TG Telegram Group Link
Channel: ሲዳማ ቡና Sidama Coffe©
Back to Bottom
በሁለተኛ አጋማሽ ያኩቡ መሃመድ በቀይ ካርድ ከሜዳ ወጥቷል
ኤሪክ ካፓዬቶ ላይ ነዉ ጥፋት የሰራበት
የእርሱን ቦታ ሳይተኩ ገብተዉ አህመድ ሁሴን ሊያስቆጥር የሚችልበት እድል ነበር ግን ወጥቷል
ሙሏለም መስፍን ወደ ኋላ ተመልሶ የመከላከል ሂደቱን እያገዙ ይገኛል
አርባምንጮች ወደኋላ አፈግፍገዉ እየተከላከሉ ይገኛሉ
ኦኦኦኦ ሰላዲን የሚገርም እድል ነበር ግን ወጣበት
ሲዳማ ቡና ቅጣት ምት አጊኝቷል
የሚገርም አመታት ነበር ግን ወጥቶበታል
በመጀመሪያው አጋማሽ ለሲዳማ ቡና የመጀመሪያውን ግብ ያስቆጠረው አንጋፋው አጥቂ ሳላዲን ሰዒድ ልክ በዛሬ ቀን ሰኔ 7 2007 ኢትዮጵያ ሌሶቶን 2-1 ስታሸንፍ ግብ አስቆጥሮ ነበር።

@Sidamacoffe
@Sidamacoffe
ተጠናቀቀ

ሲዳማ ቡና 1-2 አርባምንጭ ከተማ
ስራዉ አሁንም ቀጥሏል.........

ማንም ዘወር ብሎ ያላየዉን የሲዳማ ቡና ታዳጊዎችን ይዞ በፈተኝ ወቅት ለክለቡ ለመጀመሪያ ጊዜ ዋንጫ ይዞ መጥቶ ነበር ፤ አሁን ላይ ደግሞ እድገቱን አሳድጎ የሲዳማ ቡና ዋና አሰልጣኝ በመሆን ስራዉን ቀጥሏል እስካሁን በርስ ስር ክለቡ የተሸነፈዉ አንድ ጨዋታ ሲሆን በቡድኑ ዉስጥ የተጫዋቾች ስነልቦናን እና በራሳቸዉ እምነትን እንዲያሳድግ አድርጓል ።

ሲዳማ ቡና ሶስተኛ ደረጃን እንዲያጠናቅቅ የራሱን ድርሻ የተወጣዉ አሰልጣኝ ወንድማገኝ ተሾሜ ዛሬ በሊጉ የመጨረሻ ሳምንት ታዳጊዎችን በማሰለፍ ጨዋታዉን የሚያደርግ ይሆናል ፤ ክለቡ ዉስጥ ያሉትን ክፍተቶችን በመሸፈን ለቀጣይ አመት ለመዘጋጀት እረፍት የሚያገኘዉ ክለቡ ለዋንጫ ፉክክሩ ቀጣዩን አመት ካሁኑ እየጠበቁት ይገኛሉ።

አሰልጣኙ ባለፈዉ አመት በታዳጊዎች ዘንድሮም በሊጉ ጥሩ ስራን የሰራ ሲሆን ደጋፊዎችም ከእርሱ የሚጠብቁትን ለማድረግ ካሁኑ እየታተረ ይገኛል ፤ በአመቱ የመጨረሻ ጨዋታዉን ከሀዲያ ሆሳዕና ጋር የሚያደርጉት ቡናማዎቹ ድልን አልመዉ ይገዙ ቦጋለን የሊጉ ኮከብ ግብ አስቆጣሪ ለማድረግም ጭምር ወደ ሜዳ ይገባሉ።

ወንድማገኝ ተሾመ እና ይገዙ ቦጋለ እናመሰግናለን 👏🙏

@sidamacoffe
@sidamacoffe
ለምርጡ ተከላካያችን ጊት ጋትኩት ድምጻችሁን ስጡት ፤ በአመቱ በሲዳማ ቡና ያለዉን ሁሉ ሜዳ ዉስጥ የሰጠ በአንድ ለአንድ ግንኙነት የተካነ የአየር ላይ ኳሶች ላይ የሚደነቅ እና ለብሔራዊ ቡድን ጥሪ ከቀረበላቸዉ ተጫዋቾችም አንዱ ነበር።

ጊት ምርጡ 👏❤️

@Sidamacoffe
@sidamacoffe
ሰዎቻችን በምሽቱ ፕሮግራም ደምቀዋል.........

