Channel: እልመስጦአግያ+++
እለታዊ መልዕክት
"+ እናንተ የምድር ጨው ናችሁ . . . እናንተ የዓለም ብርሃን ናችሁ:: በተራራ ላይ ያለች ከተማ ልትሠወር አይቻላትም:: መብራትንም አብርተው በዕንቅብ በታች አይደለም እንጂ በመቅረዙ ላይ ያናሩታል:: በቤት ላሉት ሁሉም ያበራል:: መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ:: +"+ (ማቴ. 5:13-16)
"+ እናንተ የምድር ጨው ናችሁ . . . እናንተ የዓለም ብርሃን ናችሁ:: በተራራ ላይ ያለች ከተማ ልትሠወር አይቻላትም:: መብራትንም አብርተው በዕንቅብ በታች አይደለም እንጂ በመቅረዙ ላይ ያናሩታል:: በቤት ላሉት ሁሉም ያበራል:: መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ:: +"+ (ማቴ. 5:13-16)
ጭንቀት ~ምን ያህል ከአምላክ መንፈስ እንደራቅን የሚጠቁም ስሜት ነው::
ሰላም ~ ምን ያህል ወደ አምላክ መንፈስ እንደቀረብን የሚናገር ስሜት ነው::
ከፈጠረን አምላክ አስበልጠን ሌላ ነገር ስንፈልግ በውስጣችን ጭንቀት ይፈጠራል::በልባችን ፍርሃት እና ውጥረት ያድራል::
ከሁሉም ነገር አብልጠን የአምላክን መንፈስ ስንፈልግ ሰላም በውስጣችን ይወለዳል::ልባችን በፍቅር እና በደስታ ይሞላል::
ዓለም እና ነገሮቿን ሁሌም ከእኛ ጋር ማድረግ አንችልም::ሰው ..ገንዘብ …ስልጣን ….ዝና እና ወ.ዘ.ተ ምንም ጊዚያዊ ደስታን ቢሰጡም ቶሎቶሎ የመቀያየር ጠባይ አላቸው::ያዝናቸው ስንል ይሄዳሉ::
የማይሄደው እና ምንጊዜም በልባችን የሚኖረው እኛንም እስከመጨረሻ የሚወደን ቅዱሱ የእግዚአብሄር መንፈስ ብቻ ነው::
ገንዘብ ብናገኝ ብናጣ ~ሰው ቢፈልገን ባይፈልገን ~
ጤና ቢኖረን ባይኖረን በቅፅበት በሚለዋወጠው አለም ሁሌም የማይቀያየር አምላካችን ብቻ ነው::
ይህንን አምላክ ከዓለም ያስቀደሙ አለምን ያሸንፋሉ::ለከንቱ ምኞት ውድ ነፍሳቸውን አይሰጡም::በጊዜያዊ ደስታ ዘለዓለማዊውን አምላክ አይለውጡም::
በሚለዋወጠው ዓለም የማይለዋወጥ ግንኙነት ከአምላክ ጋር አድርገዋል::ከጊዚያዊው አብልጠው ዘለዓለማዊውን መርጠዋል::
እርሱ የእውነት መታመን የሚቻልበት ወዳጃቸው ነው::ጥበብ ~ፍቅር ~ሀይል ~ስልጣን ~በረከት ~ሀብት እና ሁሉም ነገር አለው::
ወደዚህ መልካም አምላክ ስንቀርብ እርሱም ወደ እኛ ይቀርባል::ሰላሙንም በልባችን ያኖራል::ጭንቀት እና ፍርሃታችን ይወገዳል::
ቃለ ሕይወትን ያሰማን
🌹 የእግዚአብሔር ቸርነት 🌹
🌹 የእመቤታችን ጸሎት 🌹
🌹 የቅዱስ ሚካኤል ጥበቃ🌹
🌹 የቅዱሳን ሁሉ በረከትና ረድኤት 🌹
ከሁላችን ጋራ ይሁን
የሰላም ሌሊት ያድርግልን እግዚአብሔር
የትንቢቱ መፈጸሚያ ከመሆን ይሰዉረን
ደህና እደሩ ተወዳጆች
ሰላም ~ ምን ያህል ወደ አምላክ መንፈስ እንደቀረብን የሚናገር ስሜት ነው::
ከፈጠረን አምላክ አስበልጠን ሌላ ነገር ስንፈልግ በውስጣችን ጭንቀት ይፈጠራል::በልባችን ፍርሃት እና ውጥረት ያድራል::
ከሁሉም ነገር አብልጠን የአምላክን መንፈስ ስንፈልግ ሰላም በውስጣችን ይወለዳል::ልባችን በፍቅር እና በደስታ ይሞላል::
ዓለም እና ነገሮቿን ሁሌም ከእኛ ጋር ማድረግ አንችልም::ሰው ..ገንዘብ …ስልጣን ….ዝና እና ወ.ዘ.ተ ምንም ጊዚያዊ ደስታን ቢሰጡም ቶሎቶሎ የመቀያየር ጠባይ አላቸው::ያዝናቸው ስንል ይሄዳሉ::
የማይሄደው እና ምንጊዜም በልባችን የሚኖረው እኛንም እስከመጨረሻ የሚወደን ቅዱሱ የእግዚአብሄር መንፈስ ብቻ ነው::
ገንዘብ ብናገኝ ብናጣ ~ሰው ቢፈልገን ባይፈልገን ~
ጤና ቢኖረን ባይኖረን በቅፅበት በሚለዋወጠው አለም ሁሌም የማይቀያየር አምላካችን ብቻ ነው::
ይህንን አምላክ ከዓለም ያስቀደሙ አለምን ያሸንፋሉ::ለከንቱ ምኞት ውድ ነፍሳቸውን አይሰጡም::በጊዜያዊ ደስታ ዘለዓለማዊውን አምላክ አይለውጡም::
በሚለዋወጠው ዓለም የማይለዋወጥ ግንኙነት ከአምላክ ጋር አድርገዋል::ከጊዚያዊው አብልጠው ዘለዓለማዊውን መርጠዋል::
እርሱ የእውነት መታመን የሚቻልበት ወዳጃቸው ነው::ጥበብ ~ፍቅር ~ሀይል ~ስልጣን ~በረከት ~ሀብት እና ሁሉም ነገር አለው::
