሞተውን ሰው በማስነሣት በሠራው ተአምር ሌሎቹ ሁለቱ ታምራት ባለማድረጋቸው የጌታን መስቀል ለይቶ ማወቅ ተችሏል። እሌኒና ክርስቲያኖች ሁሉ ለመስቀሉ ሰገዱለት፡፡ በየሀገሩ ያሉ ክርስትያኖች ሁሉ የመስቀሉን መገኘት በሰሙ ጊዜ መብራት አብርተው ደስታቸውን በመግለጥ ለዓለም እንዲታወቅ አደረጉ፡፡ ንግሥት እሌኒ ለመስቀሉ ቤተ መቅደስ ከሠራችለት ጊዜ ጀምሮ በመስከረም 17 ቀን አሁን በኢትዮጵያ እንደሚከበረው በክርስቲያኖች ዘንድ መስቀል ይከበር ነበር።

#ለወዳጆ_ሼር_ያድርጉ
╔═★══════════📄══╗
         @Zemaryan         
         @Zemaryan         
         @Zemaryan         
╚══📃══════════★═╝
ግማደ መስቀሉ ወደ ኢትዮጵያ እንዴት መጣ? 

የጌታ መስቀል ለብዙ ዓመታት በኢየሩሳሌም ከቆየ በኋላ ነገሥታት መስቀሉን ለመውሰድ ጠብ ፈጠሩ፡፡ በዚህ ጊዜ የአንጾኪያ፣ የኤፌሶን፣ የአርማንያ፣ የግሪክ፣የእስክንድርያ፣ የመሳሰሉት የሃይማኖት መሪዎች ጠቡን አበረዱት:: ከዚያም አያይዘው በኢየሩሳሌም የሚገኘውን የክርስቶስን መስቀል ለዐራት ከፍለው በስምምነት ተካፍለው ከሌሎች ታሪካዊ ንዋያተ ቅድሳት ጋር በየሀገራቸው ወስደው በክብር አስቀመጡት:: የቀኝ ክንፉ የደረሰው ለአፍሪቃ ስለነበር ከታሪካዊ ንዋየ ቅድሳት ጋር በግብፅ የሚገኘው የእስክንድርያ ፓትርያርክ ተረክቦ ወስዶ በክብር አስቀመጠው፡፡
ኢትዮጵያዊው ንጉሥ ዳግማዊ ዳዊት የግብፅ ክርስቲያኖች በአማሌቃውያን ከሚደርስባቸው ተጽዕኖ ነጻ እንዲወጡ በማድረጋቸው የግብፅ ፓትርያርክ የከበሩ ስጦታዎችን ላኩላቸው:: ንጉሥ ዳግማዊ ዳዊት ግን የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን የምትፈልገው ወርቅ ሳይሆን ጌታ የተሰቀለበትን መስቀሉን እንደሆነ ገለጹላቸው:: በመሆኑም የግብፅ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ግማደ መስቀሉን ከሌሎች ንዋየ ቅድሳት ጋር ለኢትዮጵያ ሰጥታለች:: ይህ ግማደ መስቀል በግሸን ማርያም ገዳም በእግዚአብሔር አብ ቤተ ክርስቲያን ሆኖ ኢትዮጵያን እየባረከ ይገኛል::
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መስቀልን ከሐዋርያት በተማረችው መሠረት የወርና የዓመት በዓል ሠርታ ታከብረዋለች:: መስከረም 16 ቀን ደመራ ደምራ ጸሎትና ምሥጋና ታቀርባለች። ቅዱስ መስቀል ከተቀበረበት መሬት በእሌኒ አማካኝነት መገኘቱን ስታስብ በአሁኑ ዘመን ከብዙ ሰዎች ልቡና የተሠወረው መስቀል እንዲገለጥላቸው ትጸልያለች:: በመስቀል የሚገኘውን በረከት እየተቀበለች በመስቀል የሚመሰለውን መከራ ሁሉ ትታገሣለች:: መስቀል በካህናት በምእመናንና በምእመናት ልቡና ተስሏል:: በአንገታቸውና ልብሳቸውም መስቀል አለ:: ሥራ ሲጀመርና ምግብ ሲቀርብ በመስቀል አምሳያ ይማተባል:: መስቀል ለሁሉም ነገር መጀመሪያና መጨረሻ  ነው:: “እኔን መከተል የሚወድ ቢኖር ራሱን ይካድ መስቀሉንም ተሸክሞ ይከተለኝ” (ማቴ 16፡24) እንዳለ ጌታችን ቤተ ክርስቲያናችን ዕለት ዕለት መስቀሉን ትሸከማለች።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በየዓመቱ መስከረም 16 ቀን የምትደምረው ደመራ አገራዊ አንደምታም አለው:: የመስቀል ደመራ በተባበሩት መንግስታት የትምህርት: የሳይንስና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) እውቅና ተሰጥቶት ዓለም አቀፋዊ ቅርስ ተብሎ ተመዝግቧል::
ከሀገር ቤት ርቀን የምንገኝ ኢትዮጵያውያንም የበዓሉን ታላቅነት ለልጆቻችንና ለምንኖርበት የኖርዌይ ኅብረተሰብ ማስረዳትና የበዓሉ ታዳሚ እንዲሆኑ ማድረግም ይጠበቅብናል። «የመስቀሉ ቃል ለሚጠፉት ሞኝነት ለእኛ ለምንድን ግን የእግዚብሔር ኃይል ነው» (1ቆሮ 1፥18) እያልን ልናከብረውና ልንጠብቀው ይገባናል።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር!

