Channel: Nolawi ኖላዊ
የሕይወት ሥነ ሥርዓት 10
…. አለባበስህን ጠብቅ (ካለፈው የቀጠለ)
አንዳንድ ሰዎች ስለ ራሳቸው በአፋቸው ብዙ ያወራሉ ፤ ሌሎች ደግሞ በልብሳቸው ስለራሳቸው ብዙ ያወራሉ ። ልብስ ዕርቃን መሸፈኛ ነው ። ዕራቁታችንን የሚያውቀንና የሚቀበለን እግዚአብሔር ብቻ ነው ። ሰው ያለ መሸፈኛ የማይቆም ፍጡር ነው። በሰው ፊት ለመቆም ልብስ ፣ በእግዚአብሔር ፊት ለመቆም ጸጋ ያስፈልገዋል ። ልብስ ከመሠረታዊ ፍላጎቶች አንዱ ነው ። ልብስ ሰዎች ጤናቸውን የሚጠብቁበትም ነው ። የአእምሮ በሥራ ላይ መሆን አንዱ ምልክት ልብስ መልበስ ነው ። በርግጥ እንደ ምዕራባውያን መራቆትም ፣ እንደ ዐረብ ሴቶች መጨቆንም ሁለቱም ሚዛናዊ መሆን አለበት ። ልብስ ሀብትን ማሳያ ፣ ቁንጅናን ማጉያ አድርገው የሚጠቀሙበት አሉ ። የሰው ልጅ ለራሱና ለሰዎች ብሎ የሚያደርገው ነገር ካለ እርሱ ልብስ ይበላል። ልብስ ሙሉ ሰውን ፣ ሹምን ፣ ካህንን ለመለየት የሚውል ነው ። ልብስ ትልቅ የክብር መግለጫ ነው ። የሰው ልጆችም እንደ ዕፀ በለስ በልብስ የሚፈተኑ ሆነዋል ። ላለበሰና ለለበሰ ሰው እኩል ክብር የላቸውም ። ኖር ለልብሱ ይባላል ። ኖር ለእርሱ ሳይሆን ኖር ለልብሱ መባሉ ተገቢ አይደለም።
የዓለማችን ትልቁ ምርት ከምግብ ቀጥሎ ልብስ ነው ፤ ከዚያ ቀጥሎ መድኃኒት ሊሆን ይችላል ። ጸሎታችንም “የዕለት ጉርሴን ፣ የዓመት ልብሴን አትንሣኝ” የሚል ነው ። ልብስ የሚያገለግለው ዕራቁትን ለመሸፈን ብቻ ስይሆን የሰውነት ቅርጽንም ለመሸፈን ነው ። የሰውነትን ቅርጽን ማሳየት በራሱ እንደ መራቆት ነው ። ልብስ የሰው ልጆችን ውበት የሚያላብሳቸው ነው ። ዕራቁቱን የሚያምር ከሕፃን በቀር ማግኘት አስቸጋሪ ነው ። ልብስ ከቅድስና መለኪያዎች አንዱ ነው ። ብዙ ጊዜ ልቅ አለባበስን በሚመለከት ከወንዶች ይልቅ ሴቶች ይፈተናሉ ። “የሴት ክብር ባሏ ሲገልጣት እንጂ በአደባባይ ተገልጣ ስትለምን አይደለም” ይባላል ። ሰዎች ሁሉ በዓለም ላይ ያሉ ወገኖች ልብስን በተለያየ ዓላማ ሊለብሱ ይችላሉ ።
የመጀመሪያው ፋሽን ለመከተል ነው ። የፋሽኑ ዓለም እንቅልፍ የለውም ። የሰዎችን ቀልብ ለመሳብና ገንዘብ ለመልቀም ሌሊትና ቀን ይተጋል ። የፋሽኑ ዓለም ከአጋንንት ጋር የእውቀት ልውውጥ እንደሚያደርግ ብዙ ሲነገር ኖሯል ። ሰዎችን ምን ይማርካቸዋል ? በማለት ያጠናሉ ፣ ያስጠናሉ ። በይበልጥ ዝሙትን የሚያስፋፋ ፣ ሥጋዊ ስሜትን አድራሻ ያደረገ ንድፍ ይሠራል ። ሰይጣን አያመነዝርም ፣ ግን ዝሙትን ይወዳል ። ክፉ ነገሥታትም ትውልድ የዝሙት እስረኛ ከሆነ እነርሱን ስለማያያቸው በዚህ ጦር ወግተው ያቆስሉታል ። ፋሽኑ ከተሰፋ ልብስ እስከ ተቀደደ ልብስ ፣ ከፍዝ እስከ ቦጌ ቀለም እየለዋወጠ ያመጣል ። የሰውን ወረተኛነት ትልቅ የገቢ ምንጭ በማድረግ ጠባዩን ይዋጉታል ። ዓለምን የሚመሩ ጥቂት ሰዎች ናቸው ። ዕውቅ ሰዎች ያንን ልብስ ለብሰው ሲታዩ ጎጋው ሕዝብ ይከተላል ። የልብሱ ትርጉም ምን መሆኑን እንኳ ሳይጠይቅ የለበሰውን እየጣለ ያንን ይሸምታል ። የፋሽኑ ዓለም የጊዜ ክፍተት እየሰጠ የሄደውን ፋሽን መልሶ እያመጣ አዲሱን ትውልድ ይጫወትበታል ። ፋሽን ተከታይ የሆኑ ዘመናዊና ንቁ ሰዎች እንደሆኑ ይገምታሉ ፣ ሰዎችም እንደ ዘመናዊ ያስቧቸዋል። ለልብሱ የሚጨነቅ ለነፍሱ የማይጨነቅ ደንቆሮ ነው ። እውነተኛ ሥልጣኔ ግን ከልብስ ያለፈ ነው ።
ሁለተኛው ማራኪ ለመሆን ነው ። ሴቶች ወንዶችን ለመሳብ ፣ ወንዶች ሴቶችን ለመሳብ ይለብሳሉ። በእጃቸው ላይ የሚቀቡት ሽቶ ሳይቀር የሚጨብጡት ሰው እጅ ላይ ታትሞ እንዲቀር ፣ አካባቢው ሁሉ በእነርሱ ጠረን እንዲታወድ ይፈልጋሉ ፤ ይህ መለስተኛ ጣዖትነት ነው ። ለዚህ ነው “ሽቶ የዝሙት ቅብዐ መንግሥት ነው” የሚባለው ። ከወደድነው ሁሉ ጋር አንኖርም ፣ የወደደን ሁሉም ከእኛ ጋር አይኖርም ። ከልብሳችን ይልቅ ጠባያችን ሳቢ ቢሆን የሰው ዋጋ እናገኛለን ። አሊያ የሸቀጥ ማስታወቂያ ሆነን እንቀራለን ። በዕድሜአቸው ዘመን ምንም የሚነገር ታሪክ የሌላቸው ፣ ልብስ ሲገዙ ፣ ሽቶ ሲያጠራቅሙ ኖረው ሞቱ የሚባሉ ብዙ ምስኪን ሰዎች አሉ።
ይቀጥላል
ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ሚያዝያ 1 ቀን 2016 ዓ.ም.
…. አለባበስህን ጠብቅ (ካለፈው የቀጠለ)
አንዳንድ ሰዎች ስለ ራሳቸው በአፋቸው ብዙ ያወራሉ ፤ ሌሎች ደግሞ በልብሳቸው ስለራሳቸው ብዙ ያወራሉ ። ልብስ ዕርቃን መሸፈኛ ነው ። ዕራቁታችንን የሚያውቀንና የሚቀበለን እግዚአብሔር ብቻ ነው ። ሰው ያለ መሸፈኛ የማይቆም ፍጡር ነው። በሰው ፊት ለመቆም ልብስ ፣ በእግዚአብሔር ፊት ለመቆም ጸጋ ያስፈልገዋል ። ልብስ ከመሠረታዊ ፍላጎቶች አንዱ ነው ። ልብስ ሰዎች ጤናቸውን የሚጠብቁበትም ነው ። የአእምሮ በሥራ ላይ መሆን አንዱ ምልክት ልብስ መልበስ ነው ። በርግጥ እንደ ምዕራባውያን መራቆትም ፣ እንደ ዐረብ ሴቶች መጨቆንም ሁለቱም ሚዛናዊ መሆን አለበት ። ልብስ ሀብትን ማሳያ ፣ ቁንጅናን ማጉያ አድርገው የሚጠቀሙበት አሉ ። የሰው ልጅ ለራሱና ለሰዎች ብሎ የሚያደርገው ነገር ካለ እርሱ ልብስ ይበላል። ልብስ ሙሉ ሰውን ፣ ሹምን ፣ ካህንን ለመለየት የሚውል ነው ። ልብስ ትልቅ የክብር መግለጫ ነው ። የሰው ልጆችም እንደ ዕፀ በለስ በልብስ የሚፈተኑ ሆነዋል ። ላለበሰና ለለበሰ ሰው እኩል ክብር የላቸውም ። ኖር ለልብሱ ይባላል ። ኖር ለእርሱ ሳይሆን ኖር ለልብሱ መባሉ ተገቢ አይደለም።
የዓለማችን ትልቁ ምርት ከምግብ ቀጥሎ ልብስ ነው ፤ ከዚያ ቀጥሎ መድኃኒት ሊሆን ይችላል ። ጸሎታችንም “የዕለት ጉርሴን ፣ የዓመት ልብሴን አትንሣኝ” የሚል ነው ። ልብስ የሚያገለግለው ዕራቁትን ለመሸፈን ብቻ ስይሆን የሰውነት ቅርጽንም ለመሸፈን ነው ። የሰውነትን ቅርጽን ማሳየት በራሱ እንደ መራቆት ነው ። ልብስ የሰው ልጆችን ውበት የሚያላብሳቸው ነው ። ዕራቁቱን የሚያምር ከሕፃን በቀር ማግኘት አስቸጋሪ ነው ። ልብስ ከቅድስና መለኪያዎች አንዱ ነው ። ብዙ ጊዜ ልቅ አለባበስን በሚመለከት ከወንዶች ይልቅ ሴቶች ይፈተናሉ ። “የሴት ክብር ባሏ ሲገልጣት እንጂ በአደባባይ ተገልጣ ስትለምን አይደለም” ይባላል ። ሰዎች ሁሉ በዓለም ላይ ያሉ ወገኖች ልብስን በተለያየ ዓላማ ሊለብሱ ይችላሉ ።
የመጀመሪያው ፋሽን ለመከተል ነው ። የፋሽኑ ዓለም እንቅልፍ የለውም ። የሰዎችን ቀልብ ለመሳብና ገንዘብ ለመልቀም ሌሊትና ቀን ይተጋል ። የፋሽኑ ዓለም ከአጋንንት ጋር የእውቀት ልውውጥ እንደሚያደርግ ብዙ ሲነገር ኖሯል ። ሰዎችን ምን ይማርካቸዋል ? በማለት ያጠናሉ ፣ ያስጠናሉ ። በይበልጥ ዝሙትን የሚያስፋፋ ፣ ሥጋዊ ስሜትን አድራሻ ያደረገ ንድፍ ይሠራል ። ሰይጣን አያመነዝርም ፣ ግን ዝሙትን ይወዳል ። ክፉ ነገሥታትም ትውልድ የዝሙት እስረኛ ከሆነ እነርሱን ስለማያያቸው በዚህ ጦር ወግተው ያቆስሉታል ። ፋሽኑ ከተሰፋ ልብስ እስከ ተቀደደ ልብስ ፣ ከፍዝ እስከ ቦጌ ቀለም እየለዋወጠ ያመጣል ። የሰውን ወረተኛነት ትልቅ የገቢ ምንጭ በማድረግ ጠባዩን ይዋጉታል ። ዓለምን የሚመሩ ጥቂት ሰዎች ናቸው ። ዕውቅ ሰዎች ያንን ልብስ ለብሰው ሲታዩ ጎጋው ሕዝብ ይከተላል ። የልብሱ ትርጉም ምን መሆኑን እንኳ ሳይጠይቅ የለበሰውን እየጣለ ያንን ይሸምታል ። የፋሽኑ ዓለም የጊዜ ክፍተት እየሰጠ የሄደውን ፋሽን መልሶ እያመጣ አዲሱን ትውልድ ይጫወትበታል ። ፋሽን ተከታይ የሆኑ ዘመናዊና ንቁ ሰዎች እንደሆኑ ይገምታሉ ፣ ሰዎችም እንደ ዘመናዊ ያስቧቸዋል። ለልብሱ የሚጨነቅ ለነፍሱ የማይጨነቅ ደንቆሮ ነው ። እውነተኛ ሥልጣኔ ግን ከልብስ ያለፈ ነው ።
ሁለተኛው ማራኪ ለመሆን ነው ። ሴቶች ወንዶችን ለመሳብ ፣ ወንዶች ሴቶችን ለመሳብ ይለብሳሉ። በእጃቸው ላይ የሚቀቡት ሽቶ ሳይቀር የሚጨብጡት ሰው እጅ ላይ ታትሞ እንዲቀር ፣ አካባቢው ሁሉ በእነርሱ ጠረን እንዲታወድ ይፈልጋሉ ፤ ይህ መለስተኛ ጣዖትነት ነው ። ለዚህ ነው “ሽቶ የዝሙት ቅብዐ መንግሥት ነው” የሚባለው ። ከወደድነው ሁሉ ጋር አንኖርም ፣ የወደደን ሁሉም ከእኛ ጋር አይኖርም ። ከልብሳችን ይልቅ ጠባያችን ሳቢ ቢሆን የሰው ዋጋ እናገኛለን ። አሊያ የሸቀጥ ማስታወቂያ ሆነን እንቀራለን ። በዕድሜአቸው ዘመን ምንም የሚነገር ታሪክ የሌላቸው ፣ ልብስ ሲገዙ ፣ ሽቶ ሲያጠራቅሙ ኖረው ሞቱ የሚባሉ ብዙ ምስኪን ሰዎች አሉ።
ይቀጥላል
ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ሚያዝያ 1 ቀን 2016 ዓ.ም.
የሕይወት ሥነ ሥርዓት 11
…. አለባበስህን ጠብቅ (ሐ)
ልብስን በሚመለከት ሰዎች የተለያየ አመለካከት ይኖራቸዋል ብለን ሁለቱን አይተናል ። ሰዎች ልብስን የሚለብሱት ሦስተኛው ብዙዎች ስለለበሱት ሊሆን ይችላል ። የብዙኃን ድምፅ ያሸንፋልና ለምን? ሳይባል የሚለበሱ ልብሶች አሉ ። የተጣበቀ ጠባብ ልብስ ሁሉ ሰው ስለለበሰው እኛ መልበስ ላያስፈልገን ይችላል ። የፋሽኑ ኢንዱስትሪ ትልቁንም ትንሹንም ወጣት ማስመስል የሚፈልግ ነው ። ሽምግልናም የራሱ ውበት አለው ። የራሱ አለባበስም አለው ። ይልቁንም በዕድሜ ከፍ ያሉ ወጣትነትን አይተውታልና ወጣት ለመምሰል ባይሞክሩ የተሻለ ነው ። ወጣቶች ሽምግልናን አላዩትምና ቢናፍቁት ወግ ነው ።
አራተኛ፡- ብዙዎች ስለማይለብሱት ሊሆን ይችላል ። አንዳንድ ሰዎች ብዙዎች የለበሱትን ይጠሉታል ። ከፋብሪካው በራሳቸው ስም የታተመ ልብስ ያሠራሉ ። ከጀማው ጋር መጋፋት ድሀ መሆን ይመስላቸዋል ። በእውነት ልብስ የሀብት ማሳያ መሆኑ ዕድሜ ለቻይና ጊዜው ያለፈ ሆኗል።
አምስተኛ፡- ለማጭበርበር ሊሆን ይችላል ። ሙሉ ልብስ ለብሰው ፣ ፕሮቶኮላቸውን ጠብቀው ፣ እንግሊዝኛ እያወሩ ፣ ትልልቅ ሀብትን እየተነተኑ የሚዘርፉ ብዙዎች ናቸው ። ለእነዚህ ሰዎች ልጃቸውን መዳር የሚፈልጉ ብዙ ሴት ወይዘሮዎች አሉ ። እነዚህን ማግባት የሚፈልጉ ብዙ ሀብታም ሴቶች ሊኖሩ ይችላሉ ። “እህ ትበል እናትሽ ልብሴን አይታ የዳረችሽ” የሚባለው ታሪክ የደረሰባቸው ሴቶች ብዙ ናቸው ። ውድ መኪኖችን ተከራይተው የሚያጭበረብሩ አያሌ ናቸው ። የትልልቅ ተቋማት መኪኖችን በመያዝ ባለሥልጣን ነኝ እያሉ ሞኞችን ገደል የሚከትቱ የተካኑ ሌቦችን ይህች ከተማ ይዛለች ። ቤቶቹና ፎቆቹ አፍ ቢኖራቸው ብዙ ይናገሩ ነበር ።
ስድስተኛ፡- ከማኅበረሰቡ ላለመለየት መናኛ የሚለብሱ አሉ ። አንዳንድ ሀብትና ሥልጣን ያላቸው ሰዎች “ልብስ ስመርጥ ጊዜ አላጠፋም” ብለው የወደዱትን አንድ ቀለም ያለውን ልብስ ስድስት ይገዛሉ ። ዓመት ሙሉ አንድ ዓይነት ኮት ስለሚለብሱ ልብስ የማይቀይሩ ይመስለናል ። ዛሬ በአንዳንድ ከተሞች የሚታገቱ ሰዎች ለየት ያለ ልብስ የለበሱ ናቸው ። “በሮም ሲኖሩ እንደ ሮማውያን” የሚባለው ለዚህ ነው ። ዓለም ከጉልበት ይልቅ ለጥበብ እጅ ትሰጣለች ። ስንኖር ጠቢብ መሆን መልካም ነው ። የቆዩት ሀብታሞች ብዙ የሚለብሱ አልነበሩም ። በዚህ ምክንያት አንድ ዓይነት ጨርቅ ስለሚለብሱ “ልብሳቸው ላይ አስደግመው ነው” የሚላቸው ብዙ ነበር ።
ሰባተኛ፡- የሥራ ጠባያቸው ስለሚያስገድዳቸው የሚለብሱ አሉ ። የባንክ ፣ የሆቴል ፣ የተለያዩ ተቋማት ሠራተኞች ሙሉ ልብስ እንዲለብሱ ይገደዳሉ ። ባንኮች አንድ ተራ አለባበስ የለበሰ ሠራተኛ ቢያስቀምጡ ኖሮ ማንም አምኖ ገንዘብ አያስቀምጥም ነበር ። ትምህርት ቤቶች የተማሪዎችን አንድ ዓይነት ልብስ መደንገጋቸው ያስመሰግናል ። በቤተ ክርስቲያንም ሁሉም ነጭና ርካሽ ነጠላ ለብሶ ማስቀደሱ ትልቅ ጥበብ ነው ። በሌሎች አብያተ ክርስቲያናት የልብስና የጫማ ውድድር አድክሞአቸዋል ። አስተማሪያቸውም የሚያወራው ልብሱን ከየት አገር እንዳስመጣው ነው ። ድሀ እዚህ መሐል ምን ይሠራል !