ወደዚህ መልካም አምላክ ስንቀርብ እርሱም ወደ እኛ ይቀርባል::ሰላሙንም በልባችን ያኖራል::ጭንቀት እና ፍርሃታችን ይወገዳል::
ቃለ ሕይወትን ያሰማን
🌹 የእግዚአብሔር ቸርነት 🌹
🌹 የእመቤታችን ጸሎት 🌹
🌹 የቅዱስ ሚካኤል ጥበቃ🌹
🌹 የቅዱሳን ሁሉ በረከትና ረድኤት 🌹
ከሁላችን ጋራ ይሁን
የሰላም ሌሊት ያድርግልን እግዚአብሔር
የትንቢቱ መፈጸሚያ ከመሆን ይሰዉረን
ደህና እደሩ ተወዳጆች
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_ለሴት_ተክለ_አቤል_ርእሰ_አበው። ተዘከረኒ እግዚኦ በምረትከ በእንተ ሴት ገብርከ ዘዓቀበ ትእዛዘከ ሕገከ ወሥርዓተከ፣ መሐረኒ በእንቲኣሁ ወአድኅነኒ እምሲኦል መሪር ለገብርከ አሜን"። ትርጉም፦ #የአባቶች_ራስ_ለኾነ_ለአቤል_ምትክ #ለሴት_ሰላምታ_ይገባል፤ አቤቱ ትእዛዝኽን ሕግኽንና ሥርዐትኽን የጠበቀ ስለኾነ ስለ አገልጋይኽ ስለ ሴት በምሕረትኽ ዐስበኝ፤ ስለ ርሱ ብለኽ ማረኝ፤ ከመሪር ሲኦል እኔን አገልጋይኽን አድነኝ፤ አሜን። #ሊቁ_አባ_ጊዮርጊስ_ዘጋስጫ_በተአምኆ_ቅዱሳን_ላይ።
@JohnDPT27
✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_ለሴት_ተክለ_አቤል_ርእሰ_አበው። ተዘከረኒ እግዚኦ በምረትከ በእንተ ሴት ገብርከ ዘዓቀበ ትእዛዘከ ሕገከ ወሥርዓተከ፣ መሐረኒ በእንቲኣሁ ወአድኅነኒ እምሲኦል መሪር ለገብርከ አሜን"። ትርጉም፦ #የአባቶች_ራስ_ለኾነ_ለአቤል_ምትክ #ለሴት_ሰላምታ_ይገባል፤ አቤቱ ትእዛዝኽን ሕግኽንና ሥርዐትኽን የጠበቀ ስለኾነ ስለ አገልጋይኽ ስለ ሴት በምሕረትኽ ዐስበኝ፤ ስለ ርሱ ብለኽ ማረኝ፤ ከመሪር ሲኦል እኔን አገልጋይኽን አድነኝ፤ አሜን። #ሊቁ_አባ_ጊዮርጊስ_ዘጋስጫ_በተአምኆ_ቅዱሳን_ላይ።
@JohnDPT27
የእለቱ መልዕክት
"እኔ ሕያው ነኝና ኃጢአተኛው ከመንገዱ ተመልሶ በሕይወት ይኖር ዘንድ እንጂ ኃጢአተኛው ይሞት ዘንድ አልፈቅድም" ይላል ጌታ እግዚአብሔር:: "የእሥራኤል ቤት ሆይ! ተመለሱ:: ከክፉ መንገዳችሁ ተመለሱ:: ስለ ምንስ ትሞታላችሁ?" በላቸው:: (ሕዝ. 33:11)
"እኔ ሕያው ነኝና ኃጢአተኛው ከመንገዱ ተመልሶ በሕይወት ይኖር ዘንድ እንጂ ኃጢአተኛው ይሞት ዘንድ አልፈቅድም" ይላል ጌታ እግዚአብሔር:: "የእሥራኤል ቤት ሆይ! ተመለሱ:: ከክፉ መንገዳችሁ ተመለሱ:: ስለ ምንስ ትሞታላችሁ?" በላቸው:: (ሕዝ. 33:11)
"እግዚአብሔርን "ለምን ትረሳኛለህ?" አትበለው "ጌታ ሆይ የረሳሁህን እኔን ይቅርበለኝ፤ ፍቅርህን ዘንግቻለሁና በመከራዬ ጊዜም አስበኝ" በለው እንጂ።"
#አቡነ_ሽኖዳ_ሳልሳዊ
ቃለ ሕይወትን ያሰማን
🌹 የእግዚአብሔር ቸርነት 🌹
🌹 የእመቤታችን ጸሎት 🌹
🌹 የቅዱስ ሚካኤል ጥበቃ🌹
🌹 የቅዱሳን ሁሉ በረከትና ረድኤት 🌹
ከሁላችን ጋራ ይሁን
የሰላም ሌሊት ያድርግልን እግዚአብሔር
የትንቢቱ መፈጸሚያ ከመሆን ይሰዉረን
#አቡነ_ሽኖዳ_ሳልሳዊ
ቃለ ሕይወትን ያሰማን
🌹 የእግዚአብሔር ቸርነት 🌹
🌹 የእመቤታችን ጸሎት 🌹
🌹 የቅዱስ ሚካኤል ጥበቃ🌹
🌹 የቅዱሳን ሁሉ በረከትና ረድኤት 🌹
ከሁላችን ጋራ ይሁን
የሰላም ሌሊት ያድርግልን እግዚአብሔር
የትንቢቱ መፈጸሚያ ከመሆን ይሰዉረን
💛
🕊 ቅ ዱ ስ አ ማ ኑ ኤ ል 🕊
❝ ሰላም ለአስተርእዮቱ በሥጋ
ዘአስተርአየ ገሃድ ከመ የሀበነ ጸጋ ❞
[ በግልጽ ጸጋን ያድለን ዘንድ በሥጋ የተገለጠ ለኾነ ለእርሱ አገላለጥ ሰላምታ ይገባል ]
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
❝ ስለዚህ ጌታ ራሱ ምልክት ይሰጣችኋል ፤ እነሆ ፥ ድንግል ትፀንሳለች ፥ ወንድ ልጅም ትወልዳለች ፥ ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች። ❞
[ ኢሳ.፯፥፲፬ ]
" Therefore the Lord himself shall give you a sign; Behold, a virgin shall conceive, and bear a son, and shall call his name Immanuel."
