TG Telegram Group Link
Channel: ISLAMIC SCHOOL
Back to Bottom
[ ሁለቱ ፆታዎች: ሲሄዱ ]

ወንዶች በቃን ለማለት ይፈጥናሉ .... ሁሌም ግን ተመልሰው ይመጣሉ

ሴቶች ያስባሉ፣ አብዝተው ያስባሉ፣ ያለቅሳሉ፣ ይቀወር ይላሉ .... መቆየት ከሚገባቸው በላይ ይቆያሉ። ቆርጠው ከሄዱ .... አይመለሱም

{ ለምን ? }

ወንድ ልጅ በቃኝ ብሎ ሲሄድ ብዙ ጊዜ በድንገት ነው ... ስሜታዊ ሆኖ ነው። ክብሬ ተነካ፣ ተደፈርኩ ወይም ተናደድኩ በሚል መነሻ ለመሄድ ሲወስን ቀድሞ የሚታየው "ከእሷ የተሻለ" ሞልቶ ምን አንገበገበኝ የሚል ነው። ነገሮች እንዳሰቡት አልጋ በአልጋ አለመሆኑን የሚያየው "በቃኝ" ብሎ ከወጣ በኋላ ነው። ያኔ ገፍቶ የሄደውን ምቾት፣ ታማኝነት፣ እንክብካቤ፣ ልመና እና ልምምጥ፣ ማንም የማይታገሳቸውን ፀባዮቹን የታገሰችውን ሴት ይናፍቃል። ይኼኔ አይኑን በጨው አጥቦ ከለሊቱ 8 ሰዓት ላይ " እንዴት ነሽ .... ጠፋሽ" ብሎ መልዕክት ይልክልሻል።

በምሳሌ እንየው

አየለ ምርጥ የሴት ጓደኛ ነበረችው ... አየለች። የተከራየበት ቤት ድረስ ቤቱን አፅድታለት፣ ልብሱን አጥባ፣ ምግብ ሰርታ ... የወደፊት አላማህ ምንድነው ስትለው "ቤቲንግ በልቼ ሀብታም መሆን" ሲላት አንጀቷ እያረረ "ይቅናህ" ብላ ታግሳ እየኖረች ያለች ...

የሆነ ቀን በአሳብ አለመግባባት ይመጣል። አየለ ቱግ ይላል .... ሁለተኛ ቤቴ እንዳትደርሺ ብሎ ክብረ ቢስ በሆነ መልኩ ሰድቦ የቤቱን ቁልፍ ቀምቶ ያባራታል። ከሁለት እና ሶስት ወር በኋላ አብረውት ሲዘሉ ስለከረሙት ሴቶች ማሰብ እና ማስተዋል ይጀምራል። የከበቡት ሴቶች እሱ ጋር ለመምጣት ኮንትራት ታክሲ ቤታቸው ድረስ እንዲላክላቸው የሚጠብቁ፣ ሲመጡ ቅንጡ ሆቴል ወስዶ እንዲጋብዛቸው የሚፈልጉ፣ ፍላጎታቸው በየምሽት ክለቡ እየዞሩ መጨፈር እና መዝናናት ብቻ መሆኑን እና ከእሱ ጋር የሚቆዪት የተሻለ ብር ያለው እስኪመጣ መሆኑን ይረዳል። ይኼኔ አየለች ጋር ስልኩን አንስቶ ይደውላል። ስልኩ አይሰራም .... አየለች ሲም ቀይራ፣ እራሷን ከነበረችበት የፍቅር ግንኙነት ለማራቅ ትግል ውስጥ ናት። አሁን ሄዳለች ... ላትመለስ።

ሴቶች ዝም ብለው፣ ብድግ ብለው፣ ከመሬት ተነስተው .... አይሄዱም። መጀመሪያ በስሜት መራቅ ይጀምራሉ። በዝምታ ውስጥ .... ስሜት አልባ መሆን ያስቀድማሉ። በጊዜ ሂደት  ..... መጨቃጨቅ፣ መወትወት፣ ነገሮችን ማስታወስ፣ ቅሬታን ማንሳት፣ እንዲህ ሁን እንዲህ አድርግ .... ማለት ያቆማሉ። ዝምታ ያበዛሉ .... ነገሮች ተስማምቷቸው ሳይሆን በአይምሮአቸው የመውጫ በሩ ግማሽ ላይ ደርሰው ነው። በሩን አልፈው የወጡ ጊዜ .... በህሊናቸው፣ በአይምሮአቸው፣ በልባቸው እና በነፍሳቸው ካንተ እርቀው ከሄዱ ሳምንታት ምናልባትም ወራት ሆኗቸዋል።