ስንለብስ በአቅማቸው አነስ ያሉ ሰዎች ያሉበት ከሆነ እንዳናሳቅቃቸው መጠንቀቅ ያስፈልጋል ። ያላቸውን አጥበውና ለብሰው በመጡበት ስፍራ ደግሞ ዝቅ ያለ አለባበስ ብንለብስ ይሸማቀቃሉ። ስንለብስ አካባቢውንና ሁኔታውን ማገናዘብ አለብን ። የኀዘንና የሰርግ ልብስ መለየት አለብን። ልቅሶ ቤት ነጭ ለብሰን ብንሄድ “የደስ ደስ መጣ” ብለው ይዘምቱብናል ። ጥቁር መልክ ካለን ነጭ መልበስና ቀይ ከሆንን ጥቁርን ብንለብስ የተሻለ ነው ። ልብሳችን ብዙ ዓይነት ቀለም መከተል የለበትም ። ቢያንስ ከሁለት ቀለም ማለፍ የለብንም ። ጫማችን የልብሳችንን አንደኛውን ቀለም ቢከተል መልካም ነው ። የቀለም ምርጫችን በራሱ የውስጣችንን ማንነት ይገልጣል ።
ልብሳችንን ማጠብና መተኮስ ግድ ነው ። ድሀ የሆነው ወታደር ይህንን የሚያደርግ ከሆነ ሌላው ጎበዝ መሆን አለበት ። ስለ ቆሸሸን ሰው ይሸሸናል እንጂ አያዝንልንም ፣ መንፈሳዊ አድርጎም አይመለከተንም ። በትዳር ላይም አንዱ ወገን ንጽሕናውን የማይጠብቅ ከሆነ መራራቅን ይወልዳል ። እስከ ፍቺም እንደሚደርስ ከልምዳችን መናገር እንችላለን ። ትዳር መግባት ገደል መግባት አይደለምና ራስን መጣል ተገቢ አይደለም ። ራሳችሁን ስትጥሉ እንኳን ሌላው ሊወዳችሁ ራሳችሁንም መቀበል ያቅታችኋል ። ውኃን ርካሽ አድርጎ የሰጠን ጌታ ለንጽሕና ብሎ ነው ። የሥራ ልብስ ፣ የስፖርት ልብስ መለየት አለብን ። ልብሳችንን በመልክ በመልኩ ማስቀመጥ በቀላሉ አይቶ ለመልበስ ይረዳናል ። ብዙ ጨርቅ ማብዛትም በሽታ ነው ። ከሁሉ በላይ እኛ ለምናየው ለውስጥ ልብሶቻችን ዋጋ መስጠት አለብን ። አደራ ሙሉ ልብስ ለብሰን ፣ የተቀደደ ካልሲ ማድረግ ራስን መናቅ ነው ። ያየ ሰውም ይንቀናል ። “ውስጡን ለቄስ “ ብሎ ይተርትብናል ። ለውስጥ ልብሶቻችን ንጽሕና ትልቅ ዋጋ መስጠት አለብን ።
ሰማይን በከዋክብት ፣ ምድርን በአበባ ያስጌጠ እግዚአብሔር እኛም በሥርዓት እንድንለብስ ይፈልጋል ! አልባሽ እርሱ ነውና “የዕለት ጉርሴን ፣ የዓመት ልብሴን ስጠን” እንለዋለን ።
ይቀጥላል
ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ሚያዝያ 5 ቀን 2016 ዓ.ም.
…. አለባበስህን ጠብቅ (ሐ)
ልብስን በሚመለከት ሰዎች የተለያየ አመለካከት ይኖራቸዋል ብለን ሁለቱን አይተናል ። ሰዎች ልብስን የሚለብሱት ሦስተኛው ብዙዎች ስለለበሱት ሊሆን ይችላል ። የብዙኃን ድምፅ ያሸንፋልና ለምን? ሳይባል የሚለበሱ ልብሶች አሉ ። የተጣበቀ ጠባብ ልብስ ሁሉ ሰው ስለለበሰው እኛ መልበስ ላያስፈልገን ይችላል ። የፋሽኑ ኢንዱስትሪ ትልቁንም ትንሹንም ወጣት ማስመስል የሚፈልግ ነው ። ሽምግልናም የራሱ ውበት አለው ። የራሱ አለባበስም አለው ። ይልቁንም በዕድሜ ከፍ ያሉ ወጣትነትን አይተውታልና ወጣት ለመምሰል ባይሞክሩ የተሻለ ነው ። ወጣቶች ሽምግልናን አላዩትምና ቢናፍቁት ወግ ነው ።
አራተኛ፡- ብዙዎች ስለማይለብሱት ሊሆን ይችላል ። አንዳንድ ሰዎች ብዙዎች የለበሱትን ይጠሉታል ። ከፋብሪካው በራሳቸው ስም የታተመ ልብስ ያሠራሉ ። ከጀማው ጋር መጋፋት ድሀ መሆን ይመስላቸዋል ። በእውነት ልብስ የሀብት ማሳያ መሆኑ ዕድሜ ለቻይና ጊዜው ያለፈ ሆኗል።
አምስተኛ፡- ለማጭበርበር ሊሆን ይችላል ። ሙሉ ልብስ ለብሰው ፣ ፕሮቶኮላቸውን ጠብቀው ፣ እንግሊዝኛ እያወሩ ፣ ትልልቅ ሀብትን እየተነተኑ የሚዘርፉ ብዙዎች ናቸው ። ለእነዚህ ሰዎች ልጃቸውን መዳር የሚፈልጉ ብዙ ሴት ወይዘሮዎች አሉ ። እነዚህን ማግባት የሚፈልጉ ብዙ ሀብታም ሴቶች ሊኖሩ ይችላሉ ። “እህ ትበል እናትሽ ልብሴን አይታ የዳረችሽ” የሚባለው ታሪክ የደረሰባቸው ሴቶች ብዙ ናቸው ። ውድ መኪኖችን ተከራይተው የሚያጭበረብሩ አያሌ ናቸው ። የትልልቅ ተቋማት መኪኖችን በመያዝ ባለሥልጣን ነኝ እያሉ ሞኞችን ገደል የሚከትቱ የተካኑ ሌቦችን ይህች ከተማ ይዛለች ። ቤቶቹና ፎቆቹ አፍ ቢኖራቸው ብዙ ይናገሩ ነበር ።
ስድስተኛ፡- ከማኅበረሰቡ ላለመለየት መናኛ የሚለብሱ አሉ ። አንዳንድ ሀብትና ሥልጣን ያላቸው ሰዎች “ልብስ ስመርጥ ጊዜ አላጠፋም” ብለው የወደዱትን አንድ ቀለም ያለውን ልብስ ስድስት ይገዛሉ ። ዓመት ሙሉ አንድ ዓይነት ኮት ስለሚለብሱ ልብስ የማይቀይሩ ይመስለናል ። ዛሬ በአንዳንድ ከተሞች የሚታገቱ ሰዎች ለየት ያለ ልብስ የለበሱ ናቸው ። “በሮም ሲኖሩ እንደ ሮማውያን” የሚባለው ለዚህ ነው ። ዓለም ከጉልበት ይልቅ ለጥበብ እጅ ትሰጣለች ። ስንኖር ጠቢብ መሆን መልካም ነው ። የቆዩት ሀብታሞች ብዙ የሚለብሱ አልነበሩም ። በዚህ ምክንያት አንድ ዓይነት ጨርቅ ስለሚለብሱ “ልብሳቸው ላይ አስደግመው ነው” የሚላቸው ብዙ ነበር ።
ሰባተኛ፡- የሥራ ጠባያቸው ስለሚያስገድዳቸው የሚለብሱ አሉ ። የባንክ ፣ የሆቴል ፣ የተለያዩ ተቋማት ሠራተኞች ሙሉ ልብስ እንዲለብሱ ይገደዳሉ ። ባንኮች አንድ ተራ አለባበስ የለበሰ ሠራተኛ ቢያስቀምጡ ኖሮ ማንም አምኖ ገንዘብ አያስቀምጥም ነበር ። ትምህርት ቤቶች የተማሪዎችን አንድ ዓይነት ልብስ መደንገጋቸው ያስመሰግናል ። በቤተ ክርስቲያንም ሁሉም ነጭና ርካሽ ነጠላ ለብሶ ማስቀደሱ ትልቅ ጥበብ ነው ። በሌሎች አብያተ ክርስቲያናት የልብስና የጫማ ውድድር አድክሞአቸዋል ። አስተማሪያቸውም የሚያወራው ልብሱን ከየት አገር እንዳስመጣው ነው ። ድሀ እዚህ መሐል ምን ይሠራል !
ስንለብስ በአቅማቸው አነስ ያሉ ሰዎች ያሉበት ከሆነ እንዳናሳቅቃቸው መጠንቀቅ ያስፈልጋል ። ያላቸውን አጥበውና ለብሰው በመጡበት ስፍራ ደግሞ ዝቅ ያለ አለባበስ ብንለብስ ይሸማቀቃሉ። ስንለብስ አካባቢውንና ሁኔታውን ማገናዘብ አለብን ። የኀዘንና የሰርግ ልብስ መለየት አለብን። ልቅሶ ቤት ነጭ ለብሰን ብንሄድ “የደስ ደስ መጣ” ብለው ይዘምቱብናል ። ጥቁር መልክ ካለን ነጭ መልበስና ቀይ ከሆንን ጥቁርን ብንለብስ የተሻለ ነው ። ልብሳችን ብዙ ዓይነት ቀለም መከተል የለበትም ። ቢያንስ ከሁለት ቀለም ማለፍ የለብንም ። ጫማችን የልብሳችንን አንደኛውን ቀለም ቢከተል መልካም ነው ። የቀለም ምርጫችን በራሱ የውስጣችንን ማንነት ይገልጣል ።
ልብሳችንን ማጠብና መተኮስ ግድ ነው ። ድሀ የሆነው ወታደር ይህንን የሚያደርግ ከሆነ ሌላው ጎበዝ መሆን አለበት ። ስለ ቆሸሸን ሰው ይሸሸናል እንጂ አያዝንልንም ፣ መንፈሳዊ አድርጎም አይመለከተንም ። በትዳር ላይም አንዱ ወገን ንጽሕናውን የማይጠብቅ ከሆነ መራራቅን ይወልዳል ። እስከ ፍቺም እንደሚደርስ ከልምዳችን መናገር እንችላለን ። ትዳር መግባት ገደል መግባት አይደለምና ራስን መጣል ተገቢ አይደለም ። ራሳችሁን ስትጥሉ እንኳን ሌላው ሊወዳችሁ ራሳችሁንም መቀበል ያቅታችኋል ። ውኃን ርካሽ አድርጎ የሰጠን ጌታ ለንጽሕና ብሎ ነው ። የሥራ ልብስ ፣ የስፖርት ልብስ መለየት አለብን ። ልብሳችንን በመልክ በመልኩ ማስቀመጥ በቀላሉ አይቶ ለመልበስ ይረዳናል ። ብዙ ጨርቅ ማብዛትም በሽታ ነው ። ከሁሉ በላይ እኛ ለምናየው ለውስጥ ልብሶቻችን ዋጋ መስጠት አለብን ። አደራ ሙሉ ልብስ ለብሰን ፣ የተቀደደ ካልሲ ማድረግ ራስን መናቅ ነው ። ያየ ሰውም ይንቀናል ። “ውስጡን ለቄስ “ ብሎ ይተርትብናል ። ለውስጥ ልብሶቻችን ንጽሕና ትልቅ ዋጋ መስጠት አለብን ።
ሰማይን በከዋክብት ፣ ምድርን በአበባ ያስጌጠ እግዚአብሔር እኛም በሥርዓት እንድንለብስ ይፈልጋል ! አልባሽ እርሱ ነውና “የዕለት ጉርሴን ፣ የዓመት ልብሴን ስጠን” እንለዋለን ።
ይቀጥላል
ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ሚያዝያ 5 ቀን 2016 ዓ.ም.
የዘመናችን ፈተና 8
መለኪያ መጥፋት
በ#ዲያቆን #አሸናፊ #መኮንን የተዘጋጀ ስብከት
አሁን በቴሌግራም ቻናል ይለቀቃል ። ይከታተሉ
የዲያቆን አሸናፊ መኰንን ትምህርቶችና ስብከቶች ለመከታተል ከሥር የተቀመጡትን ገጾች ይመልከቱ፡-
https://hottg.com/Nolawii
https://hottg.com/nolawisebketoch
https://www.facebook.co m/ashenafi.mekonnen.357
https://youtu.be/3qfQp9yYmHY
www.ashenafimekonen.com
መለኪያ መጥፋት
በ#ዲያቆን #አሸናፊ #መኮንን የተዘጋጀ ስብከት
አሁን በቴሌግራም ቻናል ይለቀቃል ። ይከታተሉ
የዲያቆን አሸናፊ መኰንን ትምህርቶችና ስብከቶች ለመከታተል ከሥር የተቀመጡትን ገጾች ይመልከቱ፡-
https://hottg.com/Nolawii
https://hottg.com/nolawisebketoch
https://www.facebook.co m/ashenafi.mekonnen.357
https://youtu.be/3qfQp9yYmHY
www.ashenafimekonen.com
Telegram
Nolawi ኖላዊ
ይህ ቻናል ኦርቶዶክሳዊ መንፈሳዊ ትምህርቶች የሚተላለፉበት ነው። እግዚአብሔር አገልግሎቱን ያስፋ!
0911699907 ዲያቆን አሸናፊ መኮንን
0911699907 ዲያቆን አሸናፊ መኮንን
መስፈርት የሌለበት ዘመን
(የወጣት አገልጋይ ፈተና)
ወዳጁን ለማግኘት የሚጓዝ እግር በደመና ላይ እንደሚንሳፈፍ ያህል ይሰማዋል ። ሩቅ መንገድ በፍቅር ምክንያት ቅርብ ነው ። ተራራውን ሜዳ ፣ ሸለቆውን ሙሉ የማድረግ አቅም ወትሮም የፍቅር ነው ። ብዙ ዓይነት ፍቅር ባለበት ዓለም ላይ ብዙ ዓይነት ወዳጆችም አሉ ። ወላጆች ፣ አብሮ አደጎች ፣ የሙያ አጋሮች ፣ የትዳር ጓዶች ፣ ልጆች … ወዳጆች ተብለው ይጠራሉ ። የመምህርና የተማሪ ፍቅር ግን ከዚህ ሁሉ ይለያል ፤ ይበልጣልም ። የፍቅሩ መሠረት በሥጋ መወለድ ሳይሆን ከእግዚአብሔር መወለድ ነው ። ግቡም ምድራዊ ርስት ማውረስ ሳይሆን ሰማይ ማድረስ ነው ። ሩቅ መንገድ የሚጓዝ ፍቅር መንፈሳዊ ብቻ ነው ። ምድራዊው ፍቅር ከፊት ወረት ፣ ከኋላ ሞት ይገድበዋል ። ቅዱስ ጳውሎስ በጸሎት ምጥ ፣ በአገልግሎት ጭንቅ የወለደኝ መንፈሳዊ አባት ነው ። እኔ ለኤፌሶን ምእመናን አባት ብሆንም የእኔ አባት ግን እርሱ ነው ። እርሱን ለማግኘት ያውም በመጨረሻው የዕድሜ ዘመኑ ጥሪውን ተቀብዬ ስመጣ ትልቅ ደስታ ይሰማኛል ። በአንድ ዓይኔ አለቅሳለሁ ፣ መሄጃው ጊዜ ደርሷልና ። ምድር መካሪዋን ስታጣ ትጨነቃለች ። በሁለተኛው ዓይኔ እስቃለሁ ። መምህሬን ላገኝ ነውና ።
ተማሪ መምህሩን በጣም ከመውደዱ የተነሣ የአባቱን ስም በመምህሩ ይቀይራል ። ያማረ ምግብ ሲያገኝ ወጣትነቱና የመብላት ፍላጎቱ ሳያሸንፈው “ይህን ለመምህሬ” ይላል ። የመምህሩን እግር እያጠበ ዘወትር ይመረቃል ። መምህሩንም ሲጠራ “የኔታ” ይላል ፣ የኔ ጌታ ማለት ነው ። ፍቅሩ ታላቅ አክብሮት ያለበት ነው ። ተመርቆ የወጣ እንደሆነ በዓመት አንድና ሁለት ጊዜ የቀድሞ ተማሪዎችን አስተባብሮ ፣ ካገኘው ላይ በረከት ይዞ መምህሩን ይጠይቃል ። መምህሩም ምድራዊ ወገንና ዘመዶቹን ክዶ ተማሪዎቹን ዘመድ አድርጓልና ደስ ይለዋል ። ወጉ ይህ ነው ፤ የመምህርና የተማሪ ወግ የሌለው ዘመን ዘመነ አዳፋ ነው ። ከአባቴ በፊት ነበርሁ የሚል ልጅ በትዕቢት አእምሮውን ያጣ ነው ። በሥጋ መውለድ ልዩ ችሎታ አይደለም ፣ በእውቀት መውለድ ግን ልዩ ተሰጥኦና ትልቅ አባትነትም ነው ። ልደት ያላገኙ አእምሮዎች የገዳይነት ዋሻ ናቸው ። መምህሩ የነፍስ አባት ነውና ነፍስን በእውቀት ይወልዳል ። ሰው ገንዘብ ቢሰጠን ከኪሱ ነው ፣ እውቀት ግን የነፍስ ስጦታ ነውና ከሁሉ ይበልጣል ። መምህራን ክብር ይገባቸዋል ። እንኳን የሰማይን መንገድ ይቅርና “የሮም መንገድ በዚህ በኩል ነው” ያለ ሰው ውለታው አይረሳም ። መምህሩ ሲዋረድ ተማሪ እያነሰ ይመጣል ። ተማሪ ሲጠፋ ትውልድ የጨለማ እስረኛ ይሆናል ። ተማሪ መምህሩን ሲያዋርድ ሰይጣን ታናሽ ወንድም ይሆናል ። መንፈሳውያን መምህራን ክብራቸው ሊመለስ ይገባል። ቀዳሽ ቢቀድስ ፣ ሰባኪ ቢሰብክ ፣ ማኅሌታይ ቢዘምር ምንጩ መምህራን ናቸው ። “ማን ላይ ቆመሽ ፣ ማንን ታሚያለሽ?” እንዲሉ ።
በጉዞዬ ቅዱስ ጳውሎስ ስለ አገልጋዮች መስፈርት የነገረኝን እያስታወስሁ ነበር ። አገልግሎት መስፈርት የለውም ። አገልጋዮች ግን መስፈርት አላቸው ። መስፈሪያው የእግዚአብሔር ቃል ነው ። በምድራዊ መስፈሪያ ተለክተው ሲታጩ የሚፈጥሩት መደናገር ብዙ ነው ። ቤተ መንግሥቱንና ቤተ ክህነቱን ለማገናኘት ባለ ሁለት መታወቂያ ናቸው ተብለው ሲታጩ የማያቋርጥ ማዕበል በቤተ ክርስቲያን ላይ ያመጣሉ ። አዝማደ መንግሥት ናቸው ተብለው ሲሾሙ ከእግዚአብሔር ይልቅ ጎሣቸውን ያገለግላሉ ። በሰው ታምነው ደረጃውን የወጡ የታመኑበት ሲታመም ፣ እነርሱም ትኩሳት ይጀምራቸዋል ። በወኔና በማስፈራራት ስፍራ ሲሰጣቸው ደጋጎችን ስፍራ ይነሣሉ ። በጉቦና በመማለጃ አባት ልሁን ሲሉ አባትነት ስጦታ እንጂ ግዥ አይደለምና ለብዙዎች መጥፋት ምክንያት ይሆናሉ ። “ነውር ካለባቸው ይታዘዛሉ” ተብለው በማሸማቀቂያ ካርድ ሲሾሙ “ከዚህ በኋላ ማን ይነቀንቀኛል ? ለራሱ ሲል ሁሉም ይጠብቀኛል” ብለው ክፋታቸውን ሕጋዊ ያደርጉታል ። መስፈርት የሌለው ግለሰብ የቆሻሻ መጣያ ነው ። መስፈርት የሌለው አገር ሲመክን የሚኖር ነው ። መስፈርት የሌላት ቤተ ክርስቲያን እንደ ድመት ወልዳ የምትበላ ናት ። መስፈርት ያስፈልጋል ። በእውነት መስፈርት ቢኖር የተገፋው ባለወንበሩ ፣ የተነቀፈው ባለ ሙያው መሆኑ ይታወቅ ነበር ። ቤተ ክርስቲያን ዘመድ ማፍሪያ ፣ የወንዝ ለወንዝ ጨዋታ መናኸሪያ ስትሆን ከነገድ ከቋንቋ የዋጃት ክርስቶስ ያዝናል ። መጥቀምና መጠቃቀም ለቤተ ክርስቲያን የጉዳት ዘመንን ያመጣባታል ። በቤተ ክርስቲያን ለተቸገሩት እርዳታ እንጂ ሥልጣን አይሰጥም ። ላልተማረና መንፈሳዊነት ለሌለው ሥልጣን መስጠት ለእብድ ሰይፍ መስጠት ነው ።
ይህን እያሰብሁ ከሮም ሕንፃዎች ጋር አወራ ነበር ። አዎ መስፈርት ያስፈልጋል ። መስፈርቶቹም ወደ አእምሮዬ ይመጣሉ ። መስፈርት ሲጠፋ ወጣቱ አገልጋይ መስፈርት በሌላቸው ሰዎች እየታወከ ይመጣል ።
ጢሞቴዎስ ነኝ ክፍል 13
ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ሚያዝያ 7 ቀን 2016 ዓ.ም.