[ Isaiah 7:14 ]
🕊 ቅ ዱ ስ አ ማ ኑ ኤ ል 🕊
❝ ሰላም ለአስተርእዮቱ በሥጋ
ዘአስተርአየ ገሃድ ከመ የሀበነ ጸጋ ❞
[ በግልጽ ጸጋን ያድለን ዘንድ በሥጋ የተገለጠ ለኾነ ለእርሱ አገላለጥ ሰላምታ ይገባል ]
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
❝ ስለዚህ ጌታ ራሱ ምልክት ይሰጣችኋል ፤ እነሆ ፥ ድንግል ትፀንሳለች ፥ ወንድ ልጅም ትወልዳለች ፥ ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች። ❞
[ ኢሳ.፯፥፲፬ ]
" Therefore the Lord himself shall give you a sign; Behold, a virgin shall conceive, and bear a son, and shall call his name Immanuel."
[ Isaiah 7:14 ]
የእለቱ መልእክት 📜
"+ ስለዚህ ሰው አባቱንና እናቱን ይተዋል:: ከሚስቱም ጋር ይተባበራል:: ሁለቱም አንድ ሥጋ ይሆናሉ:: ይህ ምሥጢር ታላቅ ነው:: እኔ ግን ይህን ስለ ክርስቶስና ስለ ቤተ ክርትስቲያን እላለሁ:: ሆኖም ከእናንተ ደግሞ እያንዳንዱ የገዛ ሚስቱን እንዲህ እንደ ራሱ አድርጐ ይውደዳት:: ሚስቱም ባሏን ትፍራ:: +"+ (ኤፌ. 5:31)
"+ ስለዚህ ሰው አባቱንና እናቱን ይተዋል:: ከሚስቱም ጋር ይተባበራል:: ሁለቱም አንድ ሥጋ ይሆናሉ:: ይህ ምሥጢር ታላቅ ነው:: እኔ ግን ይህን ስለ ክርስቶስና ስለ ቤተ ክርትስቲያን እላለሁ:: ሆኖም ከእናንተ ደግሞ እያንዳንዱ የገዛ ሚስቱን እንዲህ እንደ ራሱ አድርጐ ይውደዳት:: ሚስቱም ባሏን ትፍራ:: +"+ (ኤፌ. 5:31)
ፀሐይ ብርሃን ካልሰጠች ፀሐይ አትባልም፤ ብርሃን አለመስጠት ተፈጥሮዋ አይደለምና፡፡ እንስሳት ካልተነፈሱ እንስሳት አይባሉም፤ መተንፈስ ተፈጥሮአቸው ነውና፡፡ ዓሣ ከውኃ ከወጣ ሕይወት ያለው ዓሣ መኾኑ ይቀርና ይሞታል፡፡ አንድ ክርስቲያንም እውነተኛ ክርስቲያን የሚባለው፡-
#ሲጸልይ_ነው፡፡ ክርስቲያን ማለት በወልድ ውሉድ በክርስቶስ ክርስቲያን በመንፈስ ቅዱስም መንፈሳዊ መባል ነውና፡፡ ልጅ ከኾኑ ደግሞ አባትን ማናገር ክርስቲያናዊ ተፈጥሮ ነውና፡፡
#ሲያመሰግን_ነው፡፡ ክርስቲያን ማለት እግዚአብሔር ፈጣሬ ዓለማት ነው ብሎ ማመን ነውና፡፡ ስለዚህ ለአንድ ክርስቲያን የሰማይና የምድር ውበት እየተመለከተ እግዚአብሔርን ማመስገኑ ክርስቲያናዊ ተፈጥሮው ነው፡፡
#ሲመጸውት_ነው፡፡ ክርስቲያን ማለት ሀብት ኹሉ ከእግዚአብሔር እንደ ኾነ መመስከር ነውና፡፡ ስለዚህ ራስን እንደ መልእክተኛ አድርጎ በመቁጠር ያለውን ለሌላው ማካፈል ክርስቲያናዊ ተፈጥሮው ነውና፡፡
#ቅዱሳት_መጻሕፍትን_ሲያነብ_ነው፡፡ ክርስቲያን ማለት በመንፈስ ቅዱስ ሀብት ደስ የሚሰኝ ነውና፡፡ይህን ለማድረግ ደግሞ መንፈስ ቅዱስ በቅዱሳት መጻሕፍት በኩል ሲናገር መስማት ለአንድ ክርስቲያን ክርስቲያናዊ ተፈጥሮው ነውና፡፡
(ገብረ እግዚአብሔር ኪደ)
ቃለ ሕይወትን ያሰማን
🌹 የእግዚአብሔር ቸርነት 🌹
🌹 የእመቤታችን ጸሎት 🌹
🌹 የቅዱስ ሚካኤል ጥበቃ🌹
🌹 የቅዱሳን ሁሉ በረከትና ረድኤት 🌹
ከሁላችን ጋራ ይሁን
የሰላም ሌሊት ያድርግልን እግዚአብሔር
የትንቢቱ መፈጸሚያ ከመሆን ይሰዉረን
#ሲጸልይ_ነው፡፡ ክርስቲያን ማለት በወልድ ውሉድ በክርስቶስ ክርስቲያን በመንፈስ ቅዱስም መንፈሳዊ መባል ነውና፡፡ ልጅ ከኾኑ ደግሞ አባትን ማናገር ክርስቲያናዊ ተፈጥሮ ነውና፡፡
#ሲያመሰግን_ነው፡፡ ክርስቲያን ማለት እግዚአብሔር ፈጣሬ ዓለማት ነው ብሎ ማመን ነውና፡፡ ስለዚህ ለአንድ ክርስቲያን የሰማይና የምድር ውበት እየተመለከተ እግዚአብሔርን ማመስገኑ ክርስቲያናዊ ተፈጥሮው ነው፡፡
#ሲመጸውት_ነው፡፡ ክርስቲያን ማለት ሀብት ኹሉ ከእግዚአብሔር እንደ ኾነ መመስከር ነውና፡፡ ስለዚህ ራስን እንደ መልእክተኛ አድርጎ በመቁጠር ያለውን ለሌላው ማካፈል ክርስቲያናዊ ተፈጥሮው ነውና፡፡
