አንድ ዮጊ ባቡር ላይ ይሳፈራል፡፡ ሶስተኛ ደረጃ ባለው የባቡር ፉርጎ ውስጥም ተቀመጠ፡፡ ከዛም የያዘውን ሳጥን ጭንቅላቱ ላይ አስቀመጠ፡፡ ተንቀሳቃሽ አልጋውንና የመኝታ ልብሶቹን ደግሞ ሳጥኑ ላይ ደረበ፡፡ በዚህ ላይ ደግሞ ዣንጥላውን ደርቦ አስቀመጠ፡፡ በዚህ ግዜ አብረውት የነበሩት መንገደኞች፡- “ምን እያደረግክ ነው? ጓዝህን ወለሉ ላይ አስቀምጠህ ለምን በምቾት አትቀመጥም?” ሲሉ በመገረም ጠየቁት፡፡ ዮጊውም፡-
“የገዛሁት ቲኬት ለኔ ብቻ ነው! ባቡሩ ላይ ተጨማሪ ሸክም መጫን ሰናይ ምግባር እንዳልሆነ አስባለሁ፡፡ ስለዚህ ሸክሙን ጭንትላቴ ላይ መጫኑ ተገቢ ነው፡፡
ሲል መለሰላቸው፡፡
ሰዎቹም፡- “አብደሃል እንዴ? ጓዝህን ጭንቅላትህ ላይ ብትሸክመውም የክብደቱ ጫና የሚያርፈው እኮ ባቡሩ ላይ ነው፡፡ ታዲያ አላስፈላጊ ሸክም ጭንቅላትህ ላይ ለምን ትጭናላህ? ወለሉ ላይ አስቀምጠውና ፈታ ብለህ ተቀመጥ፡፡” አሉት፡፡
ከዛም ዮጊው፡-" ባቡሩ ውስጥ ያሉት ሰዎች አላዋቂዎች እንደሆኑ አስቤ ነበር። አሁን ግን ብልህ መሆናቸውን ተረድቻለሁ።” አለ። ሰዎቹ ግን የተናገረው እንዳልገባቸው ገለፁለት።
ከዛም ዮጊው፡- "በህይወት ውስጥ ብዙ ሰዎች ለአምላክ ሊተውት የሚገባቸውን ሽክም በጭንቅላታቸው ተሸክመው አይቻለሁ፡ ፡ እያንዳንዱ ሰው መላው አፅናፈ ሊሸከማቸው የሚችለውን የስጋትና የጭንቀት ተራሮች ጭንቅላቱ ላይ ተሸክሞ አይቻለሁ፡፡ ትማሩ ይሆናል በሚል ነበር ጓዜን ጭንቅላቴ ላይ የጫንኩት፡፡ እናንተ ግን ብልሆች ናችሁ፡፡ ነገር ግን ብልህነታችን እዚህ የባቡር ፉርጐ ውስጥ ብቻ ነው፡፡ ሁላችንም በህይወታችን ባቡር ውስጥ ተሳፍረን እየተጓዝን ነው፡፡ በዛ ግን ሁሉንም ጓዞቻችንን የምንጭነው ጭንቅላታችን ላይ ነው፡፡ ” ሲል መለሰላቸው።
@zephilosophy
>>Click here to continue<<