(የወጣት አገልጋይ ፈተና)
ወዳጁን ለማግኘት የሚጓዝ እግር በደመና ላይ እንደሚንሳፈፍ ያህል ይሰማዋል ። ሩቅ መንገድ በፍቅር ምክንያት ቅርብ ነው ። ተራራውን ሜዳ ፣ ሸለቆውን ሙሉ የማድረግ አቅም ወትሮም የፍቅር ነው ። ብዙ ዓይነት ፍቅር ባለበት ዓለም ላይ ብዙ ዓይነት ወዳጆችም አሉ ። ወላጆች ፣ አብሮ አደጎች ፣ የሙያ አጋሮች ፣ የትዳር ጓዶች ፣ ልጆች … ወዳጆች ተብለው ይጠራሉ ። የመምህርና የተማሪ ፍቅር ግን ከዚህ ሁሉ ይለያል ፤ ይበልጣልም ። የፍቅሩ መሠረት በሥጋ መወለድ ሳይሆን ከእግዚአብሔር መወለድ ነው ። ግቡም ምድራዊ ርስት ማውረስ ሳይሆን ሰማይ ማድረስ ነው ። ሩቅ መንገድ የሚጓዝ ፍቅር መንፈሳዊ ብቻ ነው ። ምድራዊው ፍቅር ከፊት ወረት ፣ ከኋላ ሞት ይገድበዋል ። ቅዱስ ጳውሎስ በጸሎት ምጥ ፣ በአገልግሎት ጭንቅ የወለደኝ መንፈሳዊ አባት ነው ። እኔ ለኤፌሶን ምእመናን አባት ብሆንም የእኔ አባት ግን እርሱ ነው ። እርሱን ለማግኘት ያውም በመጨረሻው የዕድሜ ዘመኑ ጥሪውን ተቀብዬ ስመጣ ትልቅ ደስታ ይሰማኛል ። በአንድ ዓይኔ አለቅሳለሁ ፣ መሄጃው ጊዜ ደርሷልና ። ምድር መካሪዋን ስታጣ ትጨነቃለች ። በሁለተኛው ዓይኔ እስቃለሁ ። መምህሬን ላገኝ ነውና ።
ተማሪ መምህሩን በጣም ከመውደዱ የተነሣ የአባቱን ስም በመምህሩ ይቀይራል ። ያማረ ምግብ ሲያገኝ ወጣትነቱና የመብላት ፍላጎቱ ሳያሸንፈው “ይህን ለመምህሬ” ይላል ። የመምህሩን እግር እያጠበ ዘወትር ይመረቃል ። መምህሩንም ሲጠራ “የኔታ” ይላል ፣ የኔ ጌታ ማለት ነው ። ፍቅሩ ታላቅ አክብሮት ያለበት ነው ። ተመርቆ የወጣ እንደሆነ በዓመት አንድና ሁለት ጊዜ የቀድሞ ተማሪዎችን አስተባብሮ ፣ ካገኘው ላይ በረከት ይዞ መምህሩን ይጠይቃል ። መምህሩም ምድራዊ ወገንና ዘመዶቹን ክዶ ተማሪዎቹን ዘመድ አድርጓልና ደስ ይለዋል ። ወጉ ይህ ነው ፤ የመምህርና የተማሪ ወግ የሌለው ዘመን ዘመነ አዳፋ ነው ። ከአባቴ በፊት ነበርሁ የሚል ልጅ በትዕቢት አእምሮውን ያጣ ነው ። በሥጋ መውለድ ልዩ ችሎታ አይደለም ፣ በእውቀት መውለድ ግን ልዩ ተሰጥኦና ትልቅ አባትነትም ነው ። ልደት ያላገኙ አእምሮዎች የገዳይነት ዋሻ ናቸው ። መምህሩ የነፍስ አባት ነውና ነፍስን በእውቀት ይወልዳል ። ሰው ገንዘብ ቢሰጠን ከኪሱ ነው ፣ እውቀት ግን የነፍስ ስጦታ ነውና ከሁሉ ይበልጣል ። መምህራን ክብር ይገባቸዋል ። እንኳን የሰማይን መንገድ ይቅርና “የሮም መንገድ በዚህ በኩል ነው” ያለ ሰው ውለታው አይረሳም ። መምህሩ ሲዋረድ ተማሪ እያነሰ ይመጣል ። ተማሪ ሲጠፋ ትውልድ የጨለማ እስረኛ ይሆናል ። ተማሪ መምህሩን ሲያዋርድ ሰይጣን ታናሽ ወንድም ይሆናል ። መንፈሳውያን መምህራን ክብራቸው ሊመለስ ይገባል። ቀዳሽ ቢቀድስ ፣ ሰባኪ ቢሰብክ ፣ ማኅሌታይ ቢዘምር ምንጩ መምህራን ናቸው ። “ማን ላይ ቆመሽ ፣ ማንን ታሚያለሽ?” እንዲሉ ።
በጉዞዬ ቅዱስ ጳውሎስ ስለ አገልጋዮች መስፈርት የነገረኝን እያስታወስሁ ነበር ። አገልግሎት መስፈርት የለውም ። አገልጋዮች ግን መስፈርት አላቸው ። መስፈሪያው የእግዚአብሔር ቃል ነው ። በምድራዊ መስፈሪያ ተለክተው ሲታጩ የሚፈጥሩት መደናገር ብዙ ነው ። ቤተ መንግሥቱንና ቤተ ክህነቱን ለማገናኘት ባለ ሁለት መታወቂያ ናቸው ተብለው ሲታጩ የማያቋርጥ ማዕበል በቤተ ክርስቲያን ላይ ያመጣሉ ። አዝማደ መንግሥት ናቸው ተብለው ሲሾሙ ከእግዚአብሔር ይልቅ ጎሣቸውን ያገለግላሉ ። በሰው ታምነው ደረጃውን የወጡ የታመኑበት ሲታመም ፣ እነርሱም ትኩሳት ይጀምራቸዋል ። በወኔና በማስፈራራት ስፍራ ሲሰጣቸው ደጋጎችን ስፍራ ይነሣሉ ። በጉቦና በመማለጃ አባት ልሁን ሲሉ አባትነት ስጦታ እንጂ ግዥ አይደለምና ለብዙዎች መጥፋት ምክንያት ይሆናሉ ። “ነውር ካለባቸው ይታዘዛሉ” ተብለው በማሸማቀቂያ ካርድ ሲሾሙ “ከዚህ በኋላ ማን ይነቀንቀኛል ? ለራሱ ሲል ሁሉም ይጠብቀኛል” ብለው ክፋታቸውን ሕጋዊ ያደርጉታል ። መስፈርት የሌለው ግለሰብ የቆሻሻ መጣያ ነው ። መስፈርት የሌለው አገር ሲመክን የሚኖር ነው ። መስፈርት የሌላት ቤተ ክርስቲያን እንደ ድመት ወልዳ የምትበላ ናት ። መስፈርት ያስፈልጋል ። በእውነት መስፈርት ቢኖር የተገፋው ባለወንበሩ ፣ የተነቀፈው ባለ ሙያው መሆኑ ይታወቅ ነበር ። ቤተ ክርስቲያን ዘመድ ማፍሪያ ፣ የወንዝ ለወንዝ ጨዋታ መናኸሪያ ስትሆን ከነገድ ከቋንቋ የዋጃት ክርስቶስ ያዝናል ። መጥቀምና መጠቃቀም ለቤተ ክርስቲያን የጉዳት ዘመንን ያመጣባታል ። በቤተ ክርስቲያን ለተቸገሩት እርዳታ እንጂ ሥልጣን አይሰጥም ። ላልተማረና መንፈሳዊነት ለሌለው ሥልጣን መስጠት ለእብድ ሰይፍ መስጠት ነው ።
ይህን እያሰብሁ ከሮም ሕንፃዎች ጋር አወራ ነበር ። አዎ መስፈርት ያስፈልጋል ። መስፈርቶቹም ወደ አእምሮዬ ይመጣሉ ። መስፈርት ሲጠፋ ወጣቱ አገልጋይ መስፈርት በሌላቸው ሰዎች እየታወከ ይመጣል ።
ጢሞቴዎስ ነኝ ክፍል 13
ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ሚያዝያ 7 ቀን 2016 ዓ.ም.
የሕይወት ሥነ ሥርዓት (12)
9- ሰላምታ ስጥ
ሰላምታ የግንኙነት የመጀመሪያው ምዕራፍ ነው ። ሰላምታ የወዳጅነት ፣ የናፍቆት ፣ የስብሰባ ፣ የስብከት ፣ የደብዳቤ ፣ የአዋጅ ፣ የቃለ ምዕዳን መክፈቻ ነው ። ሰላምታ የተቋማት መግለጫ ነው። ካህን ፣ ወታደር ፣ እስካውት ፣ ስፖርተኛ ፣ ሙስሊም ፣ ክርስቲያን በሰላምታ ይለያል ። ሰላምታ እንስሳት እንኳ ሲገናኙ በቋንቋቸው የሚገልጡት የፍቅር ንባብ ነው ። ሰዎች እንስሳትን ፣ እንስሳት ሰዎችን በሰላምታ ይቀበላሉ ። ሰላምታ ለሚያውቁት ሰው ብቻ ሳይሆን ለማያውቁት ሰውም የሚሰጥ ስጦታ ነው ። ሰላምታ በሃይማኖት ዓለም አምልኮ ነው ። በሰላምታ የሚመሰገነው እግዚአብሔር ነውና ። ሰላምታ በሰላም የመምጣታችን ማስገንዘቢያ ነው ። ሰላምታ ካልሰጠን ሰዎች በክፉ እንደመጣን ገምተው በክፉ ይዘጋጃሉ ። ሰላምታ የሰውን ልብ የምናስከፍትበት የመጀመሪያው የደወል ድምፅ ነው ። አንድ ሙሉ ሰው ሰላምታ ማቅረብ የሚችል ሰው መሆን አለበት ። ልጆችን ገና በጠዋቱ ሰላምታ መስጠትን ማለማመድ አለብን ። “ሰላምታ ስጡ” ስለሚባል ሰላምታ ስጦታ ነው። ሁሉም ሰው መስጠት የሚችለው ስጦታ ነው ።
የአንዳንድ ሰዎች ሰላምታ በጣም ይማርካል ። “ምነው ሰላም ባሉኝ!” በማለት ሰው ሁሉ ይጓጓል ። ሰላምታ ሰውነትና መንፈሳዊነት ባላቸው ትውልዶች የተከበረ ዕንቈ ነው ። ገንዘብን እንጂ ፍቅርን ለማይፈልግ ሆድ አደር ትውልድ ግን ሰላምታ ጊዜ ማጥፊያ ነው ። በአገራችን እስከ ቅርብ ዓመታት በመንገድ የተገናኘ ሰው ሰላምታ ይለዋወጣል ። ከየት እንደ መጣ ፣ ወዴት እንደሚሄድ አውርቶ የአቅሙን ያህል ድጋፍ ያደርጋል ። አሁንም በገጠሩ ሰውና ሰው ሲገናኝ ሰላምታ ይሰጣጣል ። “ከብት እንኳ ሲገናኝ እምቧ ይባባል ።” ሰው ሰውን ሲያገኝ ሰላም ሊል ይገባዋል ። በየመንገዱ ቆም ብለን የምንለዋወጠው ሰላምታ የራሳችንን ዋጋ የሚጨምር ፣ ደስታን የሚያጎናጽፍ ነው። ደግሞም መነጋገር ትልቁ የአእምሮ ጭንቀት ማስተንፈሻ ነው ። ከንግግር ውስጥ ብልሃት ይገኛል ። በአገራችን አንዱ የአንዱ የሥነ ልቡናው አካሚ ሆኖ ኖሯል ። ብዙ ችግር ቢኖርም ጭንቀት እንዳይኖር ብዙ ማስተንፈሻዎች ነበሩ ። ልቅሶውን ፣ ኀዘኑን ፣ ጭንቀቱን የምናስተናግድበት የዜማ መንገዶች ፣ የግጥም ድርድሮች አሉን ። በመድኃኒት ከሚገኝ ፈውስ በእርስ በርስ ፍቅር የሚገኝ ፈውስ ትልቅ ዋጋ ያለው ነው ።
የሰላምታ ባለጠጋ መሆን አለብህ ። ጌታ በትእዛዝ ቃሉ፡- “ሰላምታ ስጡ” ብሏል ። (ማቴ. 10 ፡ 13 ።) ወደ ቤት ስትገባ ፣ ወደ ሥራህ ስትሰማራ ፣ ስብሰባ ስትከፍት ሰላምታ መስጠት አለብህ ። ሰላምታህ ለቀጣይ ጉዳይ በር ከፋች ነው ። በሩ ካልተከፈተ ማለፍ እንደማይቻል ሰላምታህ ውጤታማ ካልሆነ ምንም መስጠትና መቀበል አትችልም ። ሰላምታህን ከሚጎዱ ነገሮች ውስጥ ጥቂቱን እንይ ። ጨፍጋጋና ኮስታራ ፣ ቍጠኛ ፊት ሰላምታን ይጎዳል ። ፈገግ ማለት የራስህንም ቆዳ ማፍታታት ነው ። ደግሞም እውነተኛ ፈገግታ ከፀሐይ ብርሃን ይልቅ ያምራል ። ኑሮ የጨለመባቸው ባንተ እውነተኛ ፈገግታ ሊበራላቸው ይችላል ። “ለካ ዛሬም ፈገግታና ሳቅ አለ” እንዲሉ ያደርጋቸዋል ። ስለ ተኮሳተርህ አትከበርም ፣ ፈገግ ስላልህ አትናቅም ። የክብር መገኛው ወይ ፍቅር ወይ ፍርሃት ነው ። ፍርሃት የሚያመጣው ክብር ሰዎችን እንዲሸሹህ ያደርጋል ። የፍቅር አክብሮት ግን እንደ ማለዳ ፀሐይ ብርሃኑን እየጨመረ እንደሚሄድ ነው ።
ሰላምታህን የሚጎዳው ኩራት ያለበት ድምፀትህ ነው ። ከመሬት ተነሥቶ ልጥጥ የሚል ሰው አትሁን ። ቃላትህንም እያስረዘምህና እየበጣጠስህ ከአፍህ አታውጣ ። ወንበር ሠርተህ ካልነገሥሁ አትበል ። ትዕቢት ራስን በቅጡ ያለማወቅ ውጤት ነው ። ደግሞም የባዶነት ማሳያ ነው ። ዓለት ጉብ ብሎ ፣ ከብዶ የሚኖር ነው ። ሲፈረከስና ራሱን ሲያሳንስ ግን ቤት መሥሪያ ፣ መንገድ ማውጫ የሚሆን ነው ። ጠቃሚ የምትሆነው በትሕትና ብቻ ነው ። የገዛ ክንፏ የከበዳት ወፍ መብረር አትችልም ። ትዕቢትም ራስን ማክበድ ፣ የራስን ሬሳ መሸከም ነው ። ። ሰላምታን የሚጎዳው ሌላው የምትመርጣቸው ቃላት ናቸው ። ሰዓቶችን ለይ ። ማታ ላይ እንዴት አደራችሁ? አይባልም ። ሰላምታ ስትሰጥ ከቀልብህ መሆን አለብህ ። ደግሞም የሰዎችን መዐረግ ማወቅና በመዐረጋቸው መሠረት መጥራት አለብህ ። ሰላምታህ በሚያግባባችሁ ነገሮች ብቻ የታጀበ መሆን አለበት ። ገና ከበር ጠብ የሚጀምር ባለጌ ነው ። ቅሬታ ሰላምታህን ይጎዳዋልና አስቀድመህ መፍታት አለብህ ።
ሰላምታ አልችልም አይባልም ። በሕይወት ውስጥ ትንሹና ቀላሉ ነገር እርሱ ነውና ። ምናልባት ተፋትተው ይሆናልና በሰላምታህ ዳር ዳሩን በል እንጂ ወደ ትዳሩ አትግባ ። ምናልባት ሞቶበት ይሆናልና “እገሌስ?” ብለህ ስትጠይቅ ጠንቃቃ ሁን ። ምናልባት ከፍቶት ይሆናልና በቀልድ አትጀምር ። ሰላምታህ ግን ያንን ሰው ነጻነት የሚሰጠው መሆን አለበት ። ይልቁንም ወደ ቤትህ የመጣው ሰው ለመቆየትም ላለመቆየትም የሚወስነው በሰላምታህ መጠን ነው ። አንተ በዚህ ምድር ላይ ቤት የለህምና በቤትህ እንግዳ የሆንከው አንተ ሆይ ! እንግዳ ተቀበል ።
ሰላምታህ አባት የሆነ እንደሁ ጉልበትና እጁን መሳም ያስፈልግሃል ። ፓትርያርክ እንደሆነ ብፁዕ አባታችን አይባልም ። ቅዱስ አባታችን ወይም ብፁዕ ወቅዱስ እያልህ ሰላምታህን አቅርብ ። ጳጳስ የሆነ እንደሁ ብፁዕ አባታችን ብለህ ጥራ ። የሲኖዶስ አባላት ፊት ስትቆም ቅዱስ አባታችን፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ብለህ በየመዐርጉ ሰላምታ አቅርብ ። መሳይና ወዳጅህን ስታገኝ እንደ ቅርበትህ በእጅህ ጨብጥ ። እንደ ቅርበትህ መሳሳምን አትርሳ ። ይሁዳ ጌታን ስሞታል ። በእውነት ቢሆን መልካም ነበረ ። በእውነት መሳም የፍቅር መግለጫ ነው ። ሕፃናት ከሆኑም የምታውቀውን ሕፃን ስትስም የማታውቃቸውንም ሕፃናት አብረህ ሳም ። ስታዋራቸውም በርከክ ብለህ ፊት ለፊት እያየህ አዋራቸው ። አንድ ቀን አድገው “ያን ጊዜ ሕፃን ሳለን ታከብረን ነበር” ብለው ሊያመሰግኑህ ይመጣሉ ። የሰው ሚስትና እጮኛን በጣም ሰላም ማለትና መቀራረብን ተዉ ። ባልዋ በሌለበትም የሰው ቤት አትሂድ ። ወደ ባል ስትደውል “ሚስትህን ሰላም በልልኝ” በል ። ማንንም ሰው ስታገኝ አንገትህን ዘንበል አድርገህ ሰላም በል ። ሰው ልዑል ፣ የንጉሥ ልጅ ነውና ። ማክበር መከበር ነው ። ክብርህን ግዛው እንጂ አትሽጠው ። ባለጌንም ከወዳጅህ ጋር አታስተዋውቅ ። ምንም ቢከፋህ የልብህን ችግር በፊትህ አደባባይ ላይ አታስነብብ ። እዚህ ላይ ላቆም እንዳላደክምህ !