#ቅዱሳት_መጻሕፍትን_ሲያነብ_ነው፡፡ ክርስቲያን ማለት በመንፈስ ቅዱስ ሀብት ደስ የሚሰኝ ነውና፡፡ይህን ለማድረግ ደግሞ መንፈስ ቅዱስ በቅዱሳት መጻሕፍት በኩል ሲናገር መስማት ለአንድ ክርስቲያን ክርስቲያናዊ ተፈጥሮው ነውና፡፡
(ገብረ እግዚአብሔር ኪደ)
ቃለ ሕይወትን ያሰማን
🌹 የእግዚአብሔር ቸርነት 🌹
🌹 የእመቤታችን ጸሎት 🌹
🌹 የቅዱስ ሚካኤል ጥበቃ🌹
🌹 የቅዱሳን ሁሉ በረከትና ረድኤት 🌹
ከሁላችን ጋራ ይሁን
የሰላም ሌሊት ያድርግልን እግዚአብሔር
የትንቢቱ መፈጸሚያ ከመሆን ይሰዉረን
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ እንኳን #ለጾመ_ፍልሰታ_ለማርያም እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ "#በጾም_ወበጸሎት_ወበምጽዋት ወበተፋቅሮ ይሰረይ ኃጢአት ይእዜኒ ወዘልፈኒ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም"። ትርጉም፦ #በጾምና_በጸሎት_በምጽዋት በመፋቀርም ኃጢአት ይወገዳል ዛሬም ዘወትርም ለዘለዓለም። #ሊቁ_ቅዱስ_ያሬድ_በጾመ_ድጓው_ላይ።
❤ ጾም ለአገራችን ኢትዮጵያና ለሕዝቧቿ ፍቅር፣ሰላም አንድነትን፤ ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖታችን ለቅዱስ ሲኖዶስ አንድነት የሚያመጣ ያድርግል። በሰላም ጀምረን በሰላም ለመጨረስ ያብቃን ለሁላችንም የበረከት ጾም መልካም ሱባኤ ይሁንልን።
@Learn_with_John
@JohnDPT27
❤ እንኳን #ለጾመ_ፍልሰታ_ለማርያም እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ "#በጾም_ወበጸሎት_ወበምጽዋት ወበተፋቅሮ ይሰረይ ኃጢአት ይእዜኒ ወዘልፈኒ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም"። ትርጉም፦ #በጾምና_በጸሎት_በምጽዋት በመፋቀርም ኃጢአት ይወገዳል ዛሬም ዘወትርም ለዘለዓለም። #ሊቁ_ቅዱስ_ያሬድ_በጾመ_ድጓው_ላይ።
❤ ጾም ለአገራችን ኢትዮጵያና ለሕዝቧቿ ፍቅር፣ሰላም አንድነትን፤ ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖታችን ለቅዱስ ሲኖዶስ አንድነት የሚያመጣ ያድርግል። በሰላም ጀምረን በሰላም ለመጨረስ ያብቃን ለሁላችንም የበረከት ጾም መልካም ሱባኤ ይሁንልን።
@Learn_with_John
@JohnDPT27
መልካም ያደረጉ ብዙ ሴቶች አሉ
አንቺ ግን ከሁሉ ትበልጫለሽ።”
ምሳ. 31፡29
ክርስቶስን ያከበሩ፤ መንገዱን የተከተሉ ብዙ ሴቶች አሉ፤ እውነትን የመሰከሩ፤ ስለ ቃሉ የኖሩ ብዙ ሴቶች አሉ፤ መስዋዕትነትን የከፈሉ በሰማዕትነት ያለፉ ብዙ ሴቶች አሉ፤
ታላላቅ የምድር ነገስታትን፤ ታላላቅ ነቢያትን የወለዱ ብዙ ሴቶች አሉ፤ ከእነዚህ ሁሉ ግን አንቺ ትበልጫለሽ።
ቅድስት ድንግል ሆይ አንቺ እኮ ሰማይ ዙፋኑ ምድር መረገጫው የሆነ፤ ድንቅ መካር ኃያል አምላክ የሰላም አለቃ፤ ሁሉ በእርሱ የሆነ ከሆነውም አንዳችም እንኳን ያለርሱ ያልሆነ፤ ዓለምን ሁሉ ከሞት ወደ ሕይወት የመለሰ፤ መንበሩን የሚሸከሙ ኪሩቤልና ሱራፌል የሚንቀጠቀጡለት፤ የሁሉ ፈጣሪ፤ የሁሉ አምላክ የሆነው የኢየሱስ ክርስቶስ እናት ነሽ።
በፊትም አሁንም ወደፊትም ካንቺ በቀር ፈጣሪዋን ልጄ ብላ የምትጠራ ሴት አልነበረችም፣ የለችም፣ አትኖርምም፤ ክርስቶስም እናቴ ብሎ የሚጠራት ብቸኛዋ ሴት አንቺ ነሽ በእውነት ከሁሉ ትበልጫለሽ።
እናት ስትሆኝ ድንግል፤ ድንግል ስትሆኝ እናት በእውነት ከሁሉ ትበልጫለሽ። ትውልድ ሁሉ ብጽዕት ብሎ የሚጠራሽ ብቸኛዋ ሴት በእውነት ከሁሉ ትበልጫለሽ። እግዚአብሔር መርጦና ጠብቆ ያስቀረሽ ዘር በእውነት ከሁሉ ትበልጫለሽ። ለዓለም ሁሉ ድኅነት ምልክት የሆንሽ በእውነት ከሁሉ ትበልጫለሽ።
እናቴ ሆይ እንግዲህ እኔ ምን ልናገር? ሺህ ቃላትን ብደረድር ያንቺን ክብር ልገልፀውስ እንደምን እችላለሁ? አዎ አሁንም እላለሁ “መልካም ያደረጉ ብዙ ሴቶች አሉ አንቺ ግን ከሁሉ ትበልጫለሽ።”
📖ምሳ. 31፡29