#ለወዳጆ_ሼር_ያድርጉ

╔═★══════════📄══╗
         @Zemaryan         
         @Zemaryan         
         @Zemaryan         
╚══📃══════════★═╝
"አባ አባ ተክለሃይማኖት"
ዝማሬ ዳዊት On Telegram
አባ አባ ተክለሃይማኖት

አባ አባ ተክለሃይማኖት አቡዬ /2/
በለኒ በለኒ ወልድየ /2/
አዝ
አባ አባ - - - እንኳን ሰው ምድሪቱን
አባ አባ - - - ጦም አያሳድርም
አባ አባ - - - አምላከ ተክልዬ
አባ አባ - - - ብዬ አፍሬ አላውቅም
አባ አባ - - - ምድራዊ መልዓክ ነህ
አባ አባ - - - የእቲሳ አምበሳ
አባ አባ - - - ለደብረ ሊባኖስ
አባ አባ - - - አንተ ነህ ሞገሷ
አዝ
አባ አባ - - - ስማኒ ብያለው
አባ አባ - - - ሳለ በሰማይ
አባ አባ - - - ከኪሩቤል ተርታ
አባ አባ - - - ሆነህ ስትታይ
አባ አባ - - - ስምህም ሲጠራ
አባ አባ - - - ገድልህ ሲነገር
አባ አባ - - - እፁብ ድንቅ ያሰኛል
አባ አባ - - - የተሰጠህ ክብር
አዝ
አባ አባ - - - አባቴ እልሃለው
አባ አባ - - - ልጄ ሆይ በለኝ
አባ አባ - - - የአባትና የልጅ
አባ አባ - - - ፍቅርህ ይጽናልኝ
አባ አባ - - - ንፍሮ ውሃ ጠጥቼ
አባ አባ - - - ታምር አይቻለሁ
አባ አባ - - - እባብና ጊንጡን
አባ አባ - - - ተረማምጃለሁ
አዝ
አባ አባ - - - እለት በለት ሄጄ
አባ አባ - - - ደጅ ስጠናው
አባ አባ - - - ይሰማል ተክልዬ
አባ አባ - - - ዛሬም ህያው ነው
አባ አባ - - - እንቆቅልሽ ፈቶ
አባ አባ - - - ደስ አሰኝቶኛል
አባ አባ - - - የተክለሃይማኖት
አባ አባ - - - ቡራኬው ደርሶኛል
ጌታችን ኢየሱስ🥹🤗🙏

እሰይ ተወለደ..
Audio
እሠይ_ተወለደ_የአለም_መድሀኒት||የገና መዝሙር|| orthodox_Ethiopia ||
እኛስ በሥጋ ከማርያም #የተወለደውን ክርስቶስን እንሰብካለን
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መግለጫ ተሰጠ ።

መግለጫውን ለኢኦተቤ ቴቪ (EOTC TV) የሠጡት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ቀዳማዊ ፖትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት; ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አኪያጅና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ : በመንበረ ፓትርያርክ የተገኙ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ናቸው።

ቅዱስነታቸው ዛሬ ማለዳ በተሰማው ሕገ ወጥ "ሢመተ ጳጳሳት" ጉዳይ በሰጡት መግለጫ ጉዳዩ ከቅዱስ ሲኖዶስ እውቅና ውጪ በሕገወጥነት የተከናወነ መሆኑን በመግለጽ :-
1. በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጭ ያሉ ሊቃነ ጳጳሳት በአስቸኳይ ወደ መንበረ ፓትርያርክ እንዲመጡ ጥሪ ቀርቧል።
2. መንግሥት ክስተቱ በሀገር ላይ ጭምር የሚያስከትለውን ጉዳት ተመልክቶ በጉዳዩ ላይ ሕጋዊ ሓላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ ቀርቧል።
3. ምዕመናን ቤተክርስቲያንን ከመቸውም ጊዜ በላይ በንቃት በሀሣብና በጸሎት እንዲጠብቁ ቅዱስነታቸው ጥሪ አቅርበዋል።