ሰላም ይብዛልህ !
ይቀጥላል
ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ሚያዝያ 9 ቀን 2016 ዓ.ም.
9- ሰላምታ ስጥ
ሰላምታ የግንኙነት የመጀመሪያው ምዕራፍ ነው ። ሰላምታ የወዳጅነት ፣ የናፍቆት ፣ የስብሰባ ፣ የስብከት ፣ የደብዳቤ ፣ የአዋጅ ፣ የቃለ ምዕዳን መክፈቻ ነው ። ሰላምታ የተቋማት መግለጫ ነው። ካህን ፣ ወታደር ፣ እስካውት ፣ ስፖርተኛ ፣ ሙስሊም ፣ ክርስቲያን በሰላምታ ይለያል ። ሰላምታ እንስሳት እንኳ ሲገናኙ በቋንቋቸው የሚገልጡት የፍቅር ንባብ ነው ። ሰዎች እንስሳትን ፣ እንስሳት ሰዎችን በሰላምታ ይቀበላሉ ። ሰላምታ ለሚያውቁት ሰው ብቻ ሳይሆን ለማያውቁት ሰውም የሚሰጥ ስጦታ ነው ። ሰላምታ በሃይማኖት ዓለም አምልኮ ነው ። በሰላምታ የሚመሰገነው እግዚአብሔር ነውና ። ሰላምታ በሰላም የመምጣታችን ማስገንዘቢያ ነው ። ሰላምታ ካልሰጠን ሰዎች በክፉ እንደመጣን ገምተው በክፉ ይዘጋጃሉ ። ሰላምታ የሰውን ልብ የምናስከፍትበት የመጀመሪያው የደወል ድምፅ ነው ። አንድ ሙሉ ሰው ሰላምታ ማቅረብ የሚችል ሰው መሆን አለበት ። ልጆችን ገና በጠዋቱ ሰላምታ መስጠትን ማለማመድ አለብን ። “ሰላምታ ስጡ” ስለሚባል ሰላምታ ስጦታ ነው። ሁሉም ሰው መስጠት የሚችለው ስጦታ ነው ።
የአንዳንድ ሰዎች ሰላምታ በጣም ይማርካል ። “ምነው ሰላም ባሉኝ!” በማለት ሰው ሁሉ ይጓጓል ። ሰላምታ ሰውነትና መንፈሳዊነት ባላቸው ትውልዶች የተከበረ ዕንቈ ነው ። ገንዘብን እንጂ ፍቅርን ለማይፈልግ ሆድ አደር ትውልድ ግን ሰላምታ ጊዜ ማጥፊያ ነው ። በአገራችን እስከ ቅርብ ዓመታት በመንገድ የተገናኘ ሰው ሰላምታ ይለዋወጣል ። ከየት እንደ መጣ ፣ ወዴት እንደሚሄድ አውርቶ የአቅሙን ያህል ድጋፍ ያደርጋል ። አሁንም በገጠሩ ሰውና ሰው ሲገናኝ ሰላምታ ይሰጣጣል ። “ከብት እንኳ ሲገናኝ እምቧ ይባባል ።” ሰው ሰውን ሲያገኝ ሰላም ሊል ይገባዋል ። በየመንገዱ ቆም ብለን የምንለዋወጠው ሰላምታ የራሳችንን ዋጋ የሚጨምር ፣ ደስታን የሚያጎናጽፍ ነው። ደግሞም መነጋገር ትልቁ የአእምሮ ጭንቀት ማስተንፈሻ ነው ። ከንግግር ውስጥ ብልሃት ይገኛል ። በአገራችን አንዱ የአንዱ የሥነ ልቡናው አካሚ ሆኖ ኖሯል ። ብዙ ችግር ቢኖርም ጭንቀት እንዳይኖር ብዙ ማስተንፈሻዎች ነበሩ ። ልቅሶውን ፣ ኀዘኑን ፣ ጭንቀቱን የምናስተናግድበት የዜማ መንገዶች ፣ የግጥም ድርድሮች አሉን ። በመድኃኒት ከሚገኝ ፈውስ በእርስ በርስ ፍቅር የሚገኝ ፈውስ ትልቅ ዋጋ ያለው ነው ።
የሰላምታ ባለጠጋ መሆን አለብህ ። ጌታ በትእዛዝ ቃሉ፡- “ሰላምታ ስጡ” ብሏል ። (ማቴ. 10 ፡ 13 ።) ወደ ቤት ስትገባ ፣ ወደ ሥራህ ስትሰማራ ፣ ስብሰባ ስትከፍት ሰላምታ መስጠት አለብህ ። ሰላምታህ ለቀጣይ ጉዳይ በር ከፋች ነው ። በሩ ካልተከፈተ ማለፍ እንደማይቻል ሰላምታህ ውጤታማ ካልሆነ ምንም መስጠትና መቀበል አትችልም ። ሰላምታህን ከሚጎዱ ነገሮች ውስጥ ጥቂቱን እንይ ። ጨፍጋጋና ኮስታራ ፣ ቍጠኛ ፊት ሰላምታን ይጎዳል ። ፈገግ ማለት የራስህንም ቆዳ ማፍታታት ነው ። ደግሞም እውነተኛ ፈገግታ ከፀሐይ ብርሃን ይልቅ ያምራል ። ኑሮ የጨለመባቸው ባንተ እውነተኛ ፈገግታ ሊበራላቸው ይችላል ። “ለካ ዛሬም ፈገግታና ሳቅ አለ” እንዲሉ ያደርጋቸዋል ። ስለ ተኮሳተርህ አትከበርም ፣ ፈገግ ስላልህ አትናቅም ። የክብር መገኛው ወይ ፍቅር ወይ ፍርሃት ነው ። ፍርሃት የሚያመጣው ክብር ሰዎችን እንዲሸሹህ ያደርጋል ። የፍቅር አክብሮት ግን እንደ ማለዳ ፀሐይ ብርሃኑን እየጨመረ እንደሚሄድ ነው ።
ሰላምታህን የሚጎዳው ኩራት ያለበት ድምፀትህ ነው ። ከመሬት ተነሥቶ ልጥጥ የሚል ሰው አትሁን ። ቃላትህንም እያስረዘምህና እየበጣጠስህ ከአፍህ አታውጣ ። ወንበር ሠርተህ ካልነገሥሁ አትበል ። ትዕቢት ራስን በቅጡ ያለማወቅ ውጤት ነው ። ደግሞም የባዶነት ማሳያ ነው ። ዓለት ጉብ ብሎ ፣ ከብዶ የሚኖር ነው ። ሲፈረከስና ራሱን ሲያሳንስ ግን ቤት መሥሪያ ፣ መንገድ ማውጫ የሚሆን ነው ። ጠቃሚ የምትሆነው በትሕትና ብቻ ነው ። የገዛ ክንፏ የከበዳት ወፍ መብረር አትችልም ። ትዕቢትም ራስን ማክበድ ፣ የራስን ሬሳ መሸከም ነው ። ። ሰላምታን የሚጎዳው ሌላው የምትመርጣቸው ቃላት ናቸው ። ሰዓቶችን ለይ ። ማታ ላይ እንዴት አደራችሁ? አይባልም ። ሰላምታ ስትሰጥ ከቀልብህ መሆን አለብህ ። ደግሞም የሰዎችን መዐረግ ማወቅና በመዐረጋቸው መሠረት መጥራት አለብህ ። ሰላምታህ በሚያግባባችሁ ነገሮች ብቻ የታጀበ መሆን አለበት ። ገና ከበር ጠብ የሚጀምር ባለጌ ነው ። ቅሬታ ሰላምታህን ይጎዳዋልና አስቀድመህ መፍታት አለብህ ።
ሰላምታ አልችልም አይባልም ። በሕይወት ውስጥ ትንሹና ቀላሉ ነገር እርሱ ነውና ። ምናልባት ተፋትተው ይሆናልና በሰላምታህ ዳር ዳሩን በል እንጂ ወደ ትዳሩ አትግባ ። ምናልባት ሞቶበት ይሆናልና “እገሌስ?” ብለህ ስትጠይቅ ጠንቃቃ ሁን ። ምናልባት ከፍቶት ይሆናልና በቀልድ አትጀምር ። ሰላምታህ ግን ያንን ሰው ነጻነት የሚሰጠው መሆን አለበት ። ይልቁንም ወደ ቤትህ የመጣው ሰው ለመቆየትም ላለመቆየትም የሚወስነው በሰላምታህ መጠን ነው ። አንተ በዚህ ምድር ላይ ቤት የለህምና በቤትህ እንግዳ የሆንከው አንተ ሆይ ! እንግዳ ተቀበል ።
ሰላምታህ አባት የሆነ እንደሁ ጉልበትና እጁን መሳም ያስፈልግሃል ። ፓትርያርክ እንደሆነ ብፁዕ አባታችን አይባልም ። ቅዱስ አባታችን ወይም ብፁዕ ወቅዱስ እያልህ ሰላምታህን አቅርብ ። ጳጳስ የሆነ እንደሁ ብፁዕ አባታችን ብለህ ጥራ ። የሲኖዶስ አባላት ፊት ስትቆም ቅዱስ አባታችን፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ብለህ በየመዐርጉ ሰላምታ አቅርብ ። መሳይና ወዳጅህን ስታገኝ እንደ ቅርበትህ በእጅህ ጨብጥ ። እንደ ቅርበትህ መሳሳምን አትርሳ ። ይሁዳ ጌታን ስሞታል ። በእውነት ቢሆን መልካም ነበረ ። በእውነት መሳም የፍቅር መግለጫ ነው ። ሕፃናት ከሆኑም የምታውቀውን ሕፃን ስትስም የማታውቃቸውንም ሕፃናት አብረህ ሳም ። ስታዋራቸውም በርከክ ብለህ ፊት ለፊት እያየህ አዋራቸው ። አንድ ቀን አድገው “ያን ጊዜ ሕፃን ሳለን ታከብረን ነበር” ብለው ሊያመሰግኑህ ይመጣሉ ። የሰው ሚስትና እጮኛን በጣም ሰላም ማለትና መቀራረብን ተዉ ። ባልዋ በሌለበትም የሰው ቤት አትሂድ ። ወደ ባል ስትደውል “ሚስትህን ሰላም በልልኝ” በል ። ማንንም ሰው ስታገኝ አንገትህን ዘንበል አድርገህ ሰላም በል ። ሰው ልዑል ፣ የንጉሥ ልጅ ነውና ። ማክበር መከበር ነው ። ክብርህን ግዛው እንጂ አትሽጠው ። ባለጌንም ከወዳጅህ ጋር አታስተዋውቅ ። ምንም ቢከፋህ የልብህን ችግር በፊትህ አደባባይ ላይ አታስነብብ ። እዚህ ላይ ላቆም እንዳላደክምህ !
ሰላም ይብዛልህ !
ይቀጥላል
ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ሚያዝያ 9 ቀን 2016 ዓ.ም.
ተመስገን ጌታዬ
ጸጋህ አይጓደል ተመስገን ጌታዬ ፣
ሁሉን ያረክልኝ ባለውለታዬ ፤
አንድ አለኝ የምልህ ዘወትር ሁልጊዜ ፣
አንተ ነህ ጋሻዬ ደጋፊ ምርኵዜ ።
አቤቱ አምላክ ሆይ የሰማይ አባቴ ፣
አካሌ ሲደክም አንተ ነህ ጉልበቴ ፤
በሰላም በጤና ስኖር በዕድሜ ጸጋ ፣
ምስጋና ብቻ ነው የምሰጥህ ዋጋ ።
የኑሮዬ ባላ የሕይወቴ ቤዛ ፣
ለእኔ ያረክልኝ ውለታህ የበዛ ፤
ተመስገን ፈጣሪ ልበልህ ጠዋት ማታ ፣
ረዳቴ አንተ ነህ የቸገረኝ ለታ ።
ሲርበኝ አጉርሰህ ስታረዝ አልብሰህ ፣
ስጨነቅ አጽናንተህ ስታመም ፈውሰህ ፣
ድረስልኝ ስልህ ስምህን ጠርቼ ፣
የምፈልገውን አላውቅም አጥቼ ።
ቸኩለህ እንደ ሰው ቅጣት የማትሰጠው ፣
ሀብታምና ድሀ የማታስበልጠው ፤
ቸሩ መድኃኔ ዓለም ይድረስህ ምስጋና ፣
ረዳቴ አንተ ነህ በስምህ ልጽናና ።
ለኮንትራት ሕይወት ነገ ለሚቀረው ፣
በመንፈስ አጽናኝ ቃልህን እንዳልሽረው ፤
ኃጢአቴን ሰርዘህ አድነኝ ከዕዳ ፣
መሐሪው አንተ ነህ ለሰው ልጆች ፍዳ ።
እመካብሃለሁ በሰማዩ አባቴ ፣
የፈጠርከኝ አምላክ አውጣኝ ከኃጢአቴ ፤
ሳዝን ፈጥነህ ደራሽ ስከፋ መካሪ ፣
መከታ ጋሻዬ አንተ ነህ ፈጣሪ ፤
ዕዝራ በመሰንቆ ዳዊት በበገና ፣
እንዳቀረቡልህ ለሥራህ ምስጋና ፣
አወድስሃለሁ እኔም በዜማዬ ፣
አንተ ነህ ጠባቂ የሕይወት ጋሻዬ ።
(ምንጭ፡- ዘለሰኛ)
ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ሚያዝያ 10 ቀን 2016 ዓ.ም.
ጸጋህ አይጓደል ተመስገን ጌታዬ ፣
ሁሉን ያረክልኝ ባለውለታዬ ፤
አንድ አለኝ የምልህ ዘወትር ሁልጊዜ ፣
አንተ ነህ ጋሻዬ ደጋፊ ምርኵዜ ።
አቤቱ አምላክ ሆይ የሰማይ አባቴ ፣
አካሌ ሲደክም አንተ ነህ ጉልበቴ ፤
በሰላም በጤና ስኖር በዕድሜ ጸጋ ፣
ምስጋና ብቻ ነው የምሰጥህ ዋጋ ።
የኑሮዬ ባላ የሕይወቴ ቤዛ ፣
ለእኔ ያረክልኝ ውለታህ የበዛ ፤
ተመስገን ፈጣሪ ልበልህ ጠዋት ማታ ፣
ረዳቴ አንተ ነህ የቸገረኝ ለታ ።
ሲርበኝ አጉርሰህ ስታረዝ አልብሰህ ፣
ስጨነቅ አጽናንተህ ስታመም ፈውሰህ ፣
ድረስልኝ ስልህ ስምህን ጠርቼ ፣
የምፈልገውን አላውቅም አጥቼ ።
ቸኩለህ እንደ ሰው ቅጣት የማትሰጠው ፣
ሀብታምና ድሀ የማታስበልጠው ፤
ቸሩ መድኃኔ ዓለም ይድረስህ ምስጋና ፣
ረዳቴ አንተ ነህ በስምህ ልጽናና ።
ለኮንትራት ሕይወት ነገ ለሚቀረው ፣
በመንፈስ አጽናኝ ቃልህን እንዳልሽረው ፤
ኃጢአቴን ሰርዘህ አድነኝ ከዕዳ ፣
መሐሪው አንተ ነህ ለሰው ልጆች ፍዳ ።
እመካብሃለሁ በሰማዩ አባቴ ፣
የፈጠርከኝ አምላክ አውጣኝ ከኃጢአቴ ፤
ሳዝን ፈጥነህ ደራሽ ስከፋ መካሪ ፣
መከታ ጋሻዬ አንተ ነህ ፈጣሪ ፤
ዕዝራ በመሰንቆ ዳዊት በበገና ፣
እንዳቀረቡልህ ለሥራህ ምስጋና ፣
አወድስሃለሁ እኔም በዜማዬ ፣
አንተ ነህ ጠባቂ የሕይወት ጋሻዬ ።
(ምንጭ፡- ዘለሰኛ)
ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ሚያዝያ 10 ቀን 2016 ዓ.ም.