✍ ብፁዕ አቡነ ሽኖዳ ሳልሳዊ
ቃለ ሕይወትን ያሰማን
🌹 የእግዚአብሔር ቸርነት 🌹
🌹 የእመቤታችን ጸሎት 🌹
🌹 የቅዱስ ሚካኤል ጥበቃ🌹
🌹 የቅዱሳን ሁሉ በረከትና ረድኤት 🌹
ከሁላችን ጋራ ይሁን
የሰላም ሌሊት ያድርግልን እግዚአብሔር
የትንቢቱ መፈጸሚያ ከመሆን ይሰዉረን
አንቺ ግን ከሁሉ ትበልጫለሽ።”
ምሳ. 31፡29
ክርስቶስን ያከበሩ፤ መንገዱን የተከተሉ ብዙ ሴቶች አሉ፤ እውነትን የመሰከሩ፤ ስለ ቃሉ የኖሩ ብዙ ሴቶች አሉ፤ መስዋዕትነትን የከፈሉ በሰማዕትነት ያለፉ ብዙ ሴቶች አሉ፤
ታላላቅ የምድር ነገስታትን፤ ታላላቅ ነቢያትን የወለዱ ብዙ ሴቶች አሉ፤ ከእነዚህ ሁሉ ግን አንቺ ትበልጫለሽ።
ቅድስት ድንግል ሆይ አንቺ እኮ ሰማይ ዙፋኑ ምድር መረገጫው የሆነ፤ ድንቅ መካር ኃያል አምላክ የሰላም አለቃ፤ ሁሉ በእርሱ የሆነ ከሆነውም አንዳችም እንኳን ያለርሱ ያልሆነ፤ ዓለምን ሁሉ ከሞት ወደ ሕይወት የመለሰ፤ መንበሩን የሚሸከሙ ኪሩቤልና ሱራፌል የሚንቀጠቀጡለት፤ የሁሉ ፈጣሪ፤ የሁሉ አምላክ የሆነው የኢየሱስ ክርስቶስ እናት ነሽ።
በፊትም አሁንም ወደፊትም ካንቺ በቀር ፈጣሪዋን ልጄ ብላ የምትጠራ ሴት አልነበረችም፣ የለችም፣ አትኖርምም፤ ክርስቶስም እናቴ ብሎ የሚጠራት ብቸኛዋ ሴት አንቺ ነሽ በእውነት ከሁሉ ትበልጫለሽ።
እናት ስትሆኝ ድንግል፤ ድንግል ስትሆኝ እናት በእውነት ከሁሉ ትበልጫለሽ። ትውልድ ሁሉ ብጽዕት ብሎ የሚጠራሽ ብቸኛዋ ሴት በእውነት ከሁሉ ትበልጫለሽ። እግዚአብሔር መርጦና ጠብቆ ያስቀረሽ ዘር በእውነት ከሁሉ ትበልጫለሽ። ለዓለም ሁሉ ድኅነት ምልክት የሆንሽ በእውነት ከሁሉ ትበልጫለሽ።
እናቴ ሆይ እንግዲህ እኔ ምን ልናገር? ሺህ ቃላትን ብደረድር ያንቺን ክብር ልገልፀውስ እንደምን እችላለሁ? አዎ አሁንም እላለሁ “መልካም ያደረጉ ብዙ ሴቶች አሉ አንቺ ግን ከሁሉ ትበልጫለሽ።”
📖ምሳ. 31፡29
✍ ብፁዕ አቡነ ሽኖዳ ሳልሳዊ
ቃለ ሕይወትን ያሰማን
🌹 የእግዚአብሔር ቸርነት 🌹
🌹 የእመቤታችን ጸሎት 🌹
🌹 የቅዱስ ሚካኤል ጥበቃ🌹
🌹 የቅዱሳን ሁሉ በረከትና ረድኤት 🌹
ከሁላችን ጋራ ይሁን
የሰላም ሌሊት ያድርግልን እግዚአብሔር
የትንቢቱ መፈጸሚያ ከመሆን ይሰዉረን
"ባርነቴን ላንቺ በመስጠት ስሜን እንደጻፍሁ እንዲሁም የሰጠሁሽን የባርነቴን ደብዳቤ ጻፊ ልጅሽ በደሙ የዋጀኝ እኔን እንድጎዳ አትጣይኝ ልጅሽንም እንዲህ በይ ይህንን ጎስቋላ ባሪያ በክቡር ደምህ የገዛኸውን ስለ በደሉ ስለ ጉስቁልናው አትናቀው ገንዘቡን በወርቁ የገዛውን ለመጥላት የሚችል የለምና።"
✍አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
✍አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
#ተወዳጁ_ልጅሽ_እንዲመግበኝ_ትለምኝልኝ_ዘንድ_እማጸንሻለሁ
እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ። የመድኃኒት እናት ሆይ በመዓልትም በሌሊትም አማላጅ ትሆኝኝ ዘንድ እሰግድልሻለሁ። እመቤቴ ቅድስት ድንግል ማርያም ሆይ ከእርሱ የሚገኘውን ኃይልን ይሰጠኝ ዘንድ ከአንቺ ወደ ተወለደው ልጂሽ እንድትለምኝልኝ እማጸናለሁ። በመወለዱ ድኅነት የተገባሽ ሆነሻልና። በሔዋን ውድቀት ሆነ። አብ በመላእክት አለቃ በቅዱስ ገብርኤል አማካኝነት ሰላምን የላከልሽ እመቤቴ ቅድስት ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ። ሰላምታን ሰጠሽ ሰገደልሽም። ጸጋን የተመላሽ ሆይ እግዚአብሔር ከአንቺ ጋር ነውና ሰላምታ ይገባሻል። እነሆ ትጸንሻለሽ ልጅም ትወልጃለሽ፣ ስሙንም አማኑኤል ትይዋለሽ። የልዑል ኃይል ይጸልልሻል፤ ከአንቺ የሚወለደውም ቅዱስ ነው፤ እርሱም የልዑል ልጅ ይባላል አለሽ።