ምንጭ: EOTC TV
ከማኅበረ ቅዱሳን በወቅታዊ ጉዳይ የተሰጠ መግለጫ
#ልዩ_መረጃ

በ"አባ" ሳዊሮስ አማካይነት ከታች የተዘረዘሩት አህጉረ ስብከት ላይ የስምዝርዝራቸው የሚገኘው መነኮሳት የአህጉረ ስብከቱ መንበረ ጵጵስ እና ከቅዱስ ሲኖዶስ ፈቃድና እውቅና ውጭ ወረራ እንዲፈጸምበት ስምሪት የተሰጠ በመሆኑ በየአካባቢው የምትገኙ ካህናትና ምዕመናን መንበረ ጵጵስና አህጉረ ስብከቱን እንድትጠብቁ ጥሪ ቀርቧል!

1."አባ" ገ/ማርያም ነጋሳ - ምዕራብ ወለጋ ሀገረ ስብከት
2."አባ" ተ/ሃይማኖት ወልዱ - ድሬዳዋ ሀገረ ስብከት
3."አባ" ገብርኤል ወ/ዮሐንስ - ጉራጌ ሶዶ ሀገረ ስብከት
4."አባ" ገ/እግዚአብሔር ታደለ - ምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት
5."አባ" ሚካኤል ገ/ማርያም - ከምባታ ሀገረ ስብከት
6."አባ" ኃይሉ እንዳለ - ምሥራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት
7."አባ" ተ/ማርያም ስሜ - ጉጂ ሊበን ሀገረ ስብከት
8."አባ" ኃ/ኢየሱስ መንግስቱ - ከፋ ሀገረ ስብከት
9."አባ" ወ/ኢየሱስ ኢፋ - ቄለም ወለጋ ሀገረ ስብከት
10."አባ" ጳውሎስ ከበደ - ሀዲያ ሀገረ ስብከት
11."አባ" ኃ/ኢየሱስ ተስፋዬ - ምሥራቅ ወለጋ ሀገረ ስብከት
12."አባ" ገ/ኢየሱስ ገለታ - ሆሮ ጉዱሩ ሀገረ ስብከት
13."አባ" ጸጋዘአብ አዱኛ - ምሁር ኢየሱስ ገዳም "የበላይ ጠባቂ"
14."አባ" ኃ/ማርያም ጌታቸው - ምዕራብ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት
15."አባ" ወ/ጊዮርጊስ ኃ/ሚካኤል - ከሚሴ ሀገረ ስብከት
16."አባ" እስጢፋኖስ ገብሬ - ባሌ ሀገረ ስብከት ረዳት
17."አባ" ገ/መድኅን ገ/ማርያም - ጎፋ ባስኬቶ ሀገረ ስብከት
18."አባ" ኃ/ሚካኤል ንጉሤ - ጊኒር ሀገረ ስብከት
19."አባ" አብርሃም መስቀሌ - ዳውሮ,ኮንታ ሀገረ ስብከት
20."አባ" ንዋየ ሥላሴ አክሊሉ - ምዕራብ ጉጂ ሀገረ ስብከት
21.አባ ኪ/ማርያም ቶሎሳ - ጅማና የም ሀገረ ስብከት
22."አባ" ወ/ማርያም ጸጋ - ቦረና ሀገረ ስብከት
23."አባ" አምደሚካኤል ኃይሌ - አርሲ (አሰላ) ሀገረ ስብከት
24."አባ" መርሐጽድቅ ኃ/ማርያም - ጌዴኦ,ቡርጁ,አማሮ ሀገረ ስብከት
25."አባ" ሞገስ ኃ/ማርያም - መናገሻ አምባ ቅድስት ማርያም ፣ ጋራ መ/ዓለምና ደ/ፀሐይ ቅ/ጊዮርጊስ "የበላይ ጠባቂ"
26."አባ" ገ/ኢየሱስ ንጉሤ - ቡኖ በደሌ ሀገረ ስብከት

መረጃው የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ነው
መልዕክቱን ለሁሉም በማዳረስ ግዴታዎን ይወጡ ።
HTML Embed Code:
2024/06/01 14:25:40
Back to Top