የሕይወት ሥነ ሥርዓት (13)
10- ሥራህን ተግተህ ሥራ
ሥራ እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ከሰጠው ጸጋ አንዱ ነው ። ሥራ ርግማን ሳይሆን በረከት ነው ። አዳም ሲፈጠር ገነትን እንዲያበጃትና እንዲንከባከባትም ነው (ዘፍ. 2 ፡ 15) ። ደግሞም ምድርን ግዛ ተብሎ ሥልጣን ሲሰጠው ትልቅ ሥራ እንደ ተሰጠው ያሳያል ። ምድር ለእርሱ ስጦታው ናትና እንደ ራሱ ገንዘብ አድርጎ መንከባከብ ይገባዋል ። ከበደል በኋላ ግን “በፊትህ ወዝ እንጀራን ትበላለህ” ተባለ (ዘፍ. 3 ፡ 19) ። ይህ ሥራ ርግማን መሆኑን የሚያሳይ ሳይሆን ከበደል በኋላ አዳም ብዙ ልፋት ጥቂት ትርፍ ይገጥመዋል ማለት ነው ። በዚህም ምክንያት እርካታ እያጣ እንደሚመጣ የሚገልጥ ነው ። እያንዳንዱ ሰው ለሚኖርበት ዓለም የሚያደርገው አስተዋጽኦ አለው ። ሰው የሁለት ዓለም ፍጡር ነውና ለምድር ኑሮው መሥራት ፣ ለሰማዩ ኑሮ ማመን አለበት ። ሥራ በረከት ነው ።
በአእምሮ ላይ የሚነሣውን የሰይጣንን ፈተና ለማሸነፍ ሥራና ጸሎት ሁለቱ መሣሪያ መሆናቸውን አባቶች ተናግረዋል ። ሥራ የፈታ አእምሮ ለሰይጣን መናገሻ ከተማ ነው ። ነገረኛ ሰዎች ሥራ የማይሠሩ ወይም አጉል ትርፍ የሚያገኙ ወገኖች ናቸው ። በሥራ የተጠመደ ነገርን ይሸሻል ። ንጹሕ አእምሮ ለማግኘት ሥራ መሥራት መልካም ነው ። ተነፋፍቆ ለመገናኘት ሥራ አስፈላጊ ነው ። የሰው ልጆች ያለማቋረጥ ከተያዩ ግንኙነቱ ይደፈርሳል ። በዓለም ላይ በተነሣው የቅርቡ ወረርሽኝ ሰው ሁሉ እቤቱ እስረኛ ሁኖ ነበር ። ብዙ ትዳር ፈርሷል ። ብዙ ግንኙነት ተበላሽቷል ። ወንጀሎች ተፈጽመዋል ። ሰዎች ለአእምሮ ጭንቀት ተዳርገዋል ። እስካሁን ድረስም ጠባሳው እያወከ ይገኛል ። ሥራ በረከት ነው ። አሁንም በቤታቸው ተቀምጠው የሚሠሩ ሰዎችን በተለያየ ዓለም እንሰማለን ። የሰይጣን ትልቁ ውጊያው ሰውና ሰው እንዳይገናኝ ማድረግ ነው ። ሥራ ያገናኛል ። ሥራ ከቤታችን ውጭ ሲሆን ለብሰን እንወጣለን ። ለራሳችን እንክብካቤ እናደርጋለን ። ከሰዎች ጋር በማውራት ብቻ ነጻ አእምሮ እናገኛለን ። አአምሮአችን ትልቅ ኃይል የተሸከመ ነውና ማረፊያ ያገኛል ። ማረፊያ ያላገኘ አእምሮ ዓለምን ለማጥፋት አቅም አለው ።
ሥራው አለቃ የሆነለት ሰው ውጤታማ ነው ። ሥራ ብዙ እንቅልፍን የሚጠላ በመሆኑ ሠራተኛ ሰው ማልዶ መነሣት አለበት ። ሥራ አካላዊ ፣ ሥነ ልቡናዊና መንፈሳዊ በረከትን ይሰጣል ። አካላችን የሚጠነክረው በሥራ ነው ። የምድር ተግዳሮትን የሚቋቋሙ ሰዎች ሠራተኛ ሰዎች ናቸው ። የዓለም መንግሥታት ትልቅ ስኬታቸውን የሚለኩት የሥራ ዕድልን በመፍጠራቸው ነው ። በአጭር ቋንቋ እግዚአብሔር ሰነፍ ልጅ የለውምና ሥራን መውደድ ይገባናል ። የሐዋርያው ቃልም ቁርጥ ያለ ነው፡- “ሊሠራ የማይወድ አይብላ ።” (2ተሰ. 3 ፡ 10) ። ስብሰባ ፣ ኮሚቴ ፣ ቃለ ጉባዔ የሚሉ ሰዎች አብዛኛዎቹ ሥራ የማይወዱ ፣ ቁጭ ብለው መነዛነዝ የሚያፈቅሩ ናቸው ። ሕይወትን ቀለል አድርጎ መኖር የሚቻለው በስብሰባ ሳይሆን በሥራ ነው ። ጨካኝ መንግሥታት ሕዝባቸውን በስብሰባ ያደነዝዛሉ ። መሪ የሆኑት ደግሞ ሕዝባቸውን ለሥራ ያነሣሣሉ ። ሕዝብን በሥራ መወጠር ከሁከትም ይጋርዳል ።
አዎ ሥራህን በታማኝነት ሥራ ። ጸልየህ ያገኘኸውን ሥራ በትጋት አለመሥራት እግዚአብሔርን ማሳዘን ነው ። ሥራ ታማኝነትና ትጋት ይፈልጋል ። ታማኝነቱ ትጋት ከሌለው ፣ ትጋቱ ታማኝነት ከሌለው አደገኛ ነው ። ሥራህ የሃይማኖትህ ቦታ አይደለም ። በሥራህ ቦታ ሥነ ምግባርን እንጂ አምልኮን ልፈጽም አትበል ። ጉቦን ተጸየፍ ። ደመወዝህ እንዲባረክ ጸልይ ። ጉቦ ያለህንም ይዞት የሚሄድ ፣ ልጆችህንም የሚያሳብድ ነው ። ጉበኞች የብዙዎችን እንባና ደም ተሸክመው ይሄዳሉ ። ሰው ወዶና ፈቅዶ እንጂ ተጨንቆ የሚሰጠን ነገር ርግማን የሚያመጣ ነው ። የሥራ ሰዓትህን አክብር ። ደመወዝህ አነስተኛ በመሆኑ ባለጉዳዩን ማንገላታት አይገባህም ። ባለጉዳይህን ፣ ያንተን ሙያ የሚፈልገውን እግዚአብሔርን እንደምታገለግል አድርገህ አገልግለው ። የሙያህ ባለቤት እግዚአብሔር ነው ። በሙያህ ሰውን አታጉላላ ። አንድ ቀን ይህ አእምሮህ ላይሠራ ይችላል ። እጆችህ ላይሠሩ ይችላሉ ። በሚያልፈው አካልህ የማያልፍ ሥራ ሥራበት ። በሙያ ሰውን ማስደሰት መታደል ነው ። ካንተ የሆነ ምንም ነገር የለም ።
ሥራ የምትሠራው አሥራትህንም ለማውጣት ነው ። ባንተ የሥራ ትርፍ የእግዚአብሔር ቤት ይገነባል ። ብዙዎች ወንጌል ይሰማሉ ። ልጆችህ ጠግበው ያድራሉ ። ትዳርህ አይታወክም ። የብዙ ትዳር ሁከትም የገቢ ማነስ ነው ። ሥራ ትልቅና ትንሽ የለውም ። በምድር ላይ የሚያሳፍረው ቆሻሻ መጥረግ ሳይሆን ቆሻሻ ጠባይ መያዝ ነው ። ጌታችን ለእኛ አርአያ ለመሆን አናጢነትን ሠርቷል ። ቅዱሳን ሁሉ ሥራቸውን በትጋት ሲሠሩ ለሰማያዊ ግዳጅ የተጠሩ ናቸው ። ትጉ ሠራተኛ ትጉህ ሐዋርያ ሊሆን ይጠራል ። ትጋት ተወዳጅ ያደርጋል ። ለክብር ለመታጨት ያበቃል ።
እግዚአብሔር የእጅህን ሥራ ይባርክ !
ይቀጥላል
ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ሚያዝያ 12 ቀን 2016 ዓ.ም.
10- ሥራህን ተግተህ ሥራ
ሥራ እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ከሰጠው ጸጋ አንዱ ነው ። ሥራ ርግማን ሳይሆን በረከት ነው ። አዳም ሲፈጠር ገነትን እንዲያበጃትና እንዲንከባከባትም ነው (ዘፍ. 2 ፡ 15) ። ደግሞም ምድርን ግዛ ተብሎ ሥልጣን ሲሰጠው ትልቅ ሥራ እንደ ተሰጠው ያሳያል ። ምድር ለእርሱ ስጦታው ናትና እንደ ራሱ ገንዘብ አድርጎ መንከባከብ ይገባዋል ። ከበደል በኋላ ግን “በፊትህ ወዝ እንጀራን ትበላለህ” ተባለ (ዘፍ. 3 ፡ 19) ። ይህ ሥራ ርግማን መሆኑን የሚያሳይ ሳይሆን ከበደል በኋላ አዳም ብዙ ልፋት ጥቂት ትርፍ ይገጥመዋል ማለት ነው ። በዚህም ምክንያት እርካታ እያጣ እንደሚመጣ የሚገልጥ ነው ። እያንዳንዱ ሰው ለሚኖርበት ዓለም የሚያደርገው አስተዋጽኦ አለው ። ሰው የሁለት ዓለም ፍጡር ነውና ለምድር ኑሮው መሥራት ፣ ለሰማዩ ኑሮ ማመን አለበት ። ሥራ በረከት ነው ።
በአእምሮ ላይ የሚነሣውን የሰይጣንን ፈተና ለማሸነፍ ሥራና ጸሎት ሁለቱ መሣሪያ መሆናቸውን አባቶች ተናግረዋል ። ሥራ የፈታ አእምሮ ለሰይጣን መናገሻ ከተማ ነው ። ነገረኛ ሰዎች ሥራ የማይሠሩ ወይም አጉል ትርፍ የሚያገኙ ወገኖች ናቸው ። በሥራ የተጠመደ ነገርን ይሸሻል ። ንጹሕ አእምሮ ለማግኘት ሥራ መሥራት መልካም ነው ። ተነፋፍቆ ለመገናኘት ሥራ አስፈላጊ ነው ። የሰው ልጆች ያለማቋረጥ ከተያዩ ግንኙነቱ ይደፈርሳል ። በዓለም ላይ በተነሣው የቅርቡ ወረርሽኝ ሰው ሁሉ እቤቱ እስረኛ ሁኖ ነበር ። ብዙ ትዳር ፈርሷል ። ብዙ ግንኙነት ተበላሽቷል ። ወንጀሎች ተፈጽመዋል ። ሰዎች ለአእምሮ ጭንቀት ተዳርገዋል ። እስካሁን ድረስም ጠባሳው እያወከ ይገኛል ። ሥራ በረከት ነው ። አሁንም በቤታቸው ተቀምጠው የሚሠሩ ሰዎችን በተለያየ ዓለም እንሰማለን ። የሰይጣን ትልቁ ውጊያው ሰውና ሰው እንዳይገናኝ ማድረግ ነው ። ሥራ ያገናኛል ። ሥራ ከቤታችን ውጭ ሲሆን ለብሰን እንወጣለን ። ለራሳችን እንክብካቤ እናደርጋለን ። ከሰዎች ጋር በማውራት ብቻ ነጻ አእምሮ እናገኛለን ። አአምሮአችን ትልቅ ኃይል የተሸከመ ነውና ማረፊያ ያገኛል ። ማረፊያ ያላገኘ አእምሮ ዓለምን ለማጥፋት አቅም አለው ።
ሥራው አለቃ የሆነለት ሰው ውጤታማ ነው ። ሥራ ብዙ እንቅልፍን የሚጠላ በመሆኑ ሠራተኛ ሰው ማልዶ መነሣት አለበት ። ሥራ አካላዊ ፣ ሥነ ልቡናዊና መንፈሳዊ በረከትን ይሰጣል ። አካላችን የሚጠነክረው በሥራ ነው ። የምድር ተግዳሮትን የሚቋቋሙ ሰዎች ሠራተኛ ሰዎች ናቸው ። የዓለም መንግሥታት ትልቅ ስኬታቸውን የሚለኩት የሥራ ዕድልን በመፍጠራቸው ነው ። በአጭር ቋንቋ እግዚአብሔር ሰነፍ ልጅ የለውምና ሥራን መውደድ ይገባናል ። የሐዋርያው ቃልም ቁርጥ ያለ ነው፡- “ሊሠራ የማይወድ አይብላ ።” (2ተሰ. 3 ፡ 10) ። ስብሰባ ፣ ኮሚቴ ፣ ቃለ ጉባዔ የሚሉ ሰዎች አብዛኛዎቹ ሥራ የማይወዱ ፣ ቁጭ ብለው መነዛነዝ የሚያፈቅሩ ናቸው ። ሕይወትን ቀለል አድርጎ መኖር የሚቻለው በስብሰባ ሳይሆን በሥራ ነው ። ጨካኝ መንግሥታት ሕዝባቸውን በስብሰባ ያደነዝዛሉ ። መሪ የሆኑት ደግሞ ሕዝባቸውን ለሥራ ያነሣሣሉ ። ሕዝብን በሥራ መወጠር ከሁከትም ይጋርዳል ።
አዎ ሥራህን በታማኝነት ሥራ ። ጸልየህ ያገኘኸውን ሥራ በትጋት አለመሥራት እግዚአብሔርን ማሳዘን ነው ። ሥራ ታማኝነትና ትጋት ይፈልጋል ። ታማኝነቱ ትጋት ከሌለው ፣ ትጋቱ ታማኝነት ከሌለው አደገኛ ነው ። ሥራህ የሃይማኖትህ ቦታ አይደለም ። በሥራህ ቦታ ሥነ ምግባርን እንጂ አምልኮን ልፈጽም አትበል ። ጉቦን ተጸየፍ ። ደመወዝህ እንዲባረክ ጸልይ ። ጉቦ ያለህንም ይዞት የሚሄድ ፣ ልጆችህንም የሚያሳብድ ነው ። ጉበኞች የብዙዎችን እንባና ደም ተሸክመው ይሄዳሉ ። ሰው ወዶና ፈቅዶ እንጂ ተጨንቆ የሚሰጠን ነገር ርግማን የሚያመጣ ነው ። የሥራ ሰዓትህን አክብር ። ደመወዝህ አነስተኛ በመሆኑ ባለጉዳዩን ማንገላታት አይገባህም ። ባለጉዳይህን ፣ ያንተን ሙያ የሚፈልገውን እግዚአብሔርን እንደምታገለግል አድርገህ አገልግለው ። የሙያህ ባለቤት እግዚአብሔር ነው ። በሙያህ ሰውን አታጉላላ ። አንድ ቀን ይህ አእምሮህ ላይሠራ ይችላል ። እጆችህ ላይሠሩ ይችላሉ ። በሚያልፈው አካልህ የማያልፍ ሥራ ሥራበት ። በሙያ ሰውን ማስደሰት መታደል ነው ። ካንተ የሆነ ምንም ነገር የለም ።
ሥራ የምትሠራው አሥራትህንም ለማውጣት ነው ። ባንተ የሥራ ትርፍ የእግዚአብሔር ቤት ይገነባል ። ብዙዎች ወንጌል ይሰማሉ ። ልጆችህ ጠግበው ያድራሉ ። ትዳርህ አይታወክም ። የብዙ ትዳር ሁከትም የገቢ ማነስ ነው ። ሥራ ትልቅና ትንሽ የለውም ። በምድር ላይ የሚያሳፍረው ቆሻሻ መጥረግ ሳይሆን ቆሻሻ ጠባይ መያዝ ነው ። ጌታችን ለእኛ አርአያ ለመሆን አናጢነትን ሠርቷል ። ቅዱሳን ሁሉ ሥራቸውን በትጋት ሲሠሩ ለሰማያዊ ግዳጅ የተጠሩ ናቸው ። ትጉ ሠራተኛ ትጉህ ሐዋርያ ሊሆን ይጠራል ። ትጋት ተወዳጅ ያደርጋል ። ለክብር ለመታጨት ያበቃል ።
እግዚአብሔር የእጅህን ሥራ ይባርክ !
ይቀጥላል
ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ሚያዝያ 12 ቀን 2016 ዓ.ም.
የዘመናችን ፈተና 9
መለኪያ መጥፋት
በ#ዲያቆን #አሸናፊ #መኮንን የተዘጋጀ ስብከት
አሁን በቴሌግራም ቻናል ይለቀቃል ። ይከታተሉ
የዲያቆን አሸናፊ መኰንን ትምህርቶችና ስብከቶች ለመከታተል ከሥር የተቀመጡትን ገጾች ይመልከቱ፡-
https://hottg.com/Nolawii
https://hottg.com/nolawisebketoch
https://www.facebook.co m/ashenafi.mekonnen.357
https://youtu.be/3qfQp9yYmHY
www.ashenafimekonen.com
መለኪያ መጥፋት
በ#ዲያቆን #አሸናፊ #መኮንን የተዘጋጀ ስብከት
አሁን በቴሌግራም ቻናል ይለቀቃል ። ይከታተሉ
የዲያቆን አሸናፊ መኰንን ትምህርቶችና ስብከቶች ለመከታተል ከሥር የተቀመጡትን ገጾች ይመልከቱ፡-
https://hottg.com/Nolawii
https://hottg.com/nolawisebketoch
https://www.facebook.co m/ashenafi.mekonnen.357
https://youtu.be/3qfQp9yYmHY
www.ashenafimekonen.com
Telegram
Nolawi ኖላዊ
ይህ ቻናል ኦርቶዶክሳዊ መንፈሳዊ ትምህርቶች የሚተላለፉበት ነው። እግዚአብሔር አገልግሎቱን ያስፋ!