በተቀደሰው ስሙ ኅሊናዬን ልቡናዬን እንዲቀድስ ትለምኝው ዘንድ እማጸንሻለሁ። ንጽሕት ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ። የሕይወት ቃል ከአንቺ ሰው ይሆን ዘንድ በሥጋ ከአንቺ ይወለድ ዘንድ የተገባሽ የመድኃኒት እናት እመቤታችን ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ። ከአንቺ በመዋሐዱም እኛ ዳንን። እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ። በእናታቸው ማሕፀን ሕፃናትን የሚስላቸው ከአባቱ እና ከመንፈስ ቅዱስ ጋርም ሁሉን የፈጠረው በማሕፀንሽ የተቀረጸብሽ የብርሃን እናት ሆይ እሰግድልሻለሁ። ረቂቅ ድንቅ ምሥጢርን ዓለምንም ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣውን እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ እለምንሻለሁ። በመንፈሳዊ ልደት ይወልደኝ ዘንድ ወደ እርሱ ዓለምና አዳኝ ወደ ሆነች ዕውቀት ከፍ ያደርገኝ ዘንድ ወደ እርሱ እንድትለምኝልኝ እለምንሻለሁ፣ አማጸንሻለሁ።
የሕይወት መገኛ የነገሥታት ንጉሥ የባለሥልጣናቱ ባለሥልጣን የአምላኮችን አምላክ በበረት ያስተኛሽው እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ። አዳኝ ስለሆነው ስለስምሽ እንዲረዳኝ ትለምኝልኝ ዘንድም ወደ አንቺ እለምናለሁ፤ እማልዳለሁም። በማየቱ አዳምንና ከእርሱ ጋር ያሉትን ሁሉ ነጻ ያወጣውን በክንድሽ የታቀፍሽው እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ።
በረቂቅ መመልከቱ እንዲመግበኝ ከሰይጣን መሰናክልም እንዲያድነኝ ትለምኝልኝ ዘንድ እለምንሻለሁ፤ እማጸንሽማለሁ። ዓለማትን ሁሉ ለሚመግበው ጡትሽን ያጠባሽው የመድኃኒት እናት እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ፤ የሰማይ ኃይላት የሚመገቡትም ከእርሱ ነው። ነፍሴን በፈቃዱ ከጸጋው ይመግባት ዘንድ ወደ እርሱ እንድትለምኝልኝ እማጸንሻለሁ።
እመቤቴ ድግል ማርያም ሆይ ተወዳጁ ልጅሽ እንደ ፍጹም ፈቃዱ እንዲመግበኝ በየጊዜው በየሰዐቱ አማላጅ ሁኚኝ። ይህችም ወደ እርሱ የምትለምኝውን ልመና የተመላች መጽሐፍ ናት ። የለመንሁትን ሁሉ እርሱ ያደርግልሻልና። ኃጢአቴን ይቅር ይለኝ ዘንድ ወደ እርሱ እንድትለምኝልኝ እማጸንሻለሁ። ሰላምን ስለሰጠሽ ስለ አብ ከአንቺ ስለተወለደው አንቺንም ስለተዋሐደው ከአንቺም ሰው ስለሆነው ስለወልድ፣ ስለቀደሰሽ፣ ከሦስቱ ቅዱስ ለአንዱ ማደሪያ ለመሆን እስከሚገባሽ ድረስ ስላነጻሽ ስለመንፈስቅዱስም እለምንሻለሁ። አገልጋይሽን ተወዳጁ ልጅሽ እንዲመግበኝ ትለምኝልኝ ዘንድ እማጸንሻለሁ። ለዘለዓለሙ አሜን።
#ቅዱስ_ባስልዮስ_ዘቂሳርያ
(Deacon Birhanu Admass የተረጎመው)
እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ። የመድኃኒት እናት ሆይ በመዓልትም በሌሊትም አማላጅ ትሆኝኝ ዘንድ እሰግድልሻለሁ። እመቤቴ ቅድስት ድንግል ማርያም ሆይ ከእርሱ የሚገኘውን ኃይልን ይሰጠኝ ዘንድ ከአንቺ ወደ ተወለደው ልጂሽ እንድትለምኝልኝ እማጸናለሁ። በመወለዱ ድኅነት የተገባሽ ሆነሻልና። በሔዋን ውድቀት ሆነ። አብ በመላእክት አለቃ በቅዱስ ገብርኤል አማካኝነት ሰላምን የላከልሽ እመቤቴ ቅድስት ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ። ሰላምታን ሰጠሽ ሰገደልሽም። ጸጋን የተመላሽ ሆይ እግዚአብሔር ከአንቺ ጋር ነውና ሰላምታ ይገባሻል። እነሆ ትጸንሻለሽ ልጅም ትወልጃለሽ፣ ስሙንም አማኑኤል ትይዋለሽ። የልዑል ኃይል ይጸልልሻል፤ ከአንቺ የሚወለደውም ቅዱስ ነው፤ እርሱም የልዑል ልጅ ይባላል አለሽ።