የሲዳማ ቡና አሰልጣኝ ወንድማገኝ ተሾሜ ፣ የክለቡ ስራ አስኪያጅ ኤሪሚያስ ተስፋዬ ፣ የክለቡ የደጋፊዎች ማህበር ጸሃፊ ደጀኔ ማርቆስ ፣ የሲዳማ ክልል ስፖርት ኮሚሺን ፍሬዉ አሬራ እና የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ሀላፊ ጃጎ አገኘሁ በፕሮግራሙ የታደሙ ሲሆን ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪዉ ይገዙ ቦጋለ የሁለት ሚልዮን ብር ተሸላሚ ሆኗል ፤ ሲዳማ ቡና እንዲሁ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ ማጠናቀቁን ተከትሎ ከሊግ ኮሚቴዉ የገንዘብ ድጋፍን በደረጃ አጊኝቷል።

አሰልጣኙ እስካሁን ባለዉ መረጃ ከክለቡ ጋር እንደሚቆዩ ሲጠበቅ በቀጣይነት ወደ ክለቡ የሚመጡ ተጫዋቾችን ዝዉዉር የማደርሳችሁ ይሆናል።

@sidamacoffe
@sidamacoffe
⚡️ እግር ኳስን ለሰላም ፣ ለመዝናኛነት ፣ ባህልን ለማስተዋወቅ ፣ እርስ በርስ ያለን ፍቅር ለማጉላት እንዲሁም ሀገርን ለማስተዋወቅ ጭምር መጠቀም የሁሉም ፍላጎት እና ምኞት ነዉ ፤ ታዲያ የእግር ኳስ ሜዳን በጸብ እና ብጥብጥ ሳይሆን ፍጹም ሰላም የሰፈነበት እና ከህጻን እስከ ሽማግሌ በአንድነት በፍቅር እንዲከታተሉ ማስቻል የቤት ስራችን ነዉ።

⚡️ በክለቦች ዘንድ ያለን ችግሮች እንዲሁም ሊሰሩ ይገባል በሚባሉ ጉዳዮች ላይ ከክለቦች ጋር በመነጋገር እግር ኳስ ወዳድ ደጋፊ የሚወደዉን እና የሚደግፈዉን ክለብ ከሌሎች የክለብ ደጋፊዎች ጋር በፍቅር እንዲመለከት ማስቻል ዋናዉ ስራ ነዉ።

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ደጋፊዎች ማህበር ጥምረት ታዲያ ይህንን ስራ ለማስራት እና የኢትዮጵያን ፕሪሚየር ሊግ ክለቦች ደጋፊዎችን ፍላጎት በማስቀደም ሊጉን ገጽታ ስፖርታዊ ጨዋነትን ለማስፈን ባለፈዉ አመት እዉቅና በማግኘት ወደስራ የገባ ተቋም ነዉ።

⚡️ እግር ኳስ ሜዳዎቻችንን ከፍርሃት እና ፀብ የፀዳ ፍጹም ሰላማዊ ለማድረግ የሚሰራዉ ይህ ተቋም እግር ኳስ ተመልካችን በእኩል አይን በማየት ለሁሉም እኩል ግልጋሎትን የሚሰጥም ጭምር ነዉ።

⚡️ ታዲያ የኢትዮጵያ ደጋፊዎች ማህበር ጥምረት የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን በመቀላቀል ስለ ክለባችሁ መረጃን ፣ በየጨዋታዉ የነበሩ ሁነቶችን ከደጋፊዎች ምስል ጋር ያገኙ:-

ፌስቡክ :- https://www.facebook.com/EthioFansCoalition
ቲዊተር :-  https://twitter.com/EthioFansCoalition
ቴሌግራም:- https://hottg.com/EPLFFC

ኢሜይል :- [email protected]

ኢንስታግራም :- EPLFFC
HTML Embed Code:
2024/05/12 19:58:59
Back to Top