Warning: mkdir(): No space left on device in /var/www/hottg/post.php on line 59

Warning: file_put_contents(aCache/aDaily/2025-07-22/post/Zephilosophy/--): Failed to open stream: No such file or directory in /var/www/hottg/post.php on line 72
አባ ይፍቱኝ @ፍልስፍና ለላቀ አስተሳሰብ Philosophy
TG Telegram Group & Channel
ፍልስፍና ለላቀ አስተሳሰብ Philosophy | United States America (US)
Create: Update:

አባ ይፍቱኝ
(በእወቀቱ ስዩም)

ሲኦል አለ ሲሉኝ፥ የለም ብየ ክጀ
የባልቴት ተረት ነው፥ በማለት ቀልጀ
አውቄ በድፍረት፥ በድያለሁና
ያንጹኝ በንስሐ፥ ያንሱኝ በቀኖና
ሲኦል ከነጭፍራው፥ በጉም ተሸፍኖ
እንዴት ሳላየው ኖርኩ፥ ካጠገቤ ሆኖ?

አባ ይፍቱኝ
ሰይጣን ብሎ ነገር፥ የተጭበረበረ
ዋዛ ነው ቧልት ነው፥ ብየ አስብ ነበረ
ይሄው እውነት ሆኖ፥ ዋዛና ተረቱ
ባይኔ በብረቱ
ዲያብሎስን አየሁት፥ በሸሚዝ ዘንጦ
እልፍ ግዳይ ጥሎ፥ ቸብቸቦ ጨብጦ

አባ
ልክ እንደ ብርሌ፥ አጥንት ሲከሰከስ
አባይን አዋሽን፥ የሚያስንቅ ደም ሲፈስ
ለምለም ፍጥረት ሁላ፥ ወደ አመድ ሲመለስ
ልክ እንደ ጧፍ ሐውልት፥ ምስኪኖች ሲጋዩ
ምድጃው ዳር ሆነው፥ ይሄንን እያዩ
ገሃነም ከላይ ነው፥ ብለው መሳትዎ
እርስዎ እንደፈቱኝ፥ እግዚሃር ይፍታዎ፡፡

@zephilosophy

አባ ይፍቱኝ
(በእወቀቱ ስዩም)

ሲኦል አለ ሲሉኝ፥ የለም ብየ ክጀ
የባልቴት ተረት ነው፥ በማለት ቀልጀ
አውቄ በድፍረት፥ በድያለሁና
ያንጹኝ በንስሐ፥ ያንሱኝ በቀኖና
ሲኦል ከነጭፍራው፥ በጉም ተሸፍኖ
እንዴት ሳላየው ኖርኩ፥ ካጠገቤ ሆኖ?

አባ ይፍቱኝ
ሰይጣን ብሎ ነገር፥ የተጭበረበረ
ዋዛ ነው ቧልት ነው፥ ብየ አስብ ነበረ
ይሄው እውነት ሆኖ፥ ዋዛና ተረቱ
ባይኔ በብረቱ
ዲያብሎስን አየሁት፥ በሸሚዝ ዘንጦ
እልፍ ግዳይ ጥሎ፥ ቸብቸቦ ጨብጦ

አባ
ልክ እንደ ብርሌ፥ አጥንት ሲከሰከስ
አባይን አዋሽን፥ የሚያስንቅ ደም ሲፈስ
ለምለም ፍጥረት ሁላ፥ ወደ አመድ ሲመለስ
ልክ እንደ ጧፍ ሐውልት፥ ምስኪኖች ሲጋዩ
ምድጃው ዳር ሆነው፥ ይሄንን እያዩ
ገሃነም ከላይ ነው፥ ብለው መሳትዎ
እርስዎ እንደፈቱኝ፥ እግዚሃር ይፍታዎ፡፡

@zephilosophy
😢4540👍20🔥5👏5😁3


>>Click here to continue<<

ፍልስፍና ለላቀ አስተሳሰብ Philosophy




Share with your best friend
VIEW MORE

United States America Popular Telegram Group (US)


Warning: Undefined array key 3 in /var/www/hottg/function.php on line 115

Fatal error: Uncaught mysqli_sql_exception: Too many connections in /var/www/db.php:16 Stack trace: #0 /var/www/db.php(16): mysqli_connect() #1 /var/www/hottg/function.php(212): db() #2 /var/www/hottg/function.php(115): select() #3 /var/www/hottg/post.php(351): daCache() #4 /var/www/hottg/route.php(63): include_once('...') #5 {main} thrown in /var/www/db.php on line 16