0911699907 ዲያቆን አሸናፊ መኮንን
0911699907 ዲያቆን አሸናፊ መኮንን
ከአገልግሎት በፊት
ሰው ብቻውን አይሆንም ። ወይ ከእግዚአብሔር አሊያም ከራሱ ጋር ያወጋል ። ሰው ካገኘም ከሰው ጋር ያወራል ። ትዝታም እንደ አሁን ትኩስና ወቅታዊ ሁኖ ያነጋግረዋል ። የመምህር ቃልም ከሚኖረው ኑሮ ጋር ሲገጣጠም እንደ ገና አዲስ ፍንዳታ ሁኖ በውስጡ ይጮኻል ። መስፈርት እጅግ አስፈላጊ መሆኑን ቅዱስ ጳውሎስ የነገረኝን ከኤፌሶን ቤተ ክርስቲያን አስተዳደር ጋር ማነጻጸር የጀመርኩት አሁን ነው ። ቤተ ክርስቲያን በእምነት የምትቀበል ፣ በፈሪሀ እግዚአብሔር መስፈርት የምትሾም ናት ። የአገልግሎት የመጀመሪያው መስፈርት ፍላጎት ነው ። አገልግሎት ጊዜን ሳይሆን ሕይወትን ሰጥተው የሚገቡበት ነው ። አገልግሎት የፍትፍት ሰደቃ ሳይሆን የመስቀል ጉዞ ነው ። ገሀነምን ከሚያህል የእሳት ዓለም ነፍስ ሲያወጡ ወላፈኑ አይንካኝ ማለት ሞኝነት ነው ። የአገልግሎት ጉዞ ራስን መካድ ያለበት ነው ። ራሴን ከዛሬ ጀምሮ ያለ ክርስቶስ አላውቀውም ብሎ መማል ይጠይቃል ። ይልቁንም ኦርቶዶክሳዊው/ቀጥተኛው ጎዳና ብዙ እንግልት ከውስጥና ከውጭ ያለበት ነው ። ከክርስቶስ ጋር ያልሞተ ፣ ገና ውዳሴና ክብርን ነቅዐ ሐሰት ከሆነው ከሰው ልጅ የሚናፍቅ ጉዞው ይከብደዋል ። ኦርቶዶክሳዊው አገልግሎት በመከራ እድናለሁ ሳይሆን በመከራ የድኅነት ጉዞዬን እፈጽማለሁ ብሎ የሚያምን ነው ።
ኦርቶዶክሳዊው አገልግሎት የሀብት ውድድር ያለበት አይደለም ። ኦርቶዶክሳዊው አምልኮ ስሜትን የሚያነቃቃ ሙዚቃና ጭፈራ ሳይሆን ተመሥጦ ያለበት ነው ። ኦርቶዶክሳዊው ክርስትና ስማዕትነት ያለበት ነው ፣ የጥብዐት/ቅዱስ ጭካኔ/ መንገድ ነው ። ራሱን ያልካደ ፣ የብልጽግና ወንጌል ሰባኪ ፣ የስስት ጦር የወጋው ፣ ግለኝነትን አምላኪ ፣ የራሱን ደሴት መሥርቶ ልጄ ሚስቴ እያለ ኗሪ ኦርቶዶክሳዊው መንገድ አይመቸውም ። ሃይማኖት ከሰው ያልተቀበልነው ፣ በሰው የማንጥለው ነው ።
አገልግሎት ሥራ ቢሆንም በሙያ ብቻ ሳይሆን በጸጋው የምንወጣው ሰማያዊ ግዳጅ ነው ። ወታደርበራሱ ትጥቅ እንደማይዋጋ አገልጋይም የመንፈስ ቅዱስ የጦር ዕቃ በሆነው በጸጋ ያገለግላል ። ቢሆንም የአገልግሎት መስፈርቱ ፍላጎት ነው ። አገልጋይ የሚሆነው በርግጥ መቍረጡ ፣ ዓለምን መካዱ መፈተን አለበት ። ይህን የመሰለ ቆንጆ አንድ ደብር ይገባዋል ብሎ አገልግሎትን ማርከስ ቀጥሎ ያረክስናል ። ጳጳሱ መፍራት ያለበት ዲቁና ሲናቅ ነው ። ዲቁና ሲናቅ ቅስና ይናቃል ፤ ቅስና ሲናቅ ጵጵስና ይናቃል ። አገልግሎት መስፈርት ከሌለ ሰላማዊ ሰልፍ ያማረው ሁሉ ወደ ዐውደ ምሕረቱ ይጠጋል ። ቄሣርን ለመዋጋት ቤተ ክርስቲያንን ምሽግ ያደርጋታል ። ቤተ ክርስቶስ ዘእግዚአብሔር መባሏ ቀርቶ ቤተ ክርስቲያን ዘጴጥሮስ ፣ ቤተ ክርስቲያን ዘጢሞቴዎስ ትባላለች ።
ራሱን የመራ ቤቱን ይመራል ። ቤቱን የመራ አገርና ቤተ ክርስቲያንን ይመራል ። አገልጋይ በግል ሕይወቱና በቤቱ መመዘን አለበት ። ንብረት ጠባቂ እንኳ ሥነ ምግባሩ ይታያል ፣ ተያዥም ይጠራል ። ነፍስን የሚጠብቀው አገልጋይማ ኑሮው መገምገም አለበት ። አገልጋይ በንግግሩ ፣ በአመጋገቡ ፣ በመጠጡ ፣ በግንኙነቱ ፣ በአስተያየቱ ልከኛ መሆን አለበት ። በሁለት ክንፍ በቤተ ክርስቲያንና በዓለም ካልበረርኩ ማለት የለበትም ። ቁጥብነት መከራን ባያስቀርም ይቀንሳል ። እጅግ መራራ ከሆኑ መተፋት አለ ፤ እጅግ ጣፋጭ ከሆኑም ማለቅ አለ ። ድንበር የሌለው አገልጋይ ሁሉ ይደፍረዋል ። ሁሉን ላስደስት የሚልም ሁሉ ይከፋበታል ። ሰውን ብናስደስት እግዚአብሔር ሊያዝንብን ይችላል ። እግዚአብሔርን ስናስደስት ግን እግዚአብሔርን የሚያውቅ ይደሰትብናል ።
ራስን መግዛት የአገልግሎት ትልቅ መስፈርት ነው ። በከተማ ላይ የበላይ ከመሆን በራስ ላይ የበላይ መሆን የተሻለ ነው ። ራስን አለመግዛት ለጸጸት ይዳርጋል ። በሕይወት ሰልፍ ውስጥ ታጋሽ ያልሆነ ሰው ራስን ባለመግዛት ይፈተናል ። ራስን መግዛት በሁሉም ነገሮች ውስጥ ያስፈልጋል ። በፍቅር ራሱን ያልገዛ ከመውደድ አልፎ አምልኮ ውስጥ ይገባል ። የወደደውን ሰው ሲያጣ ሞቱን ይመኛል ። በቸርነት ራስን መግዛት ይገባል ። ችግር በተወራበት ፣ መዋጮ በሚጠየቅበት ቦታ ሁሉ በስሜት እሰጣለሁ የሚሉ ሲጨነቁ እናያለን ። በቁጠባም ራስ መግዛት ይገባል ። ለጤናቸው እንኳ ገንዘብ ላለማውጣት የሚሰስቱ ሰዎች አሉ ። የሰበሰብነውን አንድ ቀን የማናውቀው ሰው ይበላዋል ። በቅጡ መጠቀም መልካም ነው ። በእውነት እያንዳንዱ ተልእኮ አገልግሎት ነው ። ሠራተኛ ሁሉ አገልጋይ ነው ። ስለዚህ ራስን መግዛት ይገባቸዋል ። አዳራሹ በስብሰባ ሲግል ራስን ባለ መግዛት ሹሞችን የሚሳደቡ ሲወጡ ይጨነቃሉ ። ያጨበጨበላቸው ሕዝብም የት ደረሱ አይላቸውም ። በርግጥ ነገሥታት የመከራቸውንም ሰደበን እንደሚሉ የታወቀ ነው። ቢሆንም ስንገሥጽም ራስን በመግዛት ሊሆን ይገባዋል ።
አዎ አገልግሎት የተገነባ ሰብእናና ፣ ያጌጠ መንፈሳዊነት መስፈርቱ ነው ።
ጢሞቴዎስ ነኝ ክፍል 14
ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ሚያዝያ 14 ቀን 2016 ዓ.ም.
ሰው ብቻውን አይሆንም ። ወይ ከእግዚአብሔር አሊያም ከራሱ ጋር ያወጋል ። ሰው ካገኘም ከሰው ጋር ያወራል ። ትዝታም እንደ አሁን ትኩስና ወቅታዊ ሁኖ ያነጋግረዋል ። የመምህር ቃልም ከሚኖረው ኑሮ ጋር ሲገጣጠም እንደ ገና አዲስ ፍንዳታ ሁኖ በውስጡ ይጮኻል ። መስፈርት እጅግ አስፈላጊ መሆኑን ቅዱስ ጳውሎስ የነገረኝን ከኤፌሶን ቤተ ክርስቲያን አስተዳደር ጋር ማነጻጸር የጀመርኩት አሁን ነው ። ቤተ ክርስቲያን በእምነት የምትቀበል ፣ በፈሪሀ እግዚአብሔር መስፈርት የምትሾም ናት ። የአገልግሎት የመጀመሪያው መስፈርት ፍላጎት ነው ። አገልግሎት ጊዜን ሳይሆን ሕይወትን ሰጥተው የሚገቡበት ነው ። አገልግሎት የፍትፍት ሰደቃ ሳይሆን የመስቀል ጉዞ ነው ። ገሀነምን ከሚያህል የእሳት ዓለም ነፍስ ሲያወጡ ወላፈኑ አይንካኝ ማለት ሞኝነት ነው ። የአገልግሎት ጉዞ ራስን መካድ ያለበት ነው ። ራሴን ከዛሬ ጀምሮ ያለ ክርስቶስ አላውቀውም ብሎ መማል ይጠይቃል ። ይልቁንም ኦርቶዶክሳዊው/ቀጥተኛው ጎዳና ብዙ እንግልት ከውስጥና ከውጭ ያለበት ነው ። ከክርስቶስ ጋር ያልሞተ ፣ ገና ውዳሴና ክብርን ነቅዐ ሐሰት ከሆነው ከሰው ልጅ የሚናፍቅ ጉዞው ይከብደዋል ። ኦርቶዶክሳዊው አገልግሎት በመከራ እድናለሁ ሳይሆን በመከራ የድኅነት ጉዞዬን እፈጽማለሁ ብሎ የሚያምን ነው ።
ኦርቶዶክሳዊው አገልግሎት የሀብት ውድድር ያለበት አይደለም ። ኦርቶዶክሳዊው አምልኮ ስሜትን የሚያነቃቃ ሙዚቃና ጭፈራ ሳይሆን ተመሥጦ ያለበት ነው ። ኦርቶዶክሳዊው ክርስትና ስማዕትነት ያለበት ነው ፣ የጥብዐት/ቅዱስ ጭካኔ/ መንገድ ነው ። ራሱን ያልካደ ፣ የብልጽግና ወንጌል ሰባኪ ፣ የስስት ጦር የወጋው ፣ ግለኝነትን አምላኪ ፣ የራሱን ደሴት መሥርቶ ልጄ ሚስቴ እያለ ኗሪ ኦርቶዶክሳዊው መንገድ አይመቸውም ። ሃይማኖት ከሰው ያልተቀበልነው ፣ በሰው የማንጥለው ነው ።
አገልግሎት ሥራ ቢሆንም በሙያ ብቻ ሳይሆን በጸጋው የምንወጣው ሰማያዊ ግዳጅ ነው ። ወታደርበራሱ ትጥቅ እንደማይዋጋ አገልጋይም የመንፈስ ቅዱስ የጦር ዕቃ በሆነው በጸጋ ያገለግላል ። ቢሆንም የአገልግሎት መስፈርቱ ፍላጎት ነው ። አገልጋይ የሚሆነው በርግጥ መቍረጡ ፣ ዓለምን መካዱ መፈተን አለበት ። ይህን የመሰለ ቆንጆ አንድ ደብር ይገባዋል ብሎ አገልግሎትን ማርከስ ቀጥሎ ያረክስናል ። ጳጳሱ መፍራት ያለበት ዲቁና ሲናቅ ነው ። ዲቁና ሲናቅ ቅስና ይናቃል ፤ ቅስና ሲናቅ ጵጵስና ይናቃል ። አገልግሎት መስፈርት ከሌለ ሰላማዊ ሰልፍ ያማረው ሁሉ ወደ ዐውደ ምሕረቱ ይጠጋል ። ቄሣርን ለመዋጋት ቤተ ክርስቲያንን ምሽግ ያደርጋታል ። ቤተ ክርስቶስ ዘእግዚአብሔር መባሏ ቀርቶ ቤተ ክርስቲያን ዘጴጥሮስ ፣ ቤተ ክርስቲያን ዘጢሞቴዎስ ትባላለች ።
ራሱን የመራ ቤቱን ይመራል ። ቤቱን የመራ አገርና ቤተ ክርስቲያንን ይመራል ። አገልጋይ በግል ሕይወቱና በቤቱ መመዘን አለበት ። ንብረት ጠባቂ እንኳ ሥነ ምግባሩ ይታያል ፣ ተያዥም ይጠራል ። ነፍስን የሚጠብቀው አገልጋይማ ኑሮው መገምገም አለበት ። አገልጋይ በንግግሩ ፣ በአመጋገቡ ፣ በመጠጡ ፣ በግንኙነቱ ፣ በአስተያየቱ ልከኛ መሆን አለበት ። በሁለት ክንፍ በቤተ ክርስቲያንና በዓለም ካልበረርኩ ማለት የለበትም ። ቁጥብነት መከራን ባያስቀርም ይቀንሳል ። እጅግ መራራ ከሆኑ መተፋት አለ ፤ እጅግ ጣፋጭ ከሆኑም ማለቅ አለ ። ድንበር የሌለው አገልጋይ ሁሉ ይደፍረዋል ። ሁሉን ላስደስት የሚልም ሁሉ ይከፋበታል ። ሰውን ብናስደስት እግዚአብሔር ሊያዝንብን ይችላል ። እግዚአብሔርን ስናስደስት ግን እግዚአብሔርን የሚያውቅ ይደሰትብናል ።
ራስን መግዛት የአገልግሎት ትልቅ መስፈርት ነው ። በከተማ ላይ የበላይ ከመሆን በራስ ላይ የበላይ መሆን የተሻለ ነው ። ራስን አለመግዛት ለጸጸት ይዳርጋል ። በሕይወት ሰልፍ ውስጥ ታጋሽ ያልሆነ ሰው ራስን ባለመግዛት ይፈተናል ። ራስን መግዛት በሁሉም ነገሮች ውስጥ ያስፈልጋል ። በፍቅር ራሱን ያልገዛ ከመውደድ አልፎ አምልኮ ውስጥ ይገባል ። የወደደውን ሰው ሲያጣ ሞቱን ይመኛል ። በቸርነት ራስን መግዛት ይገባል ። ችግር በተወራበት ፣ መዋጮ በሚጠየቅበት ቦታ ሁሉ በስሜት እሰጣለሁ የሚሉ ሲጨነቁ እናያለን ። በቁጠባም ራስ መግዛት ይገባል ። ለጤናቸው እንኳ ገንዘብ ላለማውጣት የሚሰስቱ ሰዎች አሉ ። የሰበሰብነውን አንድ ቀን የማናውቀው ሰው ይበላዋል ። በቅጡ መጠቀም መልካም ነው ። በእውነት እያንዳንዱ ተልእኮ አገልግሎት ነው ። ሠራተኛ ሁሉ አገልጋይ ነው ። ስለዚህ ራስን መግዛት ይገባቸዋል ። አዳራሹ በስብሰባ ሲግል ራስን ባለ መግዛት ሹሞችን የሚሳደቡ ሲወጡ ይጨነቃሉ ። ያጨበጨበላቸው ሕዝብም የት ደረሱ አይላቸውም ። በርግጥ ነገሥታት የመከራቸውንም ሰደበን እንደሚሉ የታወቀ ነው። ቢሆንም ስንገሥጽም ራስን በመግዛት ሊሆን ይገባዋል ።
አዎ አገልግሎት የተገነባ ሰብእናና ፣ ያጌጠ መንፈሳዊነት መስፈርቱ ነው ።
ጢሞቴዎስ ነኝ ክፍል 14
ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ሚያዝያ 14 ቀን 2016 ዓ.ም.
የሕይወት ሥነ ሥርዓት (14)
11- ቀጠሮ አክብር
እግዚአብሔር አምላክ ቀጠሮን በማክበር የታወቀ አምላክ ነው ። የ5550 ዘመንን ቀጠሮ ያከበረ ብቸኛ አምላክ ነው ። ሐዋርያው ይህን ሲገልጥ እንዲህ ብሏል፦ “ነገር ግን የዘመኑ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር ከሴት የተወለደውን ከሕግም በታች የተወለደውን ልጁን ላከ፤” (ገላ. 4 ፡ 4) ።
እግዚአብሔር በቀጠሮው ማርፈድ ወይም መዘግየት አያውቅም ። ይህንንም ነቢዩ እንዲህ ሲል ገልጧል፡- “ራእዩ ገና እስከ ተወሰነው ጊዜ ነው፥ ወደ ፍጻሜውም ይቸኵላል፥ እርሱም አይዋሽም ቢዘገይም በእርግጥ ይመጣልና ታገሠው እርሱ አይዘገይም ።” (ዕን. 2 ፡ 3) ።
ይህች ዓለም በእግዚአብሔር ቀጠሮ ተይዛ ያለች ዓለም ናት ። 5500 ዘመን የድኅነት ቀጠሮ ነበራት ። ላለፉት ሁለት ሺህ ዓመታት የሚመጣውን ንጉሥ እየጠበቀች ነው ። የዚህች ዓለም ትልቁ እንግዳ የመጣውና የሚመጣው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ። እርሱ ከእኛ ሳይለይ እመጣለሁ ያለ ፣ መንበሩን ሳይተው በበረት የተወለደ ነው ። በኖኅ ዘመን የጥፋት ውኃ መቼ እንደሚመጣ ፣ መቼ እንደሚቆም ተናግሮ ፣ የተናገረውንም የፈጸመ አምላክ ነው።
አምልኮተ እግዚአብሔር ታላቅ ቀጠሮ ነው ። ከእግዚአብሔር ጋር ከመገናኘት የበለጠ ቀጠሮ የለምና ። በብሉይ ኪዳን በመገናኛው ድንኳን የጠዋትና የማታ መሥዋዕት በጊዜው ይቀርባል ። የሳምንትና የዓመት አገልግሎትም ከቀጠሮ ሰዓቱ ዝንፍ አይልም ። በዓላት የሰውና የእግዚአብሔር ቀጠሮ ናቸው ። ወላጅ ለበዓል ልጆቹን እንደሚጠበቅ እግዚአብሔርም በሰንበትና በበዓላት ልጆቹን ይጠብቃል ። በዓላት የቤተሰብ ፍቅርን እንደሚጠብቁ ፣ መንፈሳዊ በዓላትም ሃይማኖትን በሰዎች ልብ ትኩስ ያደርጋሉ ። የተደመሰሱ አብያተ ክርስቲያናት አንዱ ችግራቸው በዓላት የሌላቸው መሆኑ ነው ። ደግሞም በዓላት የአንድ ሕዝብ የነጻነት ምልክት ናቸው ።
ተፈጥሮ እግዚአብሔር የሰጠውን ቀጠሮ ያከብራል ። ተፈጥሮ በራሱ ቸር አይደለም ። አንዳንድ ሰዎች የተፈጥሮ ችሮታ እያሉ ያወራሉ ። በተፈጥሮ በኩል የቸርነት እጁን የሚገልጥ እግዚአብሔር ብቻ ነው ። ተፈጥሮ ራሱን የሚመራ ሳይሆን ፈጥሮ የሚያስተዳድር አምላክ አለ ። ይህ ሁሉ አስደናቂ ተፈጥሮ የታላቅ ፍንዳታ ውጤት አይደለም ። ታላቅ ፍንዳታ ይህን ውበት ከሰጠ ፣ ትንንሽ ፍንዳታ ያለባቸው የኢራቅና የጋዛ ከተሞች ውብ በሆኑ ነበር ። ተፈጥሮ ለእግዚአብሔር ቀጠሮ የተገዛ ነው ። ሌሊትና ቀኑ ክረምትና በጋው በሰዓቱ ይመጣሉ ። የመስቀል ወፍ ፣ አደይ አበባ በሰዓቱ ሲመጡ ሰው እንዴት ቀጠሮ የሚስት ይሆናል ?
ቀጠሮን አክብር ። ይበልጥ ለአምልኮተ እግዚአብሔር ወደ ቤተ ክርስቲያን የምትሄድበትን ቀጠሮ አክብር ። ምነው ከአምልኮተ እግዚአብሔር ውጭ ወደ ቤተ ክርስቲያን ይኬዳል ወይ ? አዎ ጓደኛ ለማግኘት ፣ የወደዳት ልጅ ሰላም ማደሯን ለማረጋገጥ የሚሄዱ አሉ ። ለረብሻ ፣ ለፖለቲካ የሚሄዱ አሉ ። የዘር ዕድር ለመጠጣት ፣ የስለላ ተግባራቸውን ለማከናወን የሚሄዱ አሉ ። እግዚአብሔር ቤት ለመሄድ የምናረፍደው የሚመለከተንና የማይመለከተን አምልኮ ያለ ስለሚመስለን ሊሆን ይችላል። አንዳንድ ሰው ጸሎቱ እንዳለቀ ስብከት ላይ መድረስ ይፈልጋል ። ሁሉም ግን ለእግዚአብሔር ክብር ፣ ለሰው ጥቅም የሚደረግ አገልግሎት ነው ።
ቀጠሮን በሚመለከት ራሳችንን የረገምን ሕዝቦች ነን ። “የሀበሻ ቀጠሮ” እንላለን ። የሚገርመው ያረፈደው ሰውዬ ሳይቀር “ያው የሀበሻ ቀጠሮ አይደል” ይላል ። ቀጠሮ የሰውነት እንጂ የሀበሻና የፈረንጅ መለኪያ አይደለም ። ወላጆቻችን ቀጠሮ በጣም ያከብሩ ነበር ። ጠዋት ቀጠሮ ካላቸው እንቅልፍ አይተኙም ነበር ። ባለፈው ዘመን ከሰዓቱ በፊት የሚደርስ ትውልድ ነበረ ፣ በመካከሉ አርፍዶ የሚደርስ ትውልድ ተፈጠረ ። አሁን ደግሞ አርፍዶ የሚቀር ትውልድ እየመጣ ነው ። የሚገርመው የቀጠርነው ሰው ሲቀር እንደ መገላገል እየቆጠርን መምጣታችን ነው ። በአሁን ዘመን ቅሬታም እያለቀ ነው ። ቀጠሮ ለራስና ለሰው ያለን ክብር መግለጫ ነው ።
ቀጠሮን ለማክበር መርሳትንም ለማሸነፍ የሚረዱን ነገሮች፦
የማንችል ከሆነ ቀጠሮ መያዝ አይገባንም። ቀጠሮው ከተሰረዘም ቀደም ብለን ማሳወቅ ይገባናል ። ሰውን ቀጥሮ ስልክ ማጥፋት ነውር ነው ። ነጻ ፍጡር ነንና መገኘት ካልፈለግን ቀድመን ማሳወቅ ይገባናል ። በማስታወሻችን ላይ ቀጠሮአችንን ማስፈር ተገቢ ነው ። ማስታወሻውን በሚታይ ቦታ ላይ ማስቀመጥ መልካም ነው ። የመንገድን ሁኔታ ታሳቢ አድርገን ቀድመን መውጣት አስፈላጊ ነው ። የማይካስ የሰውን ጊዜ እንዳንበላ መጠንቀቅ ይገባናል ። ከቤተሰብ ጋር ከሆነ ወደ ቀጠሮ ቦታችን የምንሄደው ፣ ሕፃናት ሊያስረፍዱ ይችላሉና ቀድመን ማዘጋጀት አለብን ። ልጆች ካሉ ሴቶች ጫና ስለሚበዛባቸው “ቶሎ በይ” ከማለት ማገዝ የተሻለ ነው ። የሚገርመው ሙሽራ ማርፈድን እንደ ክብር የሚቆጥርበት አገር መሥርተናል ። እድምተኛ እየበላ ሙሽራን መጠበቅ የቅርብ ጊዜ ልማድ ነበር ። አሁን ግን አትብሉም ፣ ቶሎ አልመጣምም የሚል ሙሽራ አፍርተናል ። ይህ የትውልዱ መውደቅ ምልክት ነው ።
በቀጠሮአችን መሠረት ስንገናኝም የምንነጋገርበትን ርእስ መያዝ ከመጋጨትና ከመሰለቻቸት ይጠብቀናል። ስንገናኝ ጥሩና ሞቅ ያለ ሰላምታ መለዋወጥ ፣ ስናወራ ዓይን ለዓይን ተያይተን ማውራት ፣ የአክብሮትን ቃላት መጠቀም መልካም ነው ። ስንለያይ በስስት ለቀጣይ ግንኙነት በር በመክፈት መሆን ይገባዋል ። ቀጠሮ ማክበር የትልቅነት መለኪያ ነው ። ሰዎችን ስንቀጥር ከአቅም በላይ በሆነ ጉዳይ ሊቀሩ ይችላሉና መቀየም አይገባንም ። ሰዎችን ስንቀጥር የሚነበብ መጽሐፉ መያዝ ጥሩ ነው ። ቢያረፍዱ ደግሞም ቢቀሩ ጊዜውን መጠቀም እንችላለን ። ጊዜ ክቡር ነውና ቀጠሮ አክብሩ!
እግዚአብሔር ዘመናችሁን ይባርክ !
ይቀጥላል
ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ሚያዝያ 15 ቀን 2016 ዓ.ም.
11- ቀጠሮ አክብር
እግዚአብሔር አምላክ ቀጠሮን በማክበር የታወቀ አምላክ ነው ። የ5550 ዘመንን ቀጠሮ ያከበረ ብቸኛ አምላክ ነው ። ሐዋርያው ይህን ሲገልጥ እንዲህ ብሏል፦ “ነገር ግን የዘመኑ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር ከሴት የተወለደውን ከሕግም በታች የተወለደውን ልጁን ላከ፤” (ገላ. 4 ፡ 4) ።
እግዚአብሔር በቀጠሮው ማርፈድ ወይም መዘግየት አያውቅም ። ይህንንም ነቢዩ እንዲህ ሲል ገልጧል፡- “ራእዩ ገና እስከ ተወሰነው ጊዜ ነው፥ ወደ ፍጻሜውም ይቸኵላል፥ እርሱም አይዋሽም ቢዘገይም በእርግጥ ይመጣልና ታገሠው እርሱ አይዘገይም ።” (ዕን. 2 ፡ 3) ።
ይህች ዓለም በእግዚአብሔር ቀጠሮ ተይዛ ያለች ዓለም ናት ። 5500 ዘመን የድኅነት ቀጠሮ ነበራት ። ላለፉት ሁለት ሺህ ዓመታት የሚመጣውን ንጉሥ እየጠበቀች ነው ። የዚህች ዓለም ትልቁ እንግዳ የመጣውና የሚመጣው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ። እርሱ ከእኛ ሳይለይ እመጣለሁ ያለ ፣ መንበሩን ሳይተው በበረት የተወለደ ነው ። በኖኅ ዘመን የጥፋት ውኃ መቼ እንደሚመጣ ፣ መቼ እንደሚቆም ተናግሮ ፣ የተናገረውንም የፈጸመ አምላክ ነው።
አምልኮተ እግዚአብሔር ታላቅ ቀጠሮ ነው ። ከእግዚአብሔር ጋር ከመገናኘት የበለጠ ቀጠሮ የለምና ። በብሉይ ኪዳን በመገናኛው ድንኳን የጠዋትና የማታ መሥዋዕት በጊዜው ይቀርባል ። የሳምንትና የዓመት አገልግሎትም ከቀጠሮ ሰዓቱ ዝንፍ አይልም ። በዓላት የሰውና የእግዚአብሔር ቀጠሮ ናቸው ። ወላጅ ለበዓል ልጆቹን እንደሚጠበቅ እግዚአብሔርም በሰንበትና በበዓላት ልጆቹን ይጠብቃል ። በዓላት የቤተሰብ ፍቅርን እንደሚጠብቁ ፣ መንፈሳዊ በዓላትም ሃይማኖትን በሰዎች ልብ ትኩስ ያደርጋሉ ። የተደመሰሱ አብያተ ክርስቲያናት አንዱ ችግራቸው በዓላት የሌላቸው መሆኑ ነው ። ደግሞም በዓላት የአንድ ሕዝብ የነጻነት ምልክት ናቸው ።
ተፈጥሮ እግዚአብሔር የሰጠውን ቀጠሮ ያከብራል ። ተፈጥሮ በራሱ ቸር አይደለም ። አንዳንድ ሰዎች የተፈጥሮ ችሮታ እያሉ ያወራሉ ። በተፈጥሮ በኩል የቸርነት እጁን የሚገልጥ እግዚአብሔር ብቻ ነው ። ተፈጥሮ ራሱን የሚመራ ሳይሆን ፈጥሮ የሚያስተዳድር አምላክ አለ ። ይህ ሁሉ አስደናቂ ተፈጥሮ የታላቅ ፍንዳታ ውጤት አይደለም ። ታላቅ ፍንዳታ ይህን ውበት ከሰጠ ፣ ትንንሽ ፍንዳታ ያለባቸው የኢራቅና የጋዛ ከተሞች ውብ በሆኑ ነበር ። ተፈጥሮ ለእግዚአብሔር ቀጠሮ የተገዛ ነው ። ሌሊትና ቀኑ ክረምትና በጋው በሰዓቱ ይመጣሉ ። የመስቀል ወፍ ፣ አደይ አበባ በሰዓቱ ሲመጡ ሰው እንዴት ቀጠሮ የሚስት ይሆናል ?
ቀጠሮን አክብር ። ይበልጥ ለአምልኮተ እግዚአብሔር ወደ ቤተ ክርስቲያን የምትሄድበትን ቀጠሮ አክብር ። ምነው ከአምልኮተ እግዚአብሔር ውጭ ወደ ቤተ ክርስቲያን ይኬዳል ወይ ? አዎ ጓደኛ ለማግኘት ፣ የወደዳት ልጅ ሰላም ማደሯን ለማረጋገጥ የሚሄዱ አሉ ። ለረብሻ ፣ ለፖለቲካ የሚሄዱ አሉ ። የዘር ዕድር ለመጠጣት ፣ የስለላ ተግባራቸውን ለማከናወን የሚሄዱ አሉ ። እግዚአብሔር ቤት ለመሄድ የምናረፍደው የሚመለከተንና የማይመለከተን አምልኮ ያለ ስለሚመስለን ሊሆን ይችላል። አንዳንድ ሰው ጸሎቱ እንዳለቀ ስብከት ላይ መድረስ ይፈልጋል ። ሁሉም ግን ለእግዚአብሔር ክብር ፣ ለሰው ጥቅም የሚደረግ አገልግሎት ነው ።
ቀጠሮን በሚመለከት ራሳችንን የረገምን ሕዝቦች ነን ። “የሀበሻ ቀጠሮ” እንላለን ። የሚገርመው ያረፈደው ሰውዬ ሳይቀር “ያው የሀበሻ ቀጠሮ አይደል” ይላል ። ቀጠሮ የሰውነት እንጂ የሀበሻና የፈረንጅ መለኪያ አይደለም ። ወላጆቻችን ቀጠሮ በጣም ያከብሩ ነበር ። ጠዋት ቀጠሮ ካላቸው እንቅልፍ አይተኙም ነበር ። ባለፈው ዘመን ከሰዓቱ በፊት የሚደርስ ትውልድ ነበረ ፣ በመካከሉ አርፍዶ የሚደርስ ትውልድ ተፈጠረ ። አሁን ደግሞ አርፍዶ የሚቀር ትውልድ እየመጣ ነው ። የሚገርመው የቀጠርነው ሰው ሲቀር እንደ መገላገል እየቆጠርን መምጣታችን ነው ። በአሁን ዘመን ቅሬታም እያለቀ ነው ። ቀጠሮ ለራስና ለሰው ያለን ክብር መግለጫ ነው ።
ቀጠሮን ለማክበር መርሳትንም ለማሸነፍ የሚረዱን ነገሮች፦
የማንችል ከሆነ ቀጠሮ መያዝ አይገባንም። ቀጠሮው ከተሰረዘም ቀደም ብለን ማሳወቅ ይገባናል ። ሰውን ቀጥሮ ስልክ ማጥፋት ነውር ነው ። ነጻ ፍጡር ነንና መገኘት ካልፈለግን ቀድመን ማሳወቅ ይገባናል ። በማስታወሻችን ላይ ቀጠሮአችንን ማስፈር ተገቢ ነው ። ማስታወሻውን በሚታይ ቦታ ላይ ማስቀመጥ መልካም ነው ። የመንገድን ሁኔታ ታሳቢ አድርገን ቀድመን መውጣት አስፈላጊ ነው ። የማይካስ የሰውን ጊዜ እንዳንበላ መጠንቀቅ ይገባናል ። ከቤተሰብ ጋር ከሆነ ወደ ቀጠሮ ቦታችን የምንሄደው ፣ ሕፃናት ሊያስረፍዱ ይችላሉና ቀድመን ማዘጋጀት አለብን ። ልጆች ካሉ ሴቶች ጫና ስለሚበዛባቸው “ቶሎ በይ” ከማለት ማገዝ የተሻለ ነው ። የሚገርመው ሙሽራ ማርፈድን እንደ ክብር የሚቆጥርበት አገር መሥርተናል ። እድምተኛ እየበላ ሙሽራን መጠበቅ የቅርብ ጊዜ ልማድ ነበር ። አሁን ግን አትብሉም ፣ ቶሎ አልመጣምም የሚል ሙሽራ አፍርተናል ። ይህ የትውልዱ መውደቅ ምልክት ነው ።
በቀጠሮአችን መሠረት ስንገናኝም የምንነጋገርበትን ርእስ መያዝ ከመጋጨትና ከመሰለቻቸት ይጠብቀናል። ስንገናኝ ጥሩና ሞቅ ያለ ሰላምታ መለዋወጥ ፣ ስናወራ ዓይን ለዓይን ተያይተን ማውራት ፣ የአክብሮትን ቃላት መጠቀም መልካም ነው ። ስንለያይ በስስት ለቀጣይ ግንኙነት በር በመክፈት መሆን ይገባዋል ። ቀጠሮ ማክበር የትልቅነት መለኪያ ነው ። ሰዎችን ስንቀጥር ከአቅም በላይ በሆነ ጉዳይ ሊቀሩ ይችላሉና መቀየም አይገባንም ። ሰዎችን ስንቀጥር የሚነበብ መጽሐፉ መያዝ ጥሩ ነው ። ቢያረፍዱ ደግሞም ቢቀሩ ጊዜውን መጠቀም እንችላለን ። ጊዜ ክቡር ነውና ቀጠሮ አክብሩ!
እግዚአብሔር ዘመናችሁን ይባርክ !
ይቀጥላል
ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ሚያዝያ 15 ቀን 2016 ዓ.ም.