በተቀደሰው ስሙ ኅሊናዬን ልቡናዬን እንዲቀድስ ትለምኝው ዘንድ እማጸንሻለሁ። ንጽሕት ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ። የሕይወት ቃል ከአንቺ ሰው ይሆን ዘንድ በሥጋ ከአንቺ ይወለድ ዘንድ የተገባሽ የመድኃኒት እናት እመቤታችን ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ። ከአንቺ በመዋሐዱም እኛ ዳንን። እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ። በእናታቸው ማሕፀን ሕፃናትን የሚስላቸው ከአባቱ እና ከመንፈስ ቅዱስ ጋርም ሁሉን የፈጠረው በማሕፀንሽ የተቀረጸብሽ የብርሃን እናት ሆይ እሰግድልሻለሁ። ረቂቅ ድንቅ ምሥጢርን ዓለምንም ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣውን እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ እለምንሻለሁ። በመንፈሳዊ ልደት ይወልደኝ ዘንድ ወደ እርሱ ዓለምና አዳኝ ወደ ሆነች ዕውቀት ከፍ ያደርገኝ ዘንድ ወደ እርሱ እንድትለምኝልኝ እለምንሻለሁ፣ አማጸንሻለሁ።
የሕይወት መገኛ የነገሥታት ንጉሥ የባለሥልጣናቱ ባለሥልጣን የአምላኮችን አምላክ በበረት ያስተኛሽው እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ። አዳኝ ስለሆነው ስለስምሽ እንዲረዳኝ ትለምኝልኝ ዘንድም ወደ አንቺ እለምናለሁ፤ እማልዳለሁም። በማየቱ አዳምንና ከእርሱ ጋር ያሉትን ሁሉ ነጻ ያወጣውን በክንድሽ የታቀፍሽው እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ።
በረቂቅ መመልከቱ እንዲመግበኝ ከሰይጣን መሰናክልም እንዲያድነኝ ትለምኝልኝ ዘንድ እለምንሻለሁ፤ እማጸንሽማለሁ። ዓለማትን ሁሉ ለሚመግበው ጡትሽን ያጠባሽው የመድኃኒት እናት እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ፤ የሰማይ ኃይላት የሚመገቡትም ከእርሱ ነው። ነፍሴን በፈቃዱ ከጸጋው ይመግባት ዘንድ ወደ እርሱ እንድትለምኝልኝ እማጸንሻለሁ።
እመቤቴ ድግል ማርያም ሆይ ተወዳጁ ልጅሽ እንደ ፍጹም ፈቃዱ እንዲመግበኝ በየጊዜው በየሰዐቱ አማላጅ ሁኚኝ። ይህችም ወደ እርሱ የምትለምኝውን ልመና የተመላች መጽሐፍ ናት ። የለመንሁትን ሁሉ እርሱ ያደርግልሻልና። ኃጢአቴን ይቅር ይለኝ ዘንድ ወደ እርሱ እንድትለምኝልኝ እማጸንሻለሁ። ሰላምን ስለሰጠሽ ስለ አብ ከአንቺ ስለተወለደው አንቺንም ስለተዋሐደው ከአንቺም ሰው ስለሆነው ስለወልድ፣ ስለቀደሰሽ፣ ከሦስቱ ቅዱስ ለአንዱ ማደሪያ ለመሆን እስከሚገባሽ ድረስ ስላነጻሽ ስለመንፈስቅዱስም እለምንሻለሁ። አገልጋይሽን ተወዳጁ ልጅሽ እንዲመግበኝ ትለምኝልኝ ዘንድ እማጸንሻለሁ። ለዘለዓለሙ አሜን።
#ቅዱስ_ባስልዮስ_ዘቂሳርያ
(Deacon Birhanu Admass የተረጎመው)
"ዘወትር በዐይንህ ፊት ፈሪሃ እግዚአብሔር ይኑር፤ ሕይወትና ሞት የሚሰጠውን አዘክረው፡፡ ዓለምንና በዓለም ያለውን ሁሉ ጥላው፤ ከሥጋ ብሔር ቃል የገባኸውን አትርሳ፤ ያም በፍርድ ቀን ካንተ ይፈለግብሃል፡፡ ረኀብን በጸጋ ተቀበለው፤ ተጠማ፥ ተራቆት፥ ንቁና በሐዘን የምትኖር ሁን፡፡ በልቡናህ አልቅስና ጩኽ፤ ለእግዚአብሔር የምትመች መሆን አለመሆንህን ፈትን፤ ሥጋህን ቀጥተህ ነፍስህን ታድናት ዘንድ፡፡”
✍ (አባ እንጦንስ
✍ (አባ እንጦንስ
Forwarded from መንፈሳዊ ግጥሞች ዘ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ
የመዳን ቀን....
ሀጥያት በደል ቢከበኝም፤
ካንተ በቀር ሰው የለኝም።
ነውሬ በዝቶ ከዘመኔ፥ ከፀጋህ ቢያጎድለኝም፤
ይቅር የሚል የሚያድነኝ ፥ካንተ በቀር ሰው የለኝም።
ሙሉ መስሎ ያለም ደስታ፥ ሞኙን ልቤን ያማለለ፤
ያልወጣሁት የሀጢያት ማጥ፥የጠለቀ ገደል አለ።
(አቤቱ...)
:
ሲጎድልብኝ ላንተ ማልቀስ፥ ሲሞላልኝ ወደ ሀጢያት፤
አንተ ግን አልቸኮልክም፥ ለበደሌ እኔን መቅጣት።
ነብሴን ፀፀት እያወካት፥ ሰውነቴ ሰላም አቶ፤
ተስፋ ከልቤ ተሰዶ፥ መጽናናቴ ውስጤ ሞቶ።
(ማረኝ...)
፥
አይነ ህሊናዬ ታወሮ፥ ልቦናዬ ድንጋይ ሆኗል፤
በህይወቴ ብርሀን የለም፥ የጨለማዬ ዋሻ ገኗል።
ከሀጢያቴ ጉድጓድ እጮሀለሁ፥ ትሰማለህ ስጠራህ፤
እኔን ወዳንተ ሚመመልስ፥ አንድ ቃልስ ታጣለህ?
(ይቅር...)
፥
ያሳየኛል ያ ጠላቴ፥ በምናቤ ከፍታዬን፤
ዛሬን ንዶ አደላድሎ፥ ያሳለፍኩት ያን ደስታዬን።
የቆሮንጦሱ ፈተናህ፥ ዛሬም እኔን ይገጥመኛል፤
ድንጋይ-ዳቦ ስልጣን-ጀብዱ፥ ይሄን ሁሉ ያስመኘኛል።
(በለኝ...)
፥
ጌታዬ ሆይ እባክህን?
አምላኬ ሆይ እባክህን፧
ልብ ስጠኝ፤
ጊዜ ስጠኝ፤
አውጣኝ ከዚህ ከቅዠቱ፥ ከከንቱ አለም፤
ካንተ በቀር ሌላ ማንም፥ እውነት መንገድ ህይወት የለም።
(እግዚአብሔር...)
፥
ልናዘዛት ያቺን ሀጢያት፥ የማፍራትን የዘውትሬን፤
ልናዘዛት ከኔ ትውጣ፥ በንስሐ ልጠብ ነውሬን።
ልናዘዛት ያቺን ሀጢያት፥ ህሊናዬ ነጻ ይውጣ፤
ልናዘዛት እሷን ልተው፥ የመዳን ቀን እንዲመጣ።
(በሚገኝበት ጊዜ ፈልጉት፥)
፥
በምህረትህ ብዛት፥ ወደ ቤትህ አስገባኝ፤
በተወደደ ጊዜ ስማኝ፥ በማዳንህ ቀን ርዳኝ።
እስክወጣ ጥቂት ታገስ፥ በመአትህ አትቅሰፈኝ፣
እስክናዘዝ ጥቂት ታገስ፥ ይቺን አመት ብቻ ተወኝ።
(ቀርቦም ሳለ ጥሩት፤)
+++
“በተወደደ ሰዓት ሰማሁህ
በመዳንም ቀን ረዳሁህ ይላልና፤
እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤
እነሆ፥ የመዳን ቀን አሁን ነው።”
— 2ኛ ቆሮ 6፥2
+++
©ታዜና
™ #መንፈሳዊ_ግጥሞች
hottg.com/Menfesawigetmoch
ሀጥያት በደል ቢከበኝም፤
ካንተ በቀር ሰው የለኝም።
ነውሬ በዝቶ ከዘመኔ፥ ከፀጋህ ቢያጎድለኝም፤
ይቅር የሚል የሚያድነኝ ፥ካንተ በቀር ሰው የለኝም።
ሙሉ መስሎ ያለም ደስታ፥ ሞኙን ልቤን ያማለለ፤
ያልወጣሁት የሀጢያት ማጥ፥የጠለቀ ገደል አለ።
(አቤቱ...)
:
ሲጎድልብኝ ላንተ ማልቀስ፥ ሲሞላልኝ ወደ ሀጢያት፤
አንተ ግን አልቸኮልክም፥ ለበደሌ እኔን መቅጣት።
ነብሴን ፀፀት እያወካት፥ ሰውነቴ ሰላም አቶ፤
ተስፋ ከልቤ ተሰዶ፥ መጽናናቴ ውስጤ ሞቶ።
(ማረኝ...)
፥
አይነ ህሊናዬ ታወሮ፥ ልቦናዬ ድንጋይ ሆኗል፤
በህይወቴ ብርሀን የለም፥ የጨለማዬ ዋሻ ገኗል።
ከሀጢያቴ ጉድጓድ እጮሀለሁ፥ ትሰማለህ ስጠራህ፤
እኔን ወዳንተ ሚመመልስ፥ አንድ ቃልስ ታጣለህ?
(ይቅር...)
፥
ያሳየኛል ያ ጠላቴ፥ በምናቤ ከፍታዬን፤
ዛሬን ንዶ አደላድሎ፥ ያሳለፍኩት ያን ደስታዬን።
የቆሮንጦሱ ፈተናህ፥ ዛሬም እኔን ይገጥመኛል፤
ድንጋይ-ዳቦ ስልጣን-ጀብዱ፥ ይሄን ሁሉ ያስመኘኛል።
(በለኝ...)
፥
ጌታዬ ሆይ እባክህን?
አምላኬ ሆይ እባክህን፧
ልብ ስጠኝ፤
ጊዜ ስጠኝ፤
አውጣኝ ከዚህ ከቅዠቱ፥ ከከንቱ አለም፤
ካንተ በቀር ሌላ ማንም፥ እውነት መንገድ ህይወት የለም።
(እግዚአብሔር...)
፥
ልናዘዛት ያቺን ሀጢያት፥ የማፍራትን የዘውትሬን፤
ልናዘዛት ከኔ ትውጣ፥ በንስሐ ልጠብ ነውሬን።
ልናዘዛት ያቺን ሀጢያት፥ ህሊናዬ ነጻ ይውጣ፤
ልናዘዛት እሷን ልተው፥ የመዳን ቀን እንዲመጣ።
(በሚገኝበት ጊዜ ፈልጉት፥)
፥
በምህረትህ ብዛት፥ ወደ ቤትህ አስገባኝ፤
በተወደደ ጊዜ ስማኝ፥ በማዳንህ ቀን ርዳኝ።
እስክወጣ ጥቂት ታገስ፥ በመአትህ አትቅሰፈኝ፣
እስክናዘዝ ጥቂት ታገስ፥ ይቺን አመት ብቻ ተወኝ።
(ቀርቦም ሳለ ጥሩት፤)
+++
“በተወደደ ሰዓት ሰማሁህ
በመዳንም ቀን ረዳሁህ ይላልና፤
እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤
እነሆ፥ የመዳን ቀን አሁን ነው።”
— 2ኛ ቆሮ 6፥2
+++
©ታዜና
™ #መንፈሳዊ_ግጥሞች
hottg.com/Menfesawigetmoch
Telegram
መንፈሳዊ ግጥሞች ዘ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ
ለሀሳብ ለአስትያየት >>>> @Tazena291
HTML Embed Code: