TG Telegram Group Link
Channel: ርጢን ሚዲያ ( Ritin Media )
Back to Bottom
“ብዙ እናቶች ስቃይ ካለበት የወሊድ ሰዓት በኋላ ልጆቻቸውን ሌሎች እንዲመግቡላቸው ለእንግዶች ይሰጣሉ። ክርስቶስ ግን እኛ ልጆቹን በብዙ መከራ እና ስቃይ በመስቀል ላይ ከወለደን በኋላ ሌሎች እስኪመገቡን ድረስ አይተወንም። በገዛ ሥጋ እና ደሙ እየመገበ ራሱ ያሳድገናል። በዚህ ሁሉ መንገድም ከራሱ ጋር አንድ ያደርገናል”

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ (አፈ በረከት-በዓለ ፍልሠቱ)
† እንኳን ለሐዋርያው ቅዱስ አጋቦስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †

††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††

††† ቅዱስ አጋቦስ ሐዋርያ †††

††† ከ72ቱ አርድዕት አንዱ የሆነው ቅዱሱ ሐዋርያ ሃብተ-ትንቢት የተሠጠውና በዘመነ ሐዋርያት (በቀላውዴዎስ ቄሳር ጊዜ) በዓለም ላይ ከባድ ረሃብ እንደሚሆን ትንቢት የተናገረና በርካታ ክርስቲያኖችን ከረሃብና ከሞት የታደገ ትልቅ ሐዋርያ ነው:: (ሐዋ. 11:27)

በቅዱስ ጳውሎስ ላይ የሚደርሰውን መከራ በመናገሩም "ሐዋርያ ትንቢት" ተብሏል:: በአገልግሎቱ ከአይሁድና ከአረማውያን ብዙዎችን ወደ ክርስትና በመሳቡ የተበሳጩ አይሁድም በዚህች ቀን ገድለውታል:: በተቀደሰ ሥጋው (መቃብሩ) ላይ ብርሃን ሲወርድ ያየች አይሁዳዊት ሴትም በክርስቶስ አምና ተሰውታለች::

††† የአባታችን በረከት ይደርብን::

የ††† ካቲት 4 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ አጋቦስ ነቢይ: ሐዋርያና ሰማዕት
2.አባ ዘካርያስ ትሩፈ ምግባር

††† ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ ዮሐንስ ሐዋርያ ወልደ ነጎድጓድ
2.ቅዱስ እንድርያስ ሐዋርያ
3.ቅድስት ሶፊያ ሰማዕት
4.ቅዱስ ዮሐንስ ዘሐራቅሊ

††† "በዚያም ወራት ነቢያት ከኢየሩሳሌም ወደ አንጾኪያ ወረዱ:: ከእነርሱም አጋቦስ የሚሉት አንድ ሰው ተነስቶ በዓለም ሁሉ ታላቅ ራብ ሊሆን እንዳለው በመንፈስ አመለከተ:: ይህም በቀላውዴዎስ ቄሣር ዘመን ሆነ::
ደቀ መዛሙርትም እያንዳንዳቸው: እንደ ችሎታቸው መጠን አዋጥተው በይሁዳ ለሚኖሩት ወንድሞች እርዳታን ይልኩ ዘንድ ወሰኑ::
እንዲህም ደግሞ አደረጉ:: በበርናባስና በሳውልም እጅ ወደ ሽማግሌዎቹ ሰደዱት::" †††
(ሐዋ. ፲፩፥፳፯)

††† "ስለ እኛ ትጸልዩ ዘንድ ይገባቹሃል: ለሁሉ መልካም ነገርን እንደምትወዱና እንደምትሹ እናምናለን::" †††
(ዕብ. ፲፫፥፲፰)

††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††

Dn Yordanos Abebe
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን †

††† እንኩዋን ለእናታችን "ቅድስት ማርያም እንተ ዕፍረት" እና "ቅዱስ አቡሊዲስ" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ †††

+*" ቅድስት ማርያም "*+

=>ቅድስት ማርያም እንተ ዕፍረት ቅዱስ መጽሐፍ እንደሚለን በስምዖን ቤት የመድኃኔ ዓለምን እግር በእንባዋ አጥባለች:: በፀጉሯም አብሳ የ300 ብር ሽቱ ቀብታዋለች:: ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም የቀደመ ኀጢአቷን ይቅር ብሎ ከ36ቱ ቅዱሳት አንስት ደምሯታል:: (ሉቃ. 7:36-50)

+ስለዚህች ቅድስት ሙሉ ታሪክ:-
1.ትርጉዋሜ ወንጌልን
2.ተአምረ ኢየሱስን
3.ስንክሳርን እና
4.መጽሐፈ ግንዘትን በማንበብ ማግኘት ይቻላል::

+እንት ዕፍረት (ባለ ሽቱዋ ማለት ነው) ማርያም መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሚያስተምርበት ዘመን (በዘመነ ስብከቱ) የነበረችና ይህ ቀረሽ የማይሏት ቆንጆ ሴት ነበረች:: ግን መልክ የመልካም ነገሮች ምንጭ ሲሆን አይታይም::

+በመልካቸው ማማር የጠፉና ያጠፉ ብዙ ሴቶችን ዓለማችን አስተናግዳለች:: ከክሊዎፓትራ እስከ ዘመናችን "ሞዴል" ነን ባዮች : እግዚአብሔር የሰጣቸውን ጸጋ የሰይጣን መደሰቻ : የገሃነም መንገድ አድርገውት ማየት (መስማት) እጅግ ያሳዝናል::

+በአንጻሩ ደግሞ ብዙዎችን ያስደመመ መልካቸውን ንቀው : ሰማያዊ ሙሽርነትን የመረጡትን ቅዱሳቱን:- አርሴማን : ቴክላን : ጤቅላን : መሪናን : ጣጡስን : ሔራኒን : ኢራኒን : አትናስያን : ሶፍያን : ኢላርያን . . . ስናስብ ደስ ይለናል:: ዛሬም ጌታ በሚያውቀው ብዙ እናቶቻችን (እህቶቻችንም) ተመሳሳዩን በጐ ጐዳና መርጠው እየተጉዋዙ መሆኑን እናውቃለን::