የሕይወት ሥነ ሥርዓት (15)
12- የመጣህበትን አትርሳ
ሕይወት መንገድ ነው ። መንገድ የመጣንበት ደግሞም የምንሄድበት ነው ። ሀብት ቢነጥፍ ፣ ጉልበት ቢከዳ ፣ ወዳጅ ጠላት ቢሆን ሕይወት ይቀጥላል ። ሁሉም ሰው የራሱ የሆነ ሕይወት አለው ። በእግዚአብሔር ፈቃድ የጀመረች ሕይወቱ በእርሱ ፈቃድ ትቆማለች ። ከበሽታ የተነሣ ቢመረር ፣ ከማጣት የተነሣ ቢያለቅስ ፣ ከወዳጅ ሞት የተነሣ ቢከፋው ሕይወት ትቀጥላለች ። አቀባበሉ ግን ቀጣዩን ብርሃን ወይም ጨለማ ያደርገዋል ። በአንድ ዓይነት መከራ ውስጥ የሚያልፉ ሁለት ሰዎች አንዱ ቢስቅ ሌላው ቢያለቅስ ጉዳዩ የአቀባበል ነው ። አቀባበሉ ያቀለዋል አሊያም ያከብደዋል ። ያመንነውን እንወርሳለንና “ይህ ክፉ ነገር ለበጎ ነው የመጣው” ስንል በጎ ይሆናል ። አቀባበል ጨለማውን ብርሃን ያደርጋል ። መንገድ ከፍታም ዝቅታም አለው ። ሕይወት መንገድ ናትና የክብር ዘመን እንዳለ ሁሉ የውርደት ዘመንም አለ ። አልጫ አልጫ የሚል ቃል ተናግረን እንደ ጥቅስ የሚነገርበት ዘመን አለ ። የጥበብ ቃል ተናግረን “ምነው ሞቶ ባረፈው” የምንባልበት ዘመን አለ ። አንዳንድ ሁኔታዎች መታገል ሳይሆን መታደል የሚያመጣቸው ሊሆኑ ይችላሉ ።
ተራራ የወጣው መንገደኛ ቁልቁለት እንደሚወርድ እርግጠኛ ነው ። ከተራራ ቀጥሎ ተራራ አይመጣምና ። የከበረም መዋረዱ አይቀርም ። “ፖለቲከኛና አትሌት በቃህ ካልተባሉ አያቆሙም” ይባላል ። እንደ ከበሩ ዞር ማለት ትልቅ ጥበብ ነው ። ከሐር መነሳንስ ወደ ጭቃ ጅራፍ ሳይለወጥ ዞር ማለት አዋቂነት ነው ። ይልቁንም በአገራችን ወረት በዙፋን ተቀምጦ እየገዛን ይመስላል ። “አንቱ” ያልነውን ሰውዬ “አንተ” ለማለት እንቸኩላለን ። መንገድ ተመዝማዛ ነው ። ቀጣዩ አልታይ እያለን የምንጨነቅበት ፣ ተስፋ ዘይቱ እንዳለቀ መቅረዝ ጭል ፣ ጭል የሚልበት ጊዜ ጥቂት አይደለም ። ተስፋ መቍረጥም የሕይወት አንድ አካል ነው ። ያልገባን ነገር ቢኖርም “እግዚአብሔር አዋቂ ነው” ማለት ያሳርፋል ። “እግዚአብሔር አዋቂ ነው” ማለት “እግዚአብሔር ያውቅልኛል” ማለት ነው ። መንገድ ሸካራ ነው ። ውስጣችን በሰዎች ክፋት የሚበከልበት ፣ ጥርጣሬ ቀናችንን የሚዋጋበት ጊዜ ብዙ ነው ። ሰዎችን ይቅር ለማለት ከራሳችን ጋር ግብ ግብ ውስጥ የምንገባበት ፣ ቂመኝነትን ዳግም ላለመጎዳት የሚጋረድ ጋሻ አድርገን የምንመለከትበት ጊዜ አያሌ ነው ። “ተበድዬስ ይቅር አልልም” እያልን እንዘፍናለን ። ይቅር የምንለውማ ስንበደል ነው ። ፍቅር የመበደል አጥር ሲሻገር እውነተኛ ይሆናል ።
ሕይወት መንገድ ነው ። መንገድ መነሻ አለው ፣ መንገድ መድረሻ አለው ። እግዚአብሔርን ማመን ያስፈለገን መነሻና መድረሻ ያለው ሕይወት ለመያዝ ነው ። እግዚአብሔርን ካላመንን ሕይወታችን መነሻና መድረሻ የሌላት ፣ መሐል ባሕር ላይ ያለ መቅዘፊያ የተለቀቀች ጀልባ ትሆናለች ። የመጣንበት የምንሄድበትን ይወስነዋል ። የመጣንበትን በትክክል ማሰብ ከቻልን ምስጋና በአፋችን ይሞላል ። ሰውን መበደል እንጸየፋለን ። ሌሎችን ለመርዳት እንነሣሣለን ። መካሪ ሁነን አዲስ ትውልድን እናበረታታለን ። ግፍን እንጸየፋለን ። ማንንም አንንቅም ። አዎ ሕፃናት ነበርን ። ሕፃናትን መውደድና ማክበር አለብን ። አዎ ዕራቁታችንን ተወልደናል ። ስለዚህ ድሀ ነበርኩ ማለት የሚያሳፍር አይደለም ። ያለ ፍትሕ ታስረናል ። ስለዚህ ያለ ፍትሕ ሌሎችን መጉዳት አይገባንም ። አንድ ድቃቂ ሣንቲም ሊቸግር እንደሚችል ኑሮአችን ምስክር ነው ። የመጣንበትን ብናስብ እጆቻችን ለመርዳት ይዘረጉ ነበር ።
አዎ የመጣህበትን አትርሳ ። የመጣኸው ካፈር ነው ። አንድ ቀን ወደ አፈር ትመለሳለህና ኩራትን ተው ። ፊደል ለማወቅ ብዙ ወራት የፈጀብህ ፣ በብዙ ጥረት አዋቂ የሆንህ ፣ የብዙዎችን ጉልበት የጨረስህ ነህና ሰውን “ደንቆሮ” ብለህ ለመሳደብ አትድፈር ። ዕድሉን ቢያገኝ ሁሉም ሊቅ ይሆን ነበር ። ያደግህበት ሰፈር ዛሬ ካየሃቸው ውብ ከተሞች የሚበልጥ ትዝታ ያለው ነውና ያደግክበትን ቀዬ ዞር ብለህ ተመልከት ። ያሳደጉህ እናቶች ፣ ዛሬም ረሀብ ዘመድ ሆኖ አልላቀቅ ያላቸው የአባትህና የእናትህ ጓደኞች አሉና ሄደህ ጠይቃቸው ፣ ካለህ ላይ አካፍላቸው ። ትንሹ ማሙሽ አድገህ ለመስጠት በመብቃትህ ፈጣሪያቸውን ባንተ ምክንያት ያመስግኑት ። መምህራኖችህ ዛሬ ከእነርሱ የበለጠ እውቀት ብትይዝም የወጣህባቸው መሰላል ናቸውና አክብራቸው ። ዋጋቸውንም ሂደህ ንገራቸው ። የወጣህበት መሰላል ለመውረድም ይረዳልና ወጣሁ ብለህ ገፍተህ አትጣለው ። አንተን አንቱ ያሰኘህ ሕዝብ ነውና ሕዝብህን አትናቅ ። ሕዝብ ያንተ ሎሌ ሳይሆን አንተ የሕዝብ አሽከር መሆንህን እመን ። የሥልጣን በትር አንድ ቀን ከእጅ ያመልጣል ። የደጁን ስትገፋ ልጅህ እንደ አቤሴሎም ለሞት ይፈልግሃል ። ሥልጣን ፀሐይ ነው ። ምንም ቢደምቅ መጥለቁ አይቀርም ። አዎ የድሀ ልጅ ነበርህና የመጣህበትን አትርሳ ። በማጣት ዘመንህ ፣ በእስር ወራትህ የገባኸውን ቃል ኪዳን አትዘንጋ ። ዛሬ ሽቱ ስለተቀባህ ሰው ሁሉ የሚሸት መስሎህ አትጸየፈው ። የአንድ ቀን ውኃ ስታጣ አንተም ለመበላሸት ቅርብ ነህ ። የመጣህበትን አትርሳ ። ይህችን ከተማ ስትቀላቀል የነበረህን መደናገር አትዘንጋ ። ስለዚህ ማንንም መጤ ብለህ አትናገር ። ሁሉም ሰው መጤ ነው ። አንድ ቀን ይሄዳል ። በዚህ ዓለም ላይ መሰንበት እንጂ መቅረት የለም ።
የመጣህበትን አትርሳ ። እግዚአብሔር ብቻውን አስተማረኝ ብለህ ያስተማሩህን አትካድ ። እግዚአብሔር ብቻውን ረዳኝ በሚል ዘይቤ የሰውን ውለታ አታጥፋ ። የእናቴን ጡት አልጠባሁም ፣ የማንም ውለታ አላለፈብኝም ብለህ አትገበዝ ። ያልተቀበልከው ምንም ነገር የለም ። ከተቀበልህም የምትመካበት አንዳች ነገር የለህም (1ቆሮ. 4 ፡ 7) ። የዛሬ ስኬትህ የሁልጊዜ ስኬት አይደለምና እንዳረጀ ወዳጅ በበላህበት ቤት ጓሮ አትለፍ ። እንደ ጎርፍ በመንገድ ያገኘኸውን ተሸክመህ አትጓዝ ። አንገት የተሠራው ለጌጥ ሳይሆን ዞሮ ለማየት ነው ። ከስንት ሞት አምልጠህ ፣ የወዳጅህን ሞት አትመኝ ። ካልጨመሩበት ይቀንሳልና ወዳጅህን ወዳጅ አገኘሁ ብለህ አትግፋው ። ወረት የሰይጣን ልጅ ያደርጋል ። እወድሃለሁ ያለህ ሁሉ አይወድህምና ወላጆችህን አትግፋ ። “የወረት ውሻ ስሟ ወለተ ጴጥሮስ ነው” ይባላል ። እፍ ለማንደድ ፣ እፍ ለማጥፋት ነውና ዛሬ ካገኘኸው ጋር እፍ አትበል ። የፊት ወዳጅህን ጨርሰህ ክፉ ነው አትበል ፣ የኋላው ይታዘብሃል ። አዎ የመጣህበትን ታውቀዋለህ የመጣህበትን አትርሳ ። የመጣህበት ሲጠፋህ የምትሄድበት ይጠፋሃል ። ወዳጅ በብር አይለወጥም ፣ ወዳጅ ውድ ነው ፣ በወርቅ አይለወጥም !
ከወዳጅህ ጋር ለማርጀት ያብቃህ !
ይቀጥላል
ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ሚያዝያ 17 ቀን 2016 ዓ.ም.
12- የመጣህበትን አትርሳ
ሕይወት መንገድ ነው ። መንገድ የመጣንበት ደግሞም የምንሄድበት ነው ። ሀብት ቢነጥፍ ፣ ጉልበት ቢከዳ ፣ ወዳጅ ጠላት ቢሆን ሕይወት ይቀጥላል ። ሁሉም ሰው የራሱ የሆነ ሕይወት አለው ። በእግዚአብሔር ፈቃድ የጀመረች ሕይወቱ በእርሱ ፈቃድ ትቆማለች ። ከበሽታ የተነሣ ቢመረር ፣ ከማጣት የተነሣ ቢያለቅስ ፣ ከወዳጅ ሞት የተነሣ ቢከፋው ሕይወት ትቀጥላለች ። አቀባበሉ ግን ቀጣዩን ብርሃን ወይም ጨለማ ያደርገዋል ። በአንድ ዓይነት መከራ ውስጥ የሚያልፉ ሁለት ሰዎች አንዱ ቢስቅ ሌላው ቢያለቅስ ጉዳዩ የአቀባበል ነው ። አቀባበሉ ያቀለዋል አሊያም ያከብደዋል ። ያመንነውን እንወርሳለንና “ይህ ክፉ ነገር ለበጎ ነው የመጣው” ስንል በጎ ይሆናል ። አቀባበል ጨለማውን ብርሃን ያደርጋል ። መንገድ ከፍታም ዝቅታም አለው ። ሕይወት መንገድ ናትና የክብር ዘመን እንዳለ ሁሉ የውርደት ዘመንም አለ ። አልጫ አልጫ የሚል ቃል ተናግረን እንደ ጥቅስ የሚነገርበት ዘመን አለ ። የጥበብ ቃል ተናግረን “ምነው ሞቶ ባረፈው” የምንባልበት ዘመን አለ ። አንዳንድ ሁኔታዎች መታገል ሳይሆን መታደል የሚያመጣቸው ሊሆኑ ይችላሉ ።
ተራራ የወጣው መንገደኛ ቁልቁለት እንደሚወርድ እርግጠኛ ነው ። ከተራራ ቀጥሎ ተራራ አይመጣምና ። የከበረም መዋረዱ አይቀርም ። “ፖለቲከኛና አትሌት በቃህ ካልተባሉ አያቆሙም” ይባላል ። እንደ ከበሩ ዞር ማለት ትልቅ ጥበብ ነው ። ከሐር መነሳንስ ወደ ጭቃ ጅራፍ ሳይለወጥ ዞር ማለት አዋቂነት ነው ። ይልቁንም በአገራችን ወረት በዙፋን ተቀምጦ እየገዛን ይመስላል ። “አንቱ” ያልነውን ሰውዬ “አንተ” ለማለት እንቸኩላለን ። መንገድ ተመዝማዛ ነው ። ቀጣዩ አልታይ እያለን የምንጨነቅበት ፣ ተስፋ ዘይቱ እንዳለቀ መቅረዝ ጭል ፣ ጭል የሚልበት ጊዜ ጥቂት አይደለም ። ተስፋ መቍረጥም የሕይወት አንድ አካል ነው ። ያልገባን ነገር ቢኖርም “እግዚአብሔር አዋቂ ነው” ማለት ያሳርፋል ። “እግዚአብሔር አዋቂ ነው” ማለት “እግዚአብሔር ያውቅልኛል” ማለት ነው ። መንገድ ሸካራ ነው ። ውስጣችን በሰዎች ክፋት የሚበከልበት ፣ ጥርጣሬ ቀናችንን የሚዋጋበት ጊዜ ብዙ ነው ። ሰዎችን ይቅር ለማለት ከራሳችን ጋር ግብ ግብ ውስጥ የምንገባበት ፣ ቂመኝነትን ዳግም ላለመጎዳት የሚጋረድ ጋሻ አድርገን የምንመለከትበት ጊዜ አያሌ ነው ። “ተበድዬስ ይቅር አልልም” እያልን እንዘፍናለን ። ይቅር የምንለውማ ስንበደል ነው ። ፍቅር የመበደል አጥር ሲሻገር እውነተኛ ይሆናል ።
ሕይወት መንገድ ነው ። መንገድ መነሻ አለው ፣ መንገድ መድረሻ አለው ። እግዚአብሔርን ማመን ያስፈለገን መነሻና መድረሻ ያለው ሕይወት ለመያዝ ነው ። እግዚአብሔርን ካላመንን ሕይወታችን መነሻና መድረሻ የሌላት ፣ መሐል ባሕር ላይ ያለ መቅዘፊያ የተለቀቀች ጀልባ ትሆናለች ። የመጣንበት የምንሄድበትን ይወስነዋል ። የመጣንበትን በትክክል ማሰብ ከቻልን ምስጋና በአፋችን ይሞላል ። ሰውን መበደል እንጸየፋለን ። ሌሎችን ለመርዳት እንነሣሣለን ። መካሪ ሁነን አዲስ ትውልድን እናበረታታለን ። ግፍን እንጸየፋለን ። ማንንም አንንቅም ። አዎ ሕፃናት ነበርን ። ሕፃናትን መውደድና ማክበር አለብን ። አዎ ዕራቁታችንን ተወልደናል ። ስለዚህ ድሀ ነበርኩ ማለት የሚያሳፍር አይደለም ። ያለ ፍትሕ ታስረናል ። ስለዚህ ያለ ፍትሕ ሌሎችን መጉዳት አይገባንም ። አንድ ድቃቂ ሣንቲም ሊቸግር እንደሚችል ኑሮአችን ምስክር ነው ። የመጣንበትን ብናስብ እጆቻችን ለመርዳት ይዘረጉ ነበር ።
አዎ የመጣህበትን አትርሳ ። የመጣኸው ካፈር ነው ። አንድ ቀን ወደ አፈር ትመለሳለህና ኩራትን ተው ። ፊደል ለማወቅ ብዙ ወራት የፈጀብህ ፣ በብዙ ጥረት አዋቂ የሆንህ ፣ የብዙዎችን ጉልበት የጨረስህ ነህና ሰውን “ደንቆሮ” ብለህ ለመሳደብ አትድፈር ። ዕድሉን ቢያገኝ ሁሉም ሊቅ ይሆን ነበር ። ያደግህበት ሰፈር ዛሬ ካየሃቸው ውብ ከተሞች የሚበልጥ ትዝታ ያለው ነውና ያደግክበትን ቀዬ ዞር ብለህ ተመልከት ። ያሳደጉህ እናቶች ፣ ዛሬም ረሀብ ዘመድ ሆኖ አልላቀቅ ያላቸው የአባትህና የእናትህ ጓደኞች አሉና ሄደህ ጠይቃቸው ፣ ካለህ ላይ አካፍላቸው ። ትንሹ ማሙሽ አድገህ ለመስጠት በመብቃትህ ፈጣሪያቸውን ባንተ ምክንያት ያመስግኑት ። መምህራኖችህ ዛሬ ከእነርሱ የበለጠ እውቀት ብትይዝም የወጣህባቸው መሰላል ናቸውና አክብራቸው ። ዋጋቸውንም ሂደህ ንገራቸው ። የወጣህበት መሰላል ለመውረድም ይረዳልና ወጣሁ ብለህ ገፍተህ አትጣለው ። አንተን አንቱ ያሰኘህ ሕዝብ ነውና ሕዝብህን አትናቅ ። ሕዝብ ያንተ ሎሌ ሳይሆን አንተ የሕዝብ አሽከር መሆንህን እመን ። የሥልጣን በትር አንድ ቀን ከእጅ ያመልጣል ። የደጁን ስትገፋ ልጅህ እንደ አቤሴሎም ለሞት ይፈልግሃል ። ሥልጣን ፀሐይ ነው ። ምንም ቢደምቅ መጥለቁ አይቀርም ። አዎ የድሀ ልጅ ነበርህና የመጣህበትን አትርሳ ። በማጣት ዘመንህ ፣ በእስር ወራትህ የገባኸውን ቃል ኪዳን አትዘንጋ ። ዛሬ ሽቱ ስለተቀባህ ሰው ሁሉ የሚሸት መስሎህ አትጸየፈው ። የአንድ ቀን ውኃ ስታጣ አንተም ለመበላሸት ቅርብ ነህ ። የመጣህበትን አትርሳ ። ይህችን ከተማ ስትቀላቀል የነበረህን መደናገር አትዘንጋ ። ስለዚህ ማንንም መጤ ብለህ አትናገር ። ሁሉም ሰው መጤ ነው ። አንድ ቀን ይሄዳል ። በዚህ ዓለም ላይ መሰንበት እንጂ መቅረት የለም ።
የመጣህበትን አትርሳ ። እግዚአብሔር ብቻውን አስተማረኝ ብለህ ያስተማሩህን አትካድ ። እግዚአብሔር ብቻውን ረዳኝ በሚል ዘይቤ የሰውን ውለታ አታጥፋ ። የእናቴን ጡት አልጠባሁም ፣ የማንም ውለታ አላለፈብኝም ብለህ አትገበዝ ። ያልተቀበልከው ምንም ነገር የለም ። ከተቀበልህም የምትመካበት አንዳች ነገር የለህም (1ቆሮ. 4 ፡ 7) ። የዛሬ ስኬትህ የሁልጊዜ ስኬት አይደለምና እንዳረጀ ወዳጅ በበላህበት ቤት ጓሮ አትለፍ ። እንደ ጎርፍ በመንገድ ያገኘኸውን ተሸክመህ አትጓዝ ። አንገት የተሠራው ለጌጥ ሳይሆን ዞሮ ለማየት ነው ። ከስንት ሞት አምልጠህ ፣ የወዳጅህን ሞት አትመኝ ። ካልጨመሩበት ይቀንሳልና ወዳጅህን ወዳጅ አገኘሁ ብለህ አትግፋው ። ወረት የሰይጣን ልጅ ያደርጋል ። እወድሃለሁ ያለህ ሁሉ አይወድህምና ወላጆችህን አትግፋ ። “የወረት ውሻ ስሟ ወለተ ጴጥሮስ ነው” ይባላል ። እፍ ለማንደድ ፣ እፍ ለማጥፋት ነውና ዛሬ ካገኘኸው ጋር እፍ አትበል ። የፊት ወዳጅህን ጨርሰህ ክፉ ነው አትበል ፣ የኋላው ይታዘብሃል ። አዎ የመጣህበትን ታውቀዋለህ የመጣህበትን አትርሳ ። የመጣህበት ሲጠፋህ የምትሄድበት ይጠፋሃል ። ወዳጅ በብር አይለወጥም ፣ ወዳጅ ውድ ነው ፣ በወርቅ አይለወጥም !
ከወዳጅህ ጋር ለማርጀት ያብቃህ !
ይቀጥላል
ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ሚያዝያ 17 ቀን 2016 ዓ.ም.
HTML Embed Code: