TG Telegram Group Link
Channel: Campus love ❤ Stories
Back to Bottom
......... የሀዘኔ መጨረሻ ........

ክፍል 17

.......እጄን ይዞ ወደቤት አስገባኝ........ከዛን ቀን ጀምሮ ወ/ሮ ኤልሳ ለኔና ለአቤል ጥሩ ፊት አሳይታን አታውቅም፡፡ አቤልን ዝም ብላ ትቆጣዋለች እኔን ደግሞ ዝም ብላ ትገላምጠኛለች፡፡ እኔ ግን ባልሰማ ባላየ እላታለው፡፡እኔና ብሩኬ ቅልጥ ያለ ፍቅር ውስጥ ገባን፡፡ ወራቶች ተቆጠሩ ብሩኬም ወደ ዩንቨርስቲ መግቢያ ፈተና የሚወስድበት ቀን ደረሰ፡፡ ብሩኬ የማትሪክ ፈተናውን ካለፈ ወደሚደርሰው ዩንቨርስቲ እንደሚሄድ ሳስብ በጣም ይጨንቀኝ ጀመር፡፡ ብሩኬም በጣም ጨንቆታል፡፡ የፈተናው ቀንም ደረሰ፡፡ ብሩኬ በንፁህ ልቡ ፈተናውን እንዲሰራውና በጣም እንደምወደው ነግሬው ሸኘሁት፡፡

ፈተናውንም ተፈትኖ ወጣ፡፡ ፊቱ ላይ ፍርሀት ይታይበት ነበር፡፡ "ምነው ብሩኬ ፈተና ይከብድ ነበር እንዴ" አልኩት በጋ እያለኝ "ፈተናው በጣም ቆንጆ ነበር ግን ሰላሜ ፈተናውን ካለፍኩኝ የምለይሽ መስሎኝ በጣም ጨንቆኛል" ከለኝ፡፡ እቅፍ አድርጌው "ፈጣሪ ያለው ነው የሚሆነው አትጨነቅ" አልኩት፡፡ የፈተናውም ውጤት የሚለጠፍበት ቀን ደረሰ፡፡ እኔና ብሩኬ አብረን ሄደን ውጤቱን አየነው፡፡ ብሩኬ በጥሩ ውጤት አልፉል፡፡ ብሩኬ በጣም ደስ አለኝ ፡፡ ወድያው ወደ ቤት ተመለስን አቶ ሄኖክና ወ/ሮ ኤልሳ ውጤቱን ለመስማት ጓጉተው ነበር፡፡ እንደገባን ብሩኬ ውጤቱን ነገራቸው፡፡ ወ/ሮ ኤልሳ ቤቱን በእልልታ አቀለጠችው አቶ ሄኖክም በኩራት ወደ ብሩኬ ጠጋ ብለው ግንባሩን ሳሙት፡፡

ለምን ብሩኬ ፊት ላይ ደስታ እንደማይታይ ጠየቁት፡፡ እሱም " ማም ዳድ ማትሪክን በጥሩ ውጤት አልፌያለው እናንተም ይሄን ቀን ስትጠብቁት ነበር ......ግን እኔ ሌላ ሀገር መሄድ አልፈልግም እዚሁ መማር ነው የምፈልገው እባካቹ ወደ ሌላ ሀገር ሂድ እንዳትሉኝ "አላቸው፡፡ አቶ ሄኖክ ሳቃቸውን ገታ አድርገው ሶፋው ላይ ቁጭ አሉ፡፡

በድንገት ከሶፋው ላይ ተነስተው "ችግር የለውም ልጄ እዚሁ አለ የተባለ ኮሌጅ ውስጥ አስገባሀለው " አሉት ፡፡ ወ/ሮ ኤልሳም ፈገግ ብላ "አው ልጄ ከዚህ እንድትርቅ አልፈልግም አባትህ እንዳለው እዚሁ ትማራለህ " አለችው፡፡ ብሩኬም ዞር ብሎ የፊቱን ፈገግታ አሳየኝ እኔም ሳቅ አልኩኝ፡፡ ምሳችነነ መብላት ቀጠልን

ከትንሽ ሳምንታት በኀላ አቶ ሄኖክ ክፍሌ መጡ፡፡ በሩንም ከፈትኩላቸው በጣም ተናደው ነበር በጣም ደንግጬ " ምነው" አልኳቸው፡፡ ወሬውን ትቼ ወደ ክፍሌ እንድገባ ነገሩኝ ........

ክፍል 18 እንዲቀጥል like ማድረግ አትርሱ
........የሀዘኔ መጨረሻ .........

ክፍል 18

.......እንድገባ ነገሩኝ.......እኔም በፍርሀት ገብቼ አልጋዬ ላይ ቁጭ አልኩኝ፡፡ ኮስተር ብለው ይልማ ምንድን ነው ያደረገሽ አሉኝ፡፡ በጣም ደነገጥኩኝ "አይ ምንም" አልኳቸው፡፡ ድምፃቸውን ከፍ አድርገው "አትዋሺኝ ..... እኔን እኮ እንደ አባትሽ ልታይኝ ትችያለሽ እውነቱን ንገሪኝ " አሉኝ፡፡ አንገቴን አቀረቀርኩኝ፡፡ ወድያው ብሩኬ መጣ....

"ሰላም አትፍሪ ሁሉንም ነገር ለዳድ መናገር ትችያለሽ " አለኝ፡፡ ሳስበው ይልማ ሊያደርገኝ ለነበረው ነገር ቅጣት ማግኘት እንዳለበት ተሰማኝና ሁሉንም ነገር ነገርኳቸው፡፡

አቶ ሄኖክም እቅፍ አድርገውኝ "አይዞሽ ልጄ ሁሉም ነገር ያልፋል ሊያደርስብሽ ለነበረው ጥቃት ዋጋውን ያገኛል፡፡" አሉኝ፡፡ እኔም እንባዮን መጠራረግ ያዝኩኝ፡፡

አቶ ሄኖክ " በይ ሰላም ተነሺ ወደ ፖሊስ ጣቢያ እንሂድ አሉኝ፡፡" ብሩኬም "አው ልክ ነው ተነሺ እኔም አብሬያቹ እሄዳለው " አለን፡፡ ምንም አላንገራገርኩም በፍጥነት ለባብሼ አብረን ወደ ፖሊስ ጣቢያ ሄድን፡፡

እንደደረስን አቶ ሄኖክ መርማሪው ክፍል ገባ፡፡ እኔና ብሩኬም ውጪ ቆየን፡፡ ከትንሽ ደቂቃዎቾ በኀላ ወደ መርማሪው ክፍል ገባን፡፡ ተቀመጥን ከመርማሪው ጋር ከተዋወቅን በኀላ "ሰላም አቶ ሄኖክ አንዳንድ ነገሮችን ነግረውኛል አሁን አንቺ በዝርዝር ትነግሪኛለሽ" አለኝ፡፡ እኔም "እሺ" አልኩት፡፡ እስኪብርቶውን ከጠረቤዛው ላይ እያነሳ ከፊት ለፊቱ ባለው ደብተር ለመፃፍ እየቃጣ በይ አሁን ጀምሪ አለኝ፡፡ አቶ ሄኖክም "በይ ሰላም እንዳትፈሪ ሁሉንም ነገር ተናገሪ" አሉኝ፡፡ ብሩኬንም ሳየው በፈገግታ አንገቱን ነቀነቀልኝ፡፡ እኔም የሆነውን ነገር በሙሉ ለመርማሪው ተናገርኩኝ፡፡ መርማሪውም ሁሉን ነገር ከሰማ በኀላ "በሉ አሁን ወደቤታችሁ መሄድ ትችላላቹ የተቀረውን እኛ እንጨርሰዋለን" አለን፡፡ እኛም ወደ ቤት ተመልሰን ሄድን፡በሙ
እቤት እንደደረስን ወ/ሮ ኤልሳ "ይቅር በይኝ ሰላም ምንም ነገር አላወኩም ነበር እባክሽ ይቅር በይኝ " አለችኝ፡፡ እኔም "ምንም ችግር የለውም " አልኳት፡፡ አቀፈችኝ እኔም አቀፍኳት፡፡ ብሩኬና አቶ ሄኖክ ፊታቸው በፈገግታ አበራ፡፡ አቤልም መጥቶ እቅፍ አደረገኝ በጣም ተደሰትኩኝ፡፡ይልማም ተይዞ ታሰረ፡፡ መታሰሩን ሳይ በጣም ጠነከርኩኝ፡፡ ከትንሽ ቀን በኀላ ፍርድ ቤት ቀርቦ የ5 አመት እስራት ተፈረደበት፡፡

ወ/ሮ ኤልሳ ስለታሰረ ከፍቷቷል ግን ቅጣቱ እንደሚገባው አውቃለች፡፡ ከዛች ቀን ጀምሮ ሰላማዊና የተረጋጋ ህይወት ኖረኝ፡፡

በድንገት አንድ ቀን ጠዋት አቶ ሄኖክ ተነስተው ብሩክ ወደ ዮንቨርስቲ መሄድ እንዳለበት ተናገሩ ፡፡ ሁላችንም ደነገጥን፡፡ ወ/ሮ ኤልሳ ለምን ብላ ጥያቄ አቀረበች፡፡ የሳቸው መልስ የሆነውም ሳስብበት ቆይቼ እዛ ሄዶ እንዲማር ወስኛለው ምክንያቱም የህይወትን ውጣ ውረድ ማሳለፍ አለበት ሰው እንዴት ተምሮ በራሱ እንደሚቆም ማወቅ አለበት፡፡ እዚህ ከተማረ የሚጎልበት ነገር አይኖርም እሱ ደግሞ ለቀጣይ ህይወቱ ጥሩ አይሆንም አሉ፡፡

ክፍል 19 እንዲቀጥል like ማድረግ አትርሱ

CONTACT US @Juliiian
......የሀዘኔ መጨረሻ .........

ክፍል 19

.....አይሆንም አሉ፡፡ ከዛን ወደ መኝታ ክፍላቸው ገቡ፡፡ ወ/ሮ ኤልሳም ተከትላቸው ገባች፡፡ እኔና ብሩኬ ብቻ ቀረን፡፡ "ሰላሜ ካንቺ መለየት አልፈልግም " አለኝ፡፡ እንባዬ ፈሰሰ ፊቴ ላይ የውሸት ፈገግታ ጣል እያደረኩበት "ብሩኬ የአባትህን ትዛዝ ማክበር አለብህ እኔ ሁሌም እጠብቅሀለው " ብዬው እየሮጥኩኝ ወደ ክፍሌ ገብቼ ማልቀሴን ቀጠልኩኝ፡፡

ያው ጊዜያቶች ሄዱ፡፡ ብሩኬ ወደ ሌላ ዮንቨርስቲ እንዲሄድ ሆነ፡፡ በጣም ነበር የከፋኝ፡፡ ብሩኬም እንደዛው፡፡ ብሩኬ እቃዎቹን ማዘገጃጀት ጀመረ፡፡ የመሄጃው ቀን አይኑን አፍጥጦ ወጣ፡፡ የደረሰው ባህር ዳር ዮንቨርስቲ ነበር፡፡

አመሻሽ ላይ ብሩኬን የሚወስደው መኪና መጣ፡፡ በፍጥነት ከክፍሌ ወጥቼ ወደ ሳሎን ሄድኩኝ፡፡ ወ/ሮ ኤልሳ ብሩኬን አቅፋ ታለቅሳለች፡፡ አቤል ሶፋው ጥግ ላይ ተቀምጦ ለንቦጩን ጥሎታል፡፡ አቶ ሄኖክ ወ/ሮ ኤልሳን ማባበል ይዘዋል፡፡ ደርቄ ቀረሁኝ፡፡ ብሩኬ ዞር ብሎ አየኝ ከማልቀሴ ብዛት አይኖቼ ቲማቲም መስለው ነበር፡፡ ወደኔ ቀረብ አለኝ አንገቴን አቀረቀርኩኝ "ሰሊ ቻው አትይኝም እንዴ " አለኝ ፡፡ ከአይኔ እንባ እየፈሰሰ ተጠመጠምኩበት፡፡ አቶ ሄኖክ በድካም ስሜት ሶፋው ላይ ቁጭ አሉ፡፡

ከብሩኬ እቅፍ መውጣት አልፈለኩም ነበር፡፡ ግን ወድያው ሹፌሩ መጣና "ዝግጁ ነኝ ጌታዮ መሄድ እንችላለን " አለ፡፡ አቶ ሄኖክም " በል ልጄ እንዳይረፍድብህ ሂድ " አሉት፡፡ እሱም ወደ መኪናው አመራ፡፡ ከአይኖቹ እንባ ጠብ ጠብ ሲል ታየኝ፡፡ ፈጣሪዬ ለምንድን ነው የምወዳቸውን ሰዎች የሚወስድብኝ ብዬ ተማረርኩኝ፡፡ ሁላችንም አቅፎን መኪናው ውስጥ ገባ፡፡ ሁላችንም እያለቀስን ነው፡፡ መኪናው መንቀሳቀስ ጀመረ፡፡ ገና ከግቢ ሳይወጣ ቆመ፡፡ ብሩኬ ከመኪናው ውስጥ ወጥቶ አቶ ሄኖክ እግር ስር ወድቆ " አባቴ እባክህ እንድሄድ አታስገድደኝ እኔ እዚሁ መማር ነው የምፈልገው፡፡ ያንተን ትዕዛዝ ላለመሻር ብዬ የማልፈልገውን ነገር እንዳደርግ አትፍረድብኝ እባክህ አባት! " አለው፡፡ አቶ ሄኖክ ራሳቸውን ያዝ አደረጉ፡፡ ወ/ሮ ኤልሳ ብሩኬን ከአቶ ሄኖክ እግር ስር እያነሳች " ሄኖክ አሁንስ አበዛኀው ልጄ ጥሩ ልጅ ነው እንደማንኛውም ሌባ አይደለም ለሁሉምለሚፈልገው ነገር ዋጋ መክፈል ያውቃል ልጄን እንደዚ ነው ያሳደግኩት ስለዚህ እዚሁ እንዲማር አድርግ እባክህ አታስገድደው " አለችው፡፡

አቶ ሄኖክም ብሩኬን አቀፍ እያደረጉ " ልጄ ታውቃለህ ላንተ የሚበጀውን ነው የምፈልገው ግን እንደማንኛውም የሀብታም ልጅ በቤተሰብህ ብር የምትመካ እንዳትሆን ብዮ ነው " አሉት ፡፡ ብሩኬም "አይዞህ አባቴ እንደዚያ አይነት ሰው አልሆንም ብቻ አንተ አታስገድደኝ" አለው፡፡ አቶ ሄኖክም "እሺ ልጄ አምንሀለው እዚሁ ትማራለህ "አሉት፡፡ ሁላችንም ፊት ላይ ፈገግታ አበራ፡፡ ተቃቀፍን፡፡ ወደ ቤታችንም ገባን፡፡ የዛን ቀን ከምታስቡት በላይ ነበር ደስያለኝ፡፡የኔና የብሩኬ ፍቅርም ጦፈ፡፡

ብሩኬም ኮሌጅ ገባ እኔም 12ኛ ክፍል ገባሁ፡፡ ብሩኬ በትምህርቱ በጣም ጎበዝ ስለሆነ ያስጠናኛል፡፡ የምር አፍቃሪ ነው፡፡ አንድ ቀን ክፍሌ ውስጥ እያስጠናኝ " ሰላሜ " አለኝ፡፡ "ወዬ " አልኩት፡፡ ትኩር ብሎ እያየኝ "በጣም እኮነው የማፈቅርሽ " አለኝ፡፡እኔም በስስት እያየሁት " እኔም በጣም አፈቅርሀለው " አልኩት፡፡ አይን ለአይን ተፋጠጥን......

ክፍል 20 እንዲቀጥል like ማድረግ አትርሱ
Selam Selam endet nachu Salpost bzu endekoyew Awkalw Tsehafiwa tarikun Slalcheresech nw Betaaaaam Yikrta stchers epostalew
Campus love Stories pinned «Selam Selam endet nachu Salpost bzu endekoyew Awkalw Tsehafiwa tarikun Slalcheresech nw Betaaaaam Yikrta stchers epostalew»
❤️ምርጥ አጭር የፍቅር ታሪክ❤️


ወጣቱ ሲዲ ሊገዛ ወደ አንድ ሱፐርማርኬት ዘው ብሎ እንደገባ ነበር ዓይኑ
አንዲት ልጅ ላይ ያረፈው😍፡፡ ደስ የምትል የምታምር ልጅ! ልጅቱ ሱፐርማርኬቱ
ውስጥ ካሉት ሻጮች መሃከል አንዷ ነች፡፡ ለረጅም ጊዜ የሚያውቃት ያህል ነው
የተሰማው፡፡ አንዳች ደስ የሚል ስሜት ሲስበው፣ ሄደህ አናግራት፣ አዋራት፣
አብረሃት ሁን ሲለው ይሰማዋል፡፡ ልጅቷን ወዷታል😍❤️፡፡ ግን ደግሞ እሱ እንኳንስ
እንዲህ በአጋጣሚ አይቶ የወደዳትን የማያውቃትን ልጅ ይቅርና፣ በወጉ
የተዋወቃቸው ልጆች አጠገብም ዓይናፋር ብጤ ነው፡፡
እና የልቡን በልቡ ይዞ በእፍረት እንዳቀረቀረ የልጅቷን ፊት ሰረቅ አድርጎ
እየተመለከተ ወደ ልጅቷ ቀርቦ ሲዲ እንደሚፈልግ ተናገረ፡፡
ልጅቱ በፈገግታ ተቀበለችው፡፡
“ሲዲውን ልጠቅልልህ…” አለችው፡፡
“እሺ !” ከእሷጋ የሚያቆየውን የትኛውንም አጋጣሚ እጅጉን ይፈልገዋል፡፡ ልጅቷ
ሲዲውን አሽጋ ሰጠችው፡፡
ሂሳቡን ከፍሎ ሊወጣ ነው፡፡ ቢችል ትንሽ ጊዜ አብሯት ለመቆየት አንድ
ተጨማሪ ዕቃ ቢገዛ ተመኘ፡፡ ግን ደግሞ ሌላ ሊገዛ የሚፈልገው ዕቃም ሆነ
አንዳችም ተጨማሪ ሳንቲም ኪሱ ውስጥ የለም፡፡
እናም ሳይወድ በግድ የሲዲውን ጥቅል በእጁ የልጅቷን ፍቅር በልቡ እንደያዘ
ወደ ቤቱ አመራ፡፡ ከዛን ቀን በኋላ የልጁ የዘወትር ተግባር የዐይን ረሃብ
የሆነችበትን ይህቺን ልጅ ለማየት ወደ ሱፐር ማርኬቱ እየሄደ ሲዲ መግዛት
ሆነ፡፡
በቃ ሁልጊዜ እንደዚሁ ነው፡፡
ማለዳውን የልጅቷን ፍቅር እያሰበ፣ መውደዱን እሽሩሩ ሲል አርፍዶ፤ የዐይን
ረሃቡ ሲበረታበት የአንድ ሲዲ መግዢያ ጥቂት ብሮች ከየትም ፈላልጎ ወደ
ሱፐር ማርኬቱ ይፈጥናል፡፡
አዎን፣ እዛ ሱፐርማርኬት ውስጥ ያ ምትሃተኛ ፊት በፈገግታ ተጥለቅልቆ
ያገኘዋል፡፡ ይሄ ሲታሰበው እንዳች ፍርሃት የተቀላቀለበት ለሰስ ያለ ደስታ
በውስጡ ሲያልፍ ተሰማው፡፡ ሱፐር ማርኬቱ ሲደርስ አንድ ደቂቃ እንኳ
የማይሞላው የዘወትር፣ የተለመደው የሲዲ ግብይት ይካሄዳል፡፡
“ሲዲ ፈልጌ ነበር” ይላል፡፡
“ልጠቅልልልህ … ?” ትለዋለች፡፡
“አዎ”
ሲዲውን ይዛ ወደ አንድ ጥግ ትሄድና የሲዲውን ጥቅል አምጥታ ትሰጠዋለች፡፡
ሂሳቡን ይከፍላል፡፡
ይወጣል፡፡
በቃ ይሄው ነው የዘወትር የዐይን ረሃቡ ማስታገሻ፡፡ በዚህች ቅፅበት በስርቆሽ
ያየውን መልክ ቀኑን ሙሉ በናፍቆት ሲያመነዥገው ይውልና፣
ደግሞ ነገ ሲመጣ…
በዚህ መልኩ አንዳችም የልቡን ስሜት የሚገልፅ ቃል ሳይተነፍስ፣ ፍቅሩን
ሳይገልፅላት፣ ሰርክ ሲዲ እንዳስጠቀለለ ወራት ተቆጠሩ፡፡
ልጁ ከቀን ቀን ትካዜና ብቸኝነት አመጣ፡፡ ጉዳዩ ግራ ያጋባት እጅጉን
የሚቀራረቡት የአክስቱ ልጅ ‘ምን ሆነሃል ?’ ስትል ጠየቀችው፡፡ ብዙም
ሳያንገራግር ጉዳዩን አጫወታት፡፡ ሳይፈራ ቀርቦ እንዲያናግራትና የልቡን
እንዲነግራት አደፋፈረችው፡፡
ግን የልጁ ዓይናፋርነት በየት በኩል ! እንኳንስ ቀርቦ ማፍቀሩን ሊገልፅላት
ይቅርና እንዲሁም ራሱ እንደ አንዳች ነው የሚፈራት፡፡
በስተመጨረሻ ግን ከብዙ ውትወታ በኋላ ሲዲውን ገዝቶ ሲወጣ የስልክ
ቁጥሩን አስቀምጦላት እንዲወጣ የአክስቱ ልጅ ባቀረበችለት ሀሳብ ተስማማ፡፡
‘አዎን፣ ቢያንስ ልጅቷ አንዳች ስሜት ላንተ ካላት መደወሏ አይቀርም፡፡ ያኔ
ልታወሩ ትችላላችሁ፡፡ ከፈለግክ የልብህን ትነግራታለህ፡፡ አለበለዚያ
መቀራረባችሁም ቢሆን አንድ ነገር ነው፡፡ ቀስ በቀስ የሚሆነው ይታያል፡፡
ካልደወለችልህም ይቀራል’ አለችው፡፡
ተስማማ፡፡
በቀጣዩ ቀን እንደተለመደው ሲዲ እንደሚፈልግ ተናገረ፡፡
“ልጠቅልልህ…” አለችው፡፡
አዎን !
ሲዲውን ልትጠቀልልለት ዞር እንዳለች ቀስ ብሎ የስልክ ቁጥሩ ያለበትን
ብጣሽ ወረቀት አስቀመጠላት፡፡
የተጠቀለለውን ሲዲ ይዛ ስትመጣ ሂሳቡን ከፍሎ በፍጥነት ሱፐርማርኬቱን
ጥሎ ወጣ፡፡
ከሱፐርማርኬቱ እንደወጣ ባከናወነው ድርጊት ረክቶ እፎይ አለ፡፡ ካልደወለችለት
ግን ከእንግዲህ ዓይኗን የሚያይበት ድፍረት እንደማይኖረው ተገነዘበ፡፡ ሀዘን
ተጫጫነው፡፡ ትካዜው በረታ፡፡ ባትደውልልኝስ ሲል ፈራ፡፡ አዎን፣ በዕርግጥም
እኔ ተራ ደምበኛ ነኝ እንጂ ምኗ ነኝ ሲል አሰበ፡፡ እና ምን ልሁን ብላ ነው
የምትደውልልኝ ! ፈፅሞ አታደርገውም፡፡ አትደውልልኝም ሲል ደመደመ፡፡
አለመደወልም ብቻም አይደል - ጉዳዩ ከዚህም የሚከፋበት ሁኔታ አለ፡፡ ጉዳዩን
የሱፐርማርኬቱ ሰራተኞች ሲያውቁበት፣ ‘ውይ ለካንስ ለዚህ ነውና በየቀኑ ሲዲ
የሚገዛው’ እያሉ ሲሳለቁበት ታየው፡፡
አፈረ፡፡
በቀን አንዴ ሳይሳለማት የማይውለውን የልቡን ንግሥት መቼም ቢሆን ላያያት
ነው ማለት ነው፡፡ ይሄ ሲታሰበው እዛው በዛው ናፍቆቱ በርትቶ ሀዘን
ተቀራመተው፡፡ በሀሳብ እንደተዋጠ ደመነፍሱን ወደ አውራ ጎዳናው ወጣ፡፡
በቀጣዩ ቀን ረፋድ ላይ የልጁ ቤት ስልክ ጮኸ፡፡ ደዋይዋ ተፈቃሪዋ ልጅ ነች፡፡
ትላንት ልጁ በሰጣት ስልክ መደወሏ ነው፡፡
የባለታሪኩ የአክስት ልጅ ስልኩን አነሳች፡፡ በስልኩ በዛኛው ጫፍ ያለው
ልስልስ ያለ የሴት ድምፅ ልጁን እንደሚፈልግ ተናገረ፡፡
ምላሹ ግን ልብ ሰባሪ አሳዛኝ ዜና ሆነ፡፡
ልጁ በትላንትናው ዕለት በደረሰበት የመኪና አደጋ ለዘለዓለሙ አሸልቧል፡፡
ሞቷል…፡፡ ትላንት ሀዘን እንደተጫነው፣ በሀሳብ ተውጦ መንገድ ሲያቋርጥ ነበር
የመኪና አደጋው የደረሰበት፡፡
ልጅቷ ጆሮዋን ማመን አልቻለችም፡፡ አንዳች ክፉ ቀልድ ነው የመሰላት፡፡
ከልጅቷጋ የነበረውን ግንኙነት ጠንቅቃ የምታውቀው የልጁ የአክስት ልጅ
ልጅቷን ወደ ቤታቸው ጠራቻት፡፡
አንድም ሀዘንን መካፈል ነው፡፡ አንድም…
ልጅቷ እንደመጣች ሀዘን እንደደቆሳቸው ጥቂት ተጨዋወቱ፡፡ አልበሙን ከፍታ
አሳየቻት፡፡ ሁለት ልቦቻቸው የተሰበሩ እንስቶች! በስተመጨረሻ የልጁን ትዝታ
ለማደስ፣ ለዘለዓለም ያሸለበውን ልጅ ለማስታወስ ወደ ልጁ መኝታ ቤት ይዛት
ሄደች፡፡ ‘ይሄ መኝታ ክፍሉ ነበር፡፡ ሁልጊዜ እዚህ መስኮቱጋ ነበር ተቀምጦ
የሚያነበው እዚህጋ ደግሞ…’ እያለች አስጎበኘቻትና፣ በስተመጨረሻ፣
ቁምሳጥኑን ስትከፍት … ስፍር ቁጥር የሌለው የታሸጉ ሲዲዎች ክምር
ፊታቸው ተገጠገጠ፡፡ ልጅቷ በድንጋጤ ክው አለች፡፡ እነዛ በየቀኑ እየመጣ
የሚገዛቸው ሲዲዎች መሆናቸው ነው፡፡ ሁሉም እንደታሸጉ ናቸው፡፡ ከመሃከላቸው
አንዱም ከታሸገበት አልተፈታም፡፡
ልጅቷ በቀስታ አንዱን የታሸገ ሲዲ አንስታ እሽጉን ስትፈታ ከውስጡ አንድ
ብጣሽ ወረቀት ወደቀ፡፡ ወረቀቱ ላይ እንዲህ የሚል ተጽፏል፡፡ ‘…አንተ ልጅ…
በጣም ደስ ትለኛለህ❤️….ላገኝህ እፈልጋለሁ፡፡ በዚህ ስልክ ቁጥር ልትደውልልኝ
ትችላለህ…..?’ ይልና ከሥሩ ስልክ ቁጥር ሰፍሯል፡፡ ሲዲውን ስትጠቀልልለት
ይሄን ማስታወሻ ፅፋ ውስጡ ያስገባችለት ልጅቷ ራሷው ነች፡፡
የሲዲውን እሽግ ከፍቶ ማስታወሻውን እንዳላየው ስታውቅ እንባዋ ፊቷን
አጠበው፡፡ አሁንም ሌላ የሲዲ እሽግ አንስታ ከፈተች፡፡ አሁንም ሌላ
ማስታወሻ…
‘…እባክህን አንተ ልጅ…ላገኝህ እፈልጋለሁ፡፡ በዚህ ስልክ ቁጥር ደውልልኝ’
እንባዋ ፊቷን እያጠበው የሲዲዎቹን ጥቅል አንድ በአንድ ፈታቻቸው፡፡
ሁሉም የልጅቷን መልዕክት ይዘዋል፡፡
እባክህን አንተ ልጅ…በጣም ደስ ትለኛለህ❤️…ላናግርህ እፈልጋለሁ፡፡ በዚህ ስልክ
ቁጥር ደውልልኝ
እንባዋ አይኗን ጋረደው፡፡
አነባች፡፡
😭😭😭😢😭😭😭
የሀዘኔ መጨረሻ

ክፍል 21 የመጨረሻው ክፍል

የሰርጋችንን ቀን መቼም ልረሳው አልችልም፡፡ ሰርጉ ከተጠናቀቀ በኀላ ወደነ ብሩኬ የምንሄድ መስሎኝ ነበር፡፡ ነገር ግን ብሩኬ "ሰሊዬ ዛሬ አንድ ቦታ እወስድሻለው ቦታውን ከምልሽ በላይ ነው የምትወጂው" አለኝ፡፡ አቶ ሄኖክ ፈገግ ብለው አንገታቸውን ከፍ ከፍ አደረጉ፡፡ ግራ በመጋባት ስሜት ውስጥ ሆኜ ከብሩኬ ጋር ወደተዘጋጀልን መኪና ገባን፡፡ ወ/ሮ ኤልሳ አቶ ሄኖክና አቤል ወደቤት ሄድ፡፡

እኔና ብሩኬ መንገድ ላይ እየሄድን ብሩኬ መኪናውን ቆም አደረገው "ምነው ውዴ ለምን አቆምከው "ስል ጠየቅኩት እርሱም " ሰላሜ አንድ ሰርፕራይዝ አለሽ ስለዚ አይንሽን በዚ ሸፍኝው " ብሎ ቀይ ሪቫን ሰጠኝ፡፡ ፈገግ እያልኩኝ" ብሩኬ በጣም እየጓጓው ነው እኮ" አልኩት፡፡ "እመኚኝ ሰላሜ ትንሽ ብቻ ታገሺኝ" ብሎ ሪቫኑን አይኔ ላይ አስሮልኝ መንገዳችንን ቀጠልን፡፡ ከትንሽ ጉዞ በኀላ መኪናዋ ቆመች በችኮላ አይኔ ላይ ያለውን ሪቫን ልፈታው ስል "ቆይ ሰላሜ አንዴ " ብሎ አስቆመኝ፡፡ የመኪናውን በር ከፍቶ አሶረደ ኝ፡፡ እጄን ይዞ እየመራኝ ወደ ሆነ ቦታ ወሰደኝ፡፡ "አሁን ሰላሜ አይንሽን መክፈት ትችያለሽ " አለኝ፡፡ እየተጣደፍኩ ሪቫኑን ፈታሁት፡፡

አይኖቼን እንደገለጥኩኝ ያላሰብኩት ነገር ተከሰተ እራሴን መቆጣጠር አቅቶኝ ከአይኖቼ እንባ ዱብ ዱብ አለ፡፡ ብሩኬ ለኔ የሰጠኝ ነገር ከሚባለው በላይ የሚያስፈልገኝና የምወደውን ነገር ነበር.....

የበፊት ቤታችን የውሌ የሰሊ የኔ እና የአቤል እኔና አቤል ተወልደን ያደግንበት የተደሰትንበት ተጣልተን የተታረቅንበት ቤተሰብ ሆነን የኖርንበት ቤት ነበር፡፡ ቤቱ ሙሉ በሙሉ ባይሆንም ግን ድሮ እኛ ስንኖርንበት እንደነበረ ተደርጓል፡፡ የቤቱ ቀለም አንዳንድ እቃዎቹ በተለይ ሳሎኑ ፊት ለፊት ላይ የተሰቀለው የሙሌና የቤዚ ፎቶ የድሮ ትውስታዎችን ጫረብኝ፡፡

ዘወር ብዬ ብሩኬን አየሁት " ሰላሜ እኔ ወርቆች አልማዞች እንቁዎች ብሰጥሽ እንኳን ከዚኛው ቤት የበለጠ ደስተኛ ሊያደርግሽ አይችልም ነበር፡፡ ይሄ ቤት ላንቺ ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ አውቃለው ለዛም ነው ይሄን ያደረኩት አንቺ ከዚም በላይ ይገባሻል" ቃላቶች አጠሩኝ የተሰማኝን ስሜት ቃላት አጥቄለት በእንባዬ ገለፅኩት፡፡ ተንደርድሬ ብሩኬን አቀፍኩት፡፡ በሰጠኝ ስጦታ ደስተኛ መሆኔን ሲመለከት ከኔ ይበልጥ ደስተኛ ሆነ፡፡ በፍቅር መኖራችንንም ቀጠልን፡፡

ከወራቶች በኀላ የእርግዝና ወራቶቼን ጨርሼ የምታምር ሴት ልጅ ወለድኩኝ ስሟንም በምወዳት በእናቴ ስም ሰላም አልኳት፡፡ አቤልም እኛጋር መኖር ጀምሯል፡፡ ብሩኬ ሀይለኛ የቢዝነስ ሰው ሆኗል፡፡ አቶ ሄኖክና ወ/ሮ እልሳም እየመጡ ይጠይቁናል፡፡

ዛሬ እሁድ ጠዋት ነው ፀሀይዋ መንፈስን ታድሳለች፡፡ እኔ ብሩኬ ሰላም እና አቤል ቁርስ እየበላን ነው በኑሮዬ በጣም ደስተኛ ነክ ይሄ ነው የኔ ታሪክ የሀዘኔ መጨረሻ.........

........አለቀ..........

ውድ ቸከታታዬቼ ይህንን ታሪክ በተመስጦና በትዕግስት ስለተከታተላቹልኝ አመሰግናለው


Written by Samrawit Teshale
Forwarded from Julian Pictures 📸 (Julian)
Street photography
#ስራ_ፈገግታ_ጥንካሬ
   Julian Photography 📸
Join👇👇👇👇👇👇
https://hottg.com/Julian_photography
Forwarded from Julian Pictures 📸 (Julian)
Street photography
#አባትነት_ጥንካሬ
   Julian Photography 📸
Join👇👇👇👇👇👇
https://hottg.com/Julian_photography
Forwarded from Julian Pictures 📸 (Julian)
ምርጥ ምርጥ ፎቶዎችን ለመነሳት           👉👉👉@Juliiian  💛📸  

      Julian Photography 📸
Phone number 092 621 7259
https://hottg.com/Julian_photography
HTML Embed Code:
2024/04/29 08:53:53
Back to Top