+ቅድስት ማርያምም ከፈጣሪዋ በተሰጣት ቁንጅና ክፋትን ትሠራ ዘንድ ሰይጣን ሲያገብራት "እሺ" ብላ የእሱ ወጥመድ ልትሆን ተራመደች:: ለዘመናትም ዓይነ-ዘማ : ልበ-ስስ የሆኑ ወንዶችን ወደ ኃጢአት ጐዳና ማረከች::

+ለመልኩዋ ከነበራች ስስት የተነሳም ቶሎ ቶሎ ራሷን በመጽሔት (መስታውት ማለት ነው) ትመለከት ነበር:: መቼም አምላካችን ለሁሉም የመዳን ቀን ጥሪ አለውና (የሚያስተውለው ቢገኝ) ለማርያም ጥሪውን ላከላት:: ጥሪው ግን በስብከት : በመዝሙር : በመጽሐፍ . . . አልነበረም::

+እንዳስለመደች ውበቷን ለመመልከት መስታውት ፊት ቆማ የራሷን ጸጉር : ግንባር : ዐይን : አፍንጫ : ጥርስ . . . እየተመለከተች ተደመመች:: ወዲያው ግን ይህ አካል አፈር እንደሚበላው የሚያስብ ልቡና መንፈስ ቅዱስ አምጥቶባት በጣም አዘነች:: የመኖር ተስፋዋ እንዳይቆረጥ ደግሞ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ዜና ሰማች::

+መወሰን ነበረባትና ከሞት ወደ ሕይወት : ከጨለማ ወደ ብርሃን ልትሔድ ቆረጠች:: በአምላኩዋ ፊት የሚቀርቡም 3 ስጦታዎችን አዘጋጀች:: ሰይጣን ሊያጣት አልፈለገምና ወደ ክርስቶስ እንዳትደርስስ ብዙ መሰናክልን ፈጠረባት:: ግን ውሳኔዋ የእውነት ነበርና እያሳፈረችው ወደ አምላኩዋ ገሰገሰች::

+የስምዖን ዘለምጽ በረኞችም ሊያስቀሰሯት አልተቻላቸውም:: ወደ ውስጥ ዘልቃ የያዘችውን ሁሉ ለመድኃኒታችን ሰዋች::
1.ከውስጧ እንባዋን:
2.ከአካሏ ጸጉሯን:
3.ከንብረቷ ውድ የሆነውን ሽቱ አቀረበች::

+ብዙ ወዳለችና ብዙ ኃጢአቷ ተሠርዮ ቅድስት እናታችን ሆነች:: ብዙ አዝማናትን ከሐዋርያት ጋር አገልግላም በዚህች ቀን ዐርፋለች::

+*" ቅዱስ አቡሊዲስ መምህረ ኩሉ ዓለም "*+

=>የዓለም ሁሉ መምህር:
¤ባለ ብዙ ድርሳንና ተግሣጽ:
¤የቤተ ክርስቲያን ምሰሶ:
¤38 ሕግጋትን የደነገገ:
¤ስለ ቀናች እምነት የተጋደለ:
¤መራራ ሞትን በደስታ የተቀበለ:
¤የቀደመችዋ ሮም ሊቀ ዻዻሳት የነበረና:
¤ሐዋርያትን የመሰለ አባት ነው::

+በ2ኛው መቶ ክ/ዘመን መጨረሻ አካባቢ ያበራው ይሀን ኮከብ ካቶሊካውያን ክደውታል:: እነርሱ "አቡሊዲስ የሚባል ዻዻስ አልነበረም" ቢሉም ምክንያታቸው ግን ከሰይጣን ነው:: ሃይማኖታቸውን ከመለወጣቸው 250 ዓመታት በፊት ስለተናገረባቸውና አንድ ባሕርይን ስላስተማረ መሆኑን ዓለም ያውቃል::

+አባታችን ቅዱስ አቡሊዲስ የተገደለ የካቲት 5 ሲሆን የካቲት 6 ሥጋው የተገኘበት ነው::

=>አምላከ ቅዱሳን ከቅድስት ማርያም ንስሃዋን : ከአባ አቡሊዲስ ምሥጢረ ቅድስናውን ያድለን::

=>የካቲት 6 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅድስት ማርያም እንተ ዕፍረት
2.የዓለም ኁሉ መምሕር ቅዱስ አቡሊዲስ (ብዙ መንፈሳዊ ድርሳናትን የደረሰ ሊቀ ዻዻስና ሰማዕት)
3.ቅዱሳን አቡቂርና ዮሐንስ (ሰማዕታት)
4.ቅድስት አትናስያና 3ቱ ሰማዕታት ልጆቿ (ቴዎድራ : ቴዎፍናና ቴዎዶክስያ)

=>ወርኀዊ በዓላት
1.ቅድስት ደብረ ቁስቁዋም
2.አባታችን አዳምና እናታችን ሔዋን
3.አባታችን ኖኅና እናታችን ሐይከል
4.ቅዱስ ኤልያስ ነቢይ
5.ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሣርያ
6.ቅዱስ ዮሴፍ አረጋዊ
7.ቅድስት ሰሎሜ
8.አባ አርከ ሥሉስ
9.አባ ጽጌ ድንግል
10.ቅድስት አርሴማ ድንግል

=>ከበረከተ ቅዱሳን ይክፈለን::

=>+"+ . . . አንተ ራሴን ዘይት አልቀባኸኝም:: እርሷ ግን እግሬን ሽቱ ቀባች:: ስለዚህ እልሃለሁ : እጅግ ወዳለችና ብዙ ያለው ኃጢአቷ ተሰርዮላታል:: ጥቂት ግን የሚሰረይለት ጥቂት ይወዳል:: እርስዋንም:- 'ኃጢአትሽ ተሰርዮልሻል' አላት:: ከእርሱም ጋር በማዕድ ተቀምጠው የነበሩት በልባቸው:- 'ኃጢአትን እንኩዋ የሚያስተሰርይ ይህ ማነው' ይሉ ጀመር:: ሴቲቱንም:- 'እምነትሽ አድኖሻል: በሰላም ሒጂ' አላት:: +"+ (ሉቃ. 7:46)

<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን †

††† እንኩዋን ለእናታችን "ቅድስት ማርያም እንተ ዕፍረት" እና "ቅዱስ አቡሊዲስ" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ †††

+*" ቅድስት ማርያም "*+

=>ቅድስት ማርያም እንተ ዕፍረት ቅዱስ መጽሐፍ እንደሚለን በስምዖን ቤት የመድኃኔ ዓለምን እግር በእንባዋ አጥባለች:: በፀጉሯም አብሳ የ300 ብር ሽቱ ቀብታዋለች:: ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም የቀደመ ኀጢአቷን ይቅር ብሎ ከ36ቱ ቅዱሳት አንስት ደምሯታል:: (ሉቃ. 7:36-50)

+ስለዚህች ቅድስት ሙሉ ታሪክ:-
1.ትርጉዋሜ ወንጌልን
2.ተአምረ ኢየሱስን
3.ስንክሳርን እና
4.መጽሐፈ ግንዘትን በማንበብ ማግኘት ይቻላል::

+እንት ዕፍረት (ባለ ሽቱዋ ማለት ነው) ማርያም መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሚያስተምርበት ዘመን (በዘመነ ስብከቱ) የነበረችና ይህ ቀረሽ የማይሏት ቆንጆ ሴት ነበረች:: ግን መልክ የመልካም ነገሮች ምንጭ ሲሆን አይታይም::

+በመልካቸው ማማር የጠፉና ያጠፉ ብዙ ሴቶችን ዓለማችን አስተናግዳለች:: ከክሊዎፓትራ እስከ ዘመናችን "ሞዴል" ነን ባዮች : እግዚአብሔር የሰጣቸውን ጸጋ የሰይጣን መደሰቻ : የገሃነም መንገድ አድርገውት ማየት (መስማት) እጅግ ያሳዝናል::

+በአንጻሩ ደግሞ ብዙዎችን ያስደመመ መልካቸውን ንቀው : ሰማያዊ ሙሽርነትን የመረጡትን ቅዱሳቱን:- አርሴማን : ቴክላን : ጤቅላን : መሪናን : ጣጡስን : ሔራኒን : ኢራኒን : አትናስያን : ሶፍያን : ኢላርያን . . . ስናስብ ደስ ይለናል:: ዛሬም ጌታ በሚያውቀው ብዙ እናቶቻችን (እህቶቻችንም) ተመሳሳዩን በጐ ጐዳና መርጠው እየተጉዋዙ መሆኑን እናውቃለን::

+ቅድስት ማርያምም ከፈጣሪዋ በተሰጣት ቁንጅና ክፋትን ትሠራ ዘንድ ሰይጣን ሲያገብራት "እሺ" ብላ የእሱ ወጥመድ ልትሆን ተራመደች:: ለዘመናትም ዓይነ-ዘማ : ልበ-ስስ የሆኑ ወንዶችን ወደ ኃጢአት ጐዳና ማረከች::

+ለመልኩዋ ከነበራች ስስት የተነሳም ቶሎ ቶሎ ራሷን በመጽሔት (መስታውት ማለት ነው) ትመለከት ነበር:: መቼም አምላካችን ለሁሉም የመዳን ቀን ጥሪ አለውና (የሚያስተውለው ቢገኝ) ለማርያም ጥሪውን ላከላት:: ጥሪው ግን በስብከት : በመዝሙር : በመጽሐፍ . . . አልነበረም::

+እንዳስለመደች ውበቷን ለመመልከት መስታውት ፊት ቆማ የራሷን ጸጉር : ግንባር : ዐይን : አፍንጫ : ጥርስ . . . እየተመለከተች ተደመመች:: ወዲያው ግን ይህ አካል አፈር እንደሚበላው የሚያስብ ልቡና መንፈስ ቅዱስ አምጥቶባት በጣም አዘነች:: የመኖር ተስፋዋ እንዳይቆረጥ ደግሞ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ዜና ሰማች::

+መወሰን ነበረባትና ከሞት ወደ ሕይወት : ከጨለማ ወደ ብርሃን ልትሔድ ቆረጠች:: በአምላኩዋ ፊት የሚቀርቡም 3 ስጦታዎችን አዘጋጀች:: ሰይጣን ሊያጣት አልፈለገምና ወደ ክርስቶስ እንዳትደርስስ ብዙ መሰናክልን ፈጠረባት:: ግን ውሳኔዋ የእውነት ነበርና እያሳፈረችው ወደ አምላኩዋ ገሰገሰች::

+የስምዖን ዘለምጽ በረኞችም ሊያስቀሰሯት አልተቻላቸውም:: ወደ ውስጥ ዘልቃ የያዘችውን ሁሉ ለመድኃኒታችን ሰዋች::
1.ከውስጧ እንባዋን:
2.ከአካሏ ጸጉሯን:
3.ከንብረቷ ውድ የሆነውን ሽቱ አቀረበች::

+ብዙ ወዳለችና ብዙ ኃጢአቷ ተሠርዮ ቅድስት እናታችን ሆነች:: ብዙ አዝማናትን ከሐዋርያት ጋር አገልግላም በዚህች ቀን ዐርፋለች::

+*" ቅዱስ አቡሊዲስ መምህረ ኩሉ ዓለም "*+

=>የዓለም ሁሉ መምህር:
¤ባለ ብዙ ድርሳንና ተግሣጽ:
¤የቤተ ክርስቲያን ምሰሶ:
¤38 ሕግጋትን የደነገገ:
¤ስለ ቀናች እምነት የተጋደለ:
¤መራራ ሞትን በደስታ የተቀበለ:
¤የቀደመችዋ ሮም ሊቀ ዻዻሳት የነበረና:
¤ሐዋርያትን የመሰለ አባት ነው::

+በ2ኛው መቶ ክ/ዘመን መጨረሻ አካባቢ ያበራው ይሀን ኮከብ ካቶሊካውያን ክደውታል:: እነርሱ "አቡሊዲስ የሚባል ዻዻስ አልነበረም" ቢሉም ምክንያታቸው ግን ከሰይጣን ነው:: ሃይማኖታቸውን ከመለወጣቸው 250 ዓመታት በፊት ስለተናገረባቸውና አንድ ባሕርይን ስላስተማረ መሆኑን ዓለም ያውቃል::

+አባታችን ቅዱስ አቡሊዲስ የተገደለ የካቲት 5 ሲሆን የካቲት 6 ሥጋው የተገኘበት ነው::

=>አምላከ ቅዱሳን ከቅድስት ማርያም ንስሃዋን : ከአባ አቡሊዲስ ምሥጢረ ቅድስናውን ያድለን::

=>የካቲት 6 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅድስት ማርያም እንተ ዕፍረት
2.የዓለም ኁሉ መምሕር ቅዱስ አቡሊዲስ (ብዙ መንፈሳዊ ድርሳናትን የደረሰ ሊቀ ዻዻስና ሰማዕት)
3.ቅዱሳን አቡቂርና ዮሐንስ (ሰማዕታት)
4.ቅድስት አትናስያና 3ቱ ሰማዕታት ልጆቿ (ቴዎድራ : ቴዎፍናና ቴዎዶክስያ)

=>ወርኀዊ በዓላት
1.ቅድስት ደብረ ቁስቁዋም
2.አባታችን አዳምና እናታችን ሔዋን
3.አባታችን ኖኅና እናታችን ሐይከል
4.ቅዱስ ኤልያስ ነቢይ
5.ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሣርያ
6.ቅዱስ ዮሴፍ አረጋዊ
7.ቅድስት ሰሎሜ
8.አባ አርከ ሥሉስ
9.አባ ጽጌ ድንግል
10.ቅድስት አርሴማ ድንግል

=>ከበረከተ ቅዱሳን ይክፈለን::

=>+"+ . . . አንተ ራሴን ዘይት አልቀባኸኝም:: እርሷ ግን እግሬን ሽቱ ቀባች:: ስለዚህ እልሃለሁ : እጅግ ወዳለችና ብዙ ያለው ኃጢአቷ ተሰርዮላታል:: ጥቂት ግን የሚሰረይለት ጥቂት ይወዳል:: እርስዋንም:- 'ኃጢአትሽ ተሰርዮልሻል' አላት:: ከእርሱም ጋር በማዕድ ተቀምጠው የነበሩት በልባቸው:- 'ኃጢአትን እንኩዋ የሚያስተሰርይ ይህ ማነው' ይሉ ጀመር:: ሴቲቱንም:- 'እምነትሽ አድኖሻል: በሰላም ሒጂ' አላት:: +"+ (ሉቃ. 7:46)

<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>
የእግዚአብሔር_ፈቃድ_እንዴት_ይታወቃል.pdf
275.1 KB
1. የእግዚአብሔር ፈቃድ (ፈቃደ እግዚአብሔር) ምንድን ነው?

2. የእግዚአብሔርን ፈቃድ የምናውቀው እንዴት ነው?

3. በፈቃደ እግዚአብሔር ውስጥ የእግዚአብሔርንና የእኛን ድርሻ እንዴት መለየት እንችላለን?

4. በሕይወታችን የሚገጥመንን ማንኛውንም ነገር፤ መልካምም ሆነ ክፉ፤ የእግዚአብሔር ፈቃድ ነው ማለት እንችላለን ወይ?

5. በፈቃደ እግዚአብሔር ዙሪያ ሊስተዋሉ የሚገባቸው አንዳንድ መሠረታዊ ነጥቦች

በዲያቆን ያረጋል አበጋዝ
የክርስቶስ ማዳን እና የቅዱሳን ምልጃ

ሰው መድኅን ክርስቶስ ላይ ያለው መረዳት እምነቱን እና በዓለም ላይ ያለውን አኗኗር ይወስነዋል፡፡ የክርስቶስም ማዳን ዓለም ሳይፈጠር በልበ ሥላሴ የታሰበ እና የተመከረ የዘለዓለማዊ ፍቅር አምላካዊ ሥራ ነው፡፡ ሰው የተፈጠረውም በእግዚአብሔር ምሳሌ በመሆኑ፤ በዚህ አምላካዊ የማዳን ሥራ ላይም በጸጋ በመሳተፍ አምላኩን እየመሰለ ይኖራል፡፡ ልዑል እግዚአብሔር ሰውን ለማዳን እንደሚወድ (እንደሚፈቅድ)፤ በእርሱ አምሳል የተፈጠረውም ሰው እንዲሁ ሌላው እንዲድን ይወዳል (ይጓጓል)፡፡ በቅድስና ከእግዚአብሔር ይሳተፋል፡፡ ያለ ፍቅር ቅድስና የለምና፡፡ በዚያውም ሰው መሆኑን አጽንቶ በጸጋ እግዚአብሔር ይጠብቃል፡፡ አሁን እያሰብን ያለነው ቅዱሳት መጻሕፍት ስለሚናገሩለት ህያው ሰው (ማቴ 8፡ 22)፡፡ አሁን እያሰብን ያለነው ስለ እውነተኞቹ ሰዎች፤ ስለ ቅዱሳን ነው፡፡ ሰው መሆን እግዚእብሔርን መምሰል ነው ያልነው፤ በእርሱ የማዳን ሥራ ውስጥም በጸጋ መሳተፍን የሚያጠቃልል ነው፡፡ የድኅነት ምክንያት መሆን፤ ፍቅርና ትሕትናን በዓለም ላይ ማስፋት፤ ክፋትን መታገል እና ሌሎችም ተሳትፎው ምን እንደሆነ የሚያመለክቱ ናቸው፡፡ እኒህ ሁሉ ሰው ብቻውን የሚያደርጋቸው አይደሉም፤ በእግዚአብሔር ጸጋ እና ረድኤት ያደርጋቸዋል እንጂ፡፡ ሰው መውደድን ይወዳል፤ መፍቀድን ይፈቅዳል፤ እግዚአብሔር ማዳኑን ያደርጋል፡፡

የቅዱሳን ምልጃ በክርስቶስ አካል ውስጥ የሚደረግ የአባላት (የብልቶች) ትክክለኛ ሥራ ነው፡፡ የአካል ክፍሎች በትክክል ለተፈጠሩበት ዓላማ ሲሠሩ ማለታችን ነው፡፡ ብልቶች ሳይነጣጠሉ በሚሠሩት ሥራ አንዱ አካል በትክክል ይኖራል፡፡ እኒህን ጉዳዮች ማስተዋል የክርስቶስን ማዳን እና የቅዱሳንን ምልጃ ግንኙነት ለመረዳት ይጠቅማል፡፡ የክርስቶስ ማዳን እና የቅዱሳን ምልጃ ከሁለት አንዱን እንድንመርጥ የሚያስገድዱን፡ እንደ ሁለት ትይዩ መስመሮች (መንገዶች) አይደሉም፡፡ ከኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ውጪ ያሉ ሰዎች ይህን "የትይዩ መስመር አስተሳሰብ ሞዴል" ጥቂት ለማይባሉ ኦርቶዶክሳውያን ያጋቡ ይመስላል፡፡ በዚህ ምክንያት “ስለ ቅዱሳን ማስተማር ክርስቶስን ማደብዘዝ አይሆንም ወይ?”፤ “ሰው የሚድነው በክርስቶስ ቤዛነት ነው ወይስ በቅዱሳን ምልጃ?” … እና የመሳሰሉት ለሰዎች መልስ የሚሹ ዋና ጥያቄዎች ሆኑ፡፡ ነገር ግን “የአስተሳሰቡን መንገድ” ጥቂት እንመርምረው፡፡ የመድኅን ክርስቶስ ማዳን እና እርሱን የሚመስሉት ቅዱሳን ምልጃ “ወይስ” በሚል በትይዩ እና በአማራጭ የሚታሰብ ጉዳይ ነውን? ቅዱስ ወንጌል ከዚህ የተለየ እሳቤ አለው፡፡ ጌታ ደቀ መዛሙርቱን ሲሰበስብ እያንዳንዱን “ተከተለኝ” እያለ ወደ መንግሥቱ ወንጌል ጠርቷቸዋል (ዮሐ 1፡ 44)(ዮሐ 21፡ 19)(ማር 2፡ 14)(ማር 10፡ 21)፡፡ ለጊዜው በእግር ተከተለኝ ማለቱ ሲሆን፤ ፍጻሜው ደግሞ በግብር (በሥራ) ምሰለኝ ማለቱ ነው፡፡ መንገዱ እርሱ ነው፤ መንገዱንም የሚመራ መርቶም ወደ አባቱም መንግሥት የሚያስገባም እርሱ ነው፡፡ እርሱን የተከተሉ ቅዱሳን ከእርሱ ኋላ ናቸው እንጂ ከእርሱ ትይዩ አይደሉም፡፡ እርሱ በአምላካዊ ሥልጣኑ የሚሠራውን እነርሱ በጸጋ እየሰሩ፤ እርሱን በሥራቸው እየመሰሉት ከኋለው እስከማታልፍ መንግሥቱ ይከተሉታል (ፍጻሜ የሌለው እስከ እንደሆነ ልብ ይሏል)፡፡ እርሱን እየተከተሉት የሚፈጽሙት ምልጃ በመንገዱ (በሃይማኖት) ውስጥ ላሉ ለንስሐ እና ቅድሳቱ ሁሉ መቀበያ ምክንያት ነው፡፡ ከክርስቶስ ማዳን ጋር የሚተባበር ነው፡፡ ጌታ ተከተሉኝ ብሎ ደቀ መዛሙርቱን ካስከተለባት ከአንዲቱ መንገድ በበደል የወጣውን በምልጃ ምክንያት ወደ ራሱ ማዳን ይመልሰዋል፡፡ ለዚህም በቸርነቱ ብዛት ቃልኪዳንን ወደ እርሱ ለቀረቡት (ለቅዱሳን) ቃል ኪዳንን ይሰጣል፡፡ በበደል የራቀው በቅዱሳን ምልጃ ሲመለስ፤ ዐመጸኛው ዲያብሎስ ያፍራል፤ በቅዱሳን ዘንድ ደስታ ይሆናል፤ እግዚአብሔር ይህን ሁሉ ስለፈቀደ (በቸርነቱ) ስላደረገ ይመሰገናል፤ በዚህም ሕይወት ይበዛል፤ ሞት ይሰደዳል (ይጠፋል)፡፡
የእግዚአብሔር_ፈቃድ_እንዴት_ይታወቃል.pdf
275.1 KB
1. የእግዚአብሔር ፈቃድ (ፈቃደ እግዚአብሔር) ምንድን ነው?

2. የእግዚአብሔርን ፈቃድ የምናውቀው እንዴት ነው?

3. በፈቃደ እግዚአብሔር ውስጥ የእግዚአብሔርንና የእኛን ድርሻ እንዴት መለየት እንችላለን?

4. በሕይወታችን የሚገጥመንን ማንኛውንም ነገር፤ መልካምም ሆነ ክፉ፤ የእግዚአብሔር ፈቃድ ነው ማለት እንችላለን ወይ?

5. በፈቃደ እግዚአብሔር ዙሪያ ሊስተዋሉ የሚገባቸው አንዳንድ መሠረታዊ ነጥቦች

በዲያቆን ያረጋል አበጋዝ
የክርስቶስ ማዳን እና የቅዱሳን ምልጃ

ሰው መድኅን ክርስቶስ ላይ ያለው መረዳት እምነቱን እና በዓለም ላይ ያለውን አኗኗር ይወስነዋል፡፡ የክርስቶስም ማዳን ዓለም ሳይፈጠር በልበ ሥላሴ የታሰበ እና የተመከረ የዘለዓለማዊ ፍቅር አምላካዊ ሥራ ነው፡፡ ሰው የተፈጠረውም በእግዚአብሔር ምሳሌ በመሆኑ፤ በዚህ አምላካዊ የማዳን ሥራ ላይም በጸጋ በመሳተፍ አምላኩን እየመሰለ ይኖራል፡፡ ልዑል እግዚአብሔር ሰውን ለማዳን እንደሚወድ (እንደሚፈቅድ)፤ በእርሱ አምሳል የተፈጠረውም ሰው እንዲሁ ሌላው እንዲድን ይወዳል (ይጓጓል)፡፡ በቅድስና ከእግዚአብሔር ይሳተፋል፡፡ ያለ ፍቅር ቅድስና የለምና፡፡ በዚያውም ሰው መሆኑን አጽንቶ በጸጋ እግዚአብሔር ይጠብቃል፡፡ አሁን እያሰብን ያለነው ቅዱሳት መጻሕፍት ስለሚናገሩለት ህያው ሰው (ማቴ 8፡ 22)፡፡ አሁን እያሰብን ያለነው ስለ እውነተኞቹ ሰዎች፤ ስለ ቅዱሳን ነው፡፡ ሰው መሆን እግዚእብሔርን መምሰል ነው ያልነው፤ በእርሱ የማዳን ሥራ ውስጥም በጸጋ መሳተፍን የሚያጠቃልል ነው፡፡ የድኅነት ምክንያት መሆን፤ ፍቅርና ትሕትናን በዓለም ላይ ማስፋት፤ ክፋትን መታገል እና ሌሎችም ተሳትፎው ምን እንደሆነ የሚያመለክቱ ናቸው፡፡ እኒህ ሁሉ ሰው ብቻውን የሚያደርጋቸው አይደሉም፤ በእግዚአብሔር ጸጋ እና ረድኤት ያደርጋቸዋል እንጂ፡፡ ሰው መውደድን ይወዳል፤ መፍቀድን ይፈቅዳል፤ እግዚአብሔር ማዳኑን ያደርጋል፡፡

የቅዱሳን ምልጃ በክርስቶስ አካል ውስጥ የሚደረግ የአባላት (የብልቶች) ትክክለኛ ሥራ ነው፡፡ የአካል ክፍሎች በትክክል ለተፈጠሩበት ዓላማ ሲሠሩ ማለታችን ነው፡፡ ብልቶች ሳይነጣጠሉ በሚሠሩት ሥራ አንዱ አካል በትክክል ይኖራል፡፡ እኒህን ጉዳዮች ማስተዋል የክርስቶስን ማዳን እና የቅዱሳንን ምልጃ ግንኙነት ለመረዳት ይጠቅማል፡፡ የክርስቶስ ማዳን እና የቅዱሳን ምልጃ ከሁለት አንዱን እንድንመርጥ የሚያስገድዱን፡ እንደ ሁለት ትይዩ መስመሮች (መንገዶች) አይደሉም፡፡ ከኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ውጪ ያሉ ሰዎች ይህን "የትይዩ መስመር አስተሳሰብ ሞዴል" ጥቂት ለማይባሉ ኦርቶዶክሳውያን ያጋቡ ይመስላል፡፡ በዚህ ምክንያት “ስለ ቅዱሳን ማስተማር ክርስቶስን ማደብዘዝ አይሆንም ወይ?”፤ “ሰው የሚድነው በክርስቶስ ቤዛነት ነው ወይስ በቅዱሳን ምልጃ?” … እና የመሳሰሉት ለሰዎች መልስ የሚሹ ዋና ጥያቄዎች ሆኑ፡፡ ነገር ግን “የአስተሳሰቡን መንገድ” ጥቂት እንመርምረው፡፡ የመድኅን ክርስቶስ ማዳን እና እርሱን የሚመስሉት ቅዱሳን ምልጃ “ወይስ” በሚል በትይዩ እና በአማራጭ የሚታሰብ ጉዳይ ነውን? ቅዱስ ወንጌል ከዚህ የተለየ እሳቤ አለው፡፡ ጌታ ደቀ መዛሙርቱን ሲሰበስብ እያንዳንዱን “ተከተለኝ” እያለ ወደ መንግሥቱ ወንጌል ጠርቷቸዋል (ዮሐ 1፡ 44)(ዮሐ 21፡ 19)(ማር 2፡ 14)(ማር 10፡ 21)፡፡ ለጊዜው በእግር ተከተለኝ ማለቱ ሲሆን፤ ፍጻሜው ደግሞ በግብር (በሥራ) ምሰለኝ ማለቱ ነው፡፡ መንገዱ እርሱ ነው፤ መንገዱንም የሚመራ መርቶም ወደ አባቱም መንግሥት የሚያስገባም እርሱ ነው፡፡ እርሱን የተከተሉ ቅዱሳን ከእርሱ ኋላ ናቸው እንጂ ከእርሱ ትይዩ አይደሉም፡፡ እርሱ በአምላካዊ ሥልጣኑ የሚሠራውን እነርሱ በጸጋ እየሰሩ፤ እርሱን በሥራቸው እየመሰሉት ከኋለው እስከማታልፍ መንግሥቱ ይከተሉታል (ፍጻሜ የሌለው እስከ እንደሆነ ልብ ይሏል)፡፡ እርሱን እየተከተሉት የሚፈጽሙት ምልጃ በመንገዱ (በሃይማኖት) ውስጥ ላሉ ለንስሐ እና ቅድሳቱ ሁሉ መቀበያ ምክንያት ነው፡፡ ከክርስቶስ ማዳን ጋር የሚተባበር ነው፡፡ ጌታ ተከተሉኝ ብሎ ደቀ መዛሙርቱን ካስከተለባት ከአንዲቱ መንገድ በበደል የወጣውን በምልጃ ምክንያት ወደ ራሱ ማዳን ይመልሰዋል፡፡ ለዚህም በቸርነቱ ብዛት ቃልኪዳንን ወደ እርሱ ለቀረቡት (ለቅዱሳን) ቃል ኪዳንን ይሰጣል፡፡ በበደል የራቀው በቅዱሳን ምልጃ ሲመለስ፤ ዐመጸኛው ዲያብሎስ ያፍራል፤ በቅዱሳን ዘንድ ደስታ ይሆናል፤ እግዚአብሔር ይህን ሁሉ ስለፈቀደ (በቸርነቱ) ስላደረገ ይመሰገናል፤ በዚህም ሕይወት ይበዛል፤ ሞት ይሰደዳል (ይጠፋል)፡፡
ምኵራብ፡- የዐቢይ ጾም ሦስተኛ ሳምንት
 
“ቦአ ኢየሱስ ምኵራበ አይሁድ ወመሐረ ቃለ ሃይማኖት፤ ወይቤሎሙ ምጽዋተ አበድር እመሥዋዕት፤ አነ ውእቱ እግዚኣ ለሰንበት ወአቡሃ ለምሕረት፤ እግዚኣ ውእቱ ለሰንበት ወልደ እጓለ እመሕያው፤ ጌታችን ኢየሱስ ወደ አይሁድ ምኵራብ ገባ፤ የሃይማኖት ቃልን አስተማረ፤ ከመሥዋዕት ይልቅ ምሕረትን እወዳለሁ፤ የሰንበት ጌታዋ የምሕረት አባቷም እኔ ነኝ፤ የሰው ልጅም
የሰንበት ጌታዋ ነው።” (ጾመ ድጓ)
 
በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሦስተኛውን የዐቢይ ጾም ሳምንት “ምኵራብ” ይባላል። ቀጥተኛ ፍቺው “ኮረብታ፣ ተራራ የሚያህል ታላቅ ሕንጻ፣ ሰቀላ መሰል አዳራሽ” ሲሆን፣ የአይሁድ መካነ ጸሎት ወይም ቤተ መቅደስ በመሆን ያገለግል ነበር። በብሉይ ኪዳን አይሁድ ቤተ መቅደስ ነበራቸው፡፡
 
ናቡከደነጾር ኢየሩሳሌምን በወረረ ጊዜ ግን ቤተ መቅደሱን አፈረሰ፤ ሕዝቡን ወደ ባቢሎን አፈለሰ፤(፪ኛነገ.፳፬-፳፭፣ኤር.፬፥፯:፣፴፱፥፩-፲፣፶፪፥፩-፴) ከዚህ ጊዜ ጀምሮ አይሁድ በሚኖሩባቸው ሥፍራዎች ሁሉ ለጸሎት ቤት ይሠሩ ነበር፡፡ በዚያን ዘመን ቢያንስ ዐሥር አባ ወራዎች/የቤተ ሰብ ኃላፊዎች/ በቦታው ከተገኙ እነዚህን ምኵራቦችን ለመሥራት ይፈቀድላቸው ነበር፡፡ (Talmud Mishnah, Responsa literature, Jewish Encyclopedia, Academic Scholarly Works.)  ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በኢየሩሳሌም እየተዘዋወረ በሚያስተምርበት ጊዜ ግን ብዙ ምኵራቦች ነበሩ፡፡ በሐዲስ ኪዳንም ለሐዋርያት በብዛት የስብከት ዓውደ ምሕረቶች ሆነው አገልግለዋል።
 
ምኵራበ አይሁድ በውስጡ የብራና የሕግ እና የነቢያት መጻሐፍት ይገኛሉ፡፡ ምእመኑ እንዲሰማቸው ከፍ ባለ መድረክ ላይ በመሆን መምህራንና ካህናት ቆመው መጻሕፍትን ያነባሉ፤ ቃለ እግዚአብሔርንም  ያስተምሩ ነበር። የምኵራብ ሹማምንት አለቆች ጥፋተኛ ሰው ሊቀጡ ሥልጣን ነበራቸው፡፡ አገልጋይ ወይም የሚራዱ ወጣቶችም ልጆችን በማስተማር፣ በማቅረብ በተጨማሪ የአለቆችን ትእዛዝ በመፈጸም ያገለግላሉ፡፡
 
በሰንበት ሕዝብ ሁሉ በምኵራብ ተሰብስቦ ከሕግና ከነቢያት ንባብ፣ ስብከትና ቡራኬ በመቀበል አምልኮታቸውን ይፈጽሙ ነበር፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ምኵራብ ተገኝቶ ሕዝቡን አስተምሯል፡፡ ቅዱስ ሉቃስ በወንጌሉ ”ወዳደገበትም ወደ ናዝሬት መጣ፤ እንደ ልማዱም በሰንበት ቀን  ምኵራብ ገባ ሊያነብም ተነሣ” እንዳለ ቅዱሳት መጻሕፍትን ማንበብ፣ መማር፣ መመርመር፣መተርጎም፣ጉባኤ መሥራት አዘውትረው የሚፈጽሙት ተግባር እንደነበር ያስረዳል።(ሉቃ.፬፡፥፲፮)
 
ነገር ግን በምኵራብ ሰዎች ለተለያየ ዓላማ ይሰበሰቡ ነበር፡፡
 
፩. አማናዊ እረኛ ነው ብለው፦
ወልድ ዋሕድ ብለው ሲጠብቁት የነበረው ተስፋ “ደረሰልን፤ ወረደ፤ ተወለደ፤ የዓለም መድኃኒት እርሱ ነው” ብለው አዳኝነቱን አምነው ይከተሉታል። “ነዋ በግዑ ለእግዚብሔር ዘያአትት ወያሴስል ኃጢአተ ዓለም፤ የዓለሙን ኃጢአት የሚያስተሰርይ የእግዚብሔር በግ መሆኑን አውቀው የሚከተሉት አሉ። ”በጎቹም ድምፁን ያውቃሉና ይከተሉታል” እንዲል። (ዮሐ.፲፥፬)
 
፪. የቃሉን ትምህርት የእጁን ተአምራት ሽተው፦ ከደዌ ለመፈወስ ይሰበሰባሉ፤ ልብሱን ዳሰው፣ ወድቀው ሰግደው፣ ጥላውን ተጋርደው፣ በእጁ ተዳሰው የሚፈወሱ ነበሩ። (ማር. ፭፥፳፪ እስከ ፍጻሜ)። ጌታችን በዕለተ ሰንበት ሕዝብ በተሰበሰበበት በምኵራብ እንደሚያስተምር ያስረዳናል፤ ”ሰንበትም በሆነ ጊዜ በምኵራብ ያስተምር ጀመር፤…ወደ ምኩራባቸውም ገብቶ ዝም ይሉ ዘንድ ገሠፃቸው፤ እነርሱም ትምህርቱን፣ የቃሉን ግርማ፣ የአነጋገሩን ጣዕምና፣ የአንደበቱን ቅልጥፍና አደነቁ፡፡”  (ማር.፮፥፩) “ወደ ገዛ አገሩም መጥቶ እስኪገረሙ ድረስ በሚገባቸው ያስተምራቸው ነበር።” (ማቴ.፲፫፥፶፬)
 
፫. ምግበ-ሥጋ ፈልገው ደም ግባቱን አይተው:- ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከምኵራብ ጉባኤ ትምህርት በኋላ ጥቂቱን አበርክቶ እልፉን ይመግብ ስለነበር ጉባኤውን ይታደማሉ። ክርስቲያኖች እግዚአብሔርን የምናመልከው ምግበ ሥጋ ስለሰጠን አይደለም። እርሱንማ ለሕዝብም ለአሕዛብም ሳይሰስት የሚመግብ መጋቤ ዓለማት ነው። ክርስቲያን በመብል አይገመትም። “እንግዲህ በመብልም ቢሆን÷ በመጠጥም ቢሆን÷ በልዩ ልዩ በዓላትም ቢሆን÷ በመባቻም ቢሆን÷ በሰንበትም ቢሆን የሚነቅፋችሁ እንዳይኖር ተጠንቀቁ፡፡” እንዲል፡፡ (ቆላ. ፪፥፲፮ እስከ ፍጻሜ)
 
፬. ለክስ የሚቀርቡ አሉ፦ ከቃሉ ግድፈት ከትምህርቱ ስሕተት የሚፈልጉ ሰቃለያን አይሁድ፣ ሊቃነ ካህናት አምላክነቱን የሚጠራጠሩ አይሁድ የሸንጎውን ጌታ ለሸንጎ ፍርድ ሊያቀርቡት ከግር በግር ይከተሉት ነበር። “ወጸቢሖ ተጋብኡ ሊቃነ ካህናት ወጸሐፍት ወሊቃናተ ሕዝብ ወወሰድዎ ውስተ ዐውዶሙ። ወይቤልዎ እመ አንተሁ ክርስቶስ ንግረነ ገሃደ ወይቤሎሙ እመኒ አይዳእኩክሙ ኢተአምኑኒ፡፡ በነጋም ጊዜ፥ የካህናት አለቆች፥ ጻፎችና የሕዝቡ ሽማግሌዎች ተሰብስበው ወደ ሸንጎአቸው ወሰዱት፡፡ “አንተ ክርስቶስ እንደ ሆንህ በግልጥ ንገረን” አሉት፡፡እርሱም እንዲህ አላቸው፥ “ብነግራችሁም አታምኑኝም” እንዲል፡፡ (ሉቃ. ፳፪፥፷፮፣ ማቴ.፳፮፥፶፱)
 
ዛሬም በአማናዊቷ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሥጋዊ ነገር ብቻ ገዝፎባቸው ቤተ መቅደሱን ለንግድ፣ ንዋያተ ቅድሳትን ለትርፍ ብቻ አሳልፈው የሚሸጡ፣ የሚለውጡ፣ ለክስ የሚፋጠኑ ከምኵራብ ያልወጡ የበጎችን እረኛ አሳልፈው የሚሰጡ አዋልደ ይሁዳ እንዳሉ ግልጽ ነው። “ወረከበ በምኵራብ እለ ይሠይጡ አልህምተ ወአባግዐ ወአርጋበ …፤ በመቅደስም በሬዎችን፣ ላሞችን፣ በጎችን፣ ርግቦችን፣ የሚሸጡትን አገኘ …፤ “ኢትግበሩ ቤተ አቡየ ቤተ ምስያጥ ቤትየሰ ቤተ ጸሎት ይሰመይ፤ የአባቴን ቤት የንግድ ቦታ አታድርጉት፤ እናንተ ግን የሌቦች ዋሻ አደረጋችሁት፤ ቤቴስ የጸሎት ቤት ይባላል” እያለም የሃይማኖትን ቃል አስተማራቸው፡፡ (ዮሐ.፪፥፲፮፣ማቴ.፳፩፥፲፫)
 
በምኵራብ ይሸጡ፣ ይለውጡ የነበሩትን የገሠፀበት፣ ቤተ መቅደስን የከብት መንጃ የወርቅ መነገጃ ያደረጉ ሰዎችን ከእነ ሸቀጣቸው ከቤተ መቅደስ ያስወጣበት፣ ቤተ መቅደስ የእግዚአብሔር ማደሪያ፣ የመሥዋዕቱ መክበሪያ፣ የጸሎት ሥፍራ ምስካበ ቅዱሳን መሆኗን ያስተማረበት ዕለት ነው። ቃሉ በዚያን ዘመን ተነግሮ ብቻ ያለፈ አይደለም፤ ለእኛ የተነገረን መሆኑን አውቀን የባለቤቱ ጅራፍ ሳይገርፈን ልንመለስ ይገባል። “የገመድም ጅራፍ አበጅቶ ሁሉን በጎችንም በሬዎችንም ከመቅደስ አወጣቸው፥ የለዋጮችንም ገንዘብ አፈሰሰ ገበታዎቻቸውንም ገለበጠ፡፡” (ዮሐ.፪፥፲፬)
 
ከሚመጣው ጅራፍ ለመዳን እምነት ከተግባር ይዞ መገኘት ያስፈልጋል።” ወንድሞቻችን ሆይ÷ እምነት አለኝ፤ ምግባር ግን የለኝም የሚል ሰው ቢኖር÷ ምን ይጠቅመዋል? በውኑ እምነቱ ልታድነው ትችላለችን? ከወንድሞቻችን÷ ወይም ከእኅቶቻችን÷ የታረዙ ወይም የዕለት ምግብ ያጡ ቢኖሩ÷ ከእናንተም አንዱ …እንደዚሁም ሥራ የሌለው እምነት ቢኖር በራሱ የሞተ ነው።” እንዳለ። (ያዕ.፪፥፲፬ እስከ ፍጻሜ)
 
የዕለቱ መዝሙር (ከጾመ ድጓ)፦ ቦአ ኢየሱስ ምኩራበ አይሁድ ወመሐረ ቃለ ሃይማኖት፤ጌታችን ኢየሱስ ወደ አይሁድ ምኩራብ ገባ፤ የሃይማኖት ቃልን አስተማረ፤
 
መልእክታት፦(ቆላ.፪፥፲፮ እስከ ፍጻሜ) (ያዕ.፪፥፲፬ እስከ ፍጻሜ)
ወንጌል፦ (ዮሐ.፪፥፲፪-እስከ ፍጻሜ)
(የሐዋ.፲፥፩-፰)
 
ምስባክ፦ “እስመ ቅንዐተ ቤትከ በልዐኒ፡፡ ትዕይርቶሙ ለእለ ይትዔየሩከ ወድቀ ላዕሌየ፡፡ወቀጻዕክዋ በጾም ለነፍስየ፡፡” ትርጉም “የቤትህ ቅንዓት በልቶኛልና፥ የሚሰድቡህም ስድብ በለዬ ወድቆአልና፡፡ ሰውነቴን በጾም አደከምኋት፡፡  (መዝ.፷፰፥፱)     
 
በምሕረቱ ይታደገን፤ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፤ አሜን!!!
HTML Embed Code:
2024/03/29 07:15:47
Back to Top