ያለፉትን አምስት አመታት አንድም ቀን ተግብረኸው የማታውቀውን ቃልህን በተስፋ እየጠበቀች፣ ውሸቶችህን ሁሉ ይቅር እያለች፣ ግማሽ እውነቶችህን እየተቀበለች .... ጢባጢቤ ስትጫወትባት ችላ ኖራለች። ካንተም ብሶ በቃኝ እያልክ እየሄድክ ስትመለስ ምንም እንዳልተፈጠረ ስትቀበልህ ቆይታለች። ያልገባህ ነገር በየቀኑ እየሸራረፍካት እንደነበረ ነው። የሆነ ቀን መከራከር ታቆማለች። እንደዘበት ትተውሀለች። ሁለነገሯን ጠቅላላ ከህይወትህ ውልቅ ትላለች። ልብህ አብጦ "የራሷ ጉዳይ" ... "ለምናኝ ትመለሳለች" ብለህ ታልፈዋለህ። ጊዜው ሲነጉድ ግራ ትጋባለህ .... እንደምንም ደፈር ብለህ ትደውላለህ .... ስልኳን ቀይራለች። ላትመለስ ሄዳለች።

ሴት ትታገሳለች፣ ሴት ብዙ ትችላለች .... ሲበቃት ግን ድምፅ አታሰማ፣ ድራማ አትሰራ .... በዝምታ ውልቅ ነው። መመለስ አይደለም ወደኋላ ዞራ አታይም።

የትም አትሄድም ጨዋታ ላይ ከሆንክ .... አንደምን አደርክ: አንድ ቀን ትሄዳለች፥ ደግሞም አትመለስም። ስትሄድ ደግሞ የምትዝረከረክ፣ የማይመቻት፣ የምትጎሳቆል ከመሰለህ .... እንደምን አመሸህ: ሰላሟን ይዛ፣ ክብሯን ጠብቃ፣ የፀጉር አሰራሯ ሁሉ "ይሄንን ከንቱ ሲጀመር ምን ስሆን አፈቀርኩት" የሚል መልዕክት እንዲሰጥህ አድርጋ ነው።




                    © Abby Junior


💐<<<<<<>>>>>>⭐️<<<<<<>>>>>>💐
hottg.com/IslamisUniverstiy_public_group
  hottg.com/IslamisUniverstiy_public_group
#ከሞትኩ_ልብሱን_ለሱ_ትሰጠዋለሀ

አል- አሕነፍ ኢብኑ ቀይስ አረቦች ዘንድ በጣም የሚከበር መሪና በህይወቱ አንዴ እንኳ ሲቆጣ ታይቶ የማይታወቅ የታጋሽነት ምሳሌ ነበር።

አንድ ጊዜ ለልብስ ሰፊ የሰጠው ልብስ ዘገየበትና ሁሌ ሊቀበለው ሲሄድ ነገ ና እያለው ሲያመላልሰው ቆይቶ ልብሱን ሳይሰጠው 2 ዓመት ሲያልፍ
.....አል-አሕነፍ ልጁን ይዞ ወደ ልብስ ሰፊው በመሄድ "ከሞትኩ ልብሱን ለሱ ትሰጠዋለህ" ብሎት ትቶት ሄደ ይባላል!🙄🙄🙄



ገርሞ የሚገርም ነዉ


💐<<<<<<>>>>>>⭐️<<<<<<>>>>>>💐
hottg.com/IslamisUniverstiy_public_group
  hottg.com/IslamisUniverstiy_public_group
ሀቢቡና ሰይዲና ሙሀመድ ﷺ እንዲህ ብለዋል-

✏️ #ከሴቶቻችሁ_ሁሉ_በላጮቹ
☞ ወላድ የሆኑት፣
☞ መልካም ፀባይ ያላቸው፣
☞ ስታማክሯቸው ምክራቸውን የሚለግሱና
☞ አላህን ፈሪዎቹ ናቸው፡፡


✏️ #ከሴቶቻችሁ_መጥፎዎቹ ደግሞ
☞ መተበሪጃት (ተገላልጠው የሚሄዱ) የሆኑት፣
☞ ሙተኸይላት በኩራት ተወጥረው የሚራመዱና
☞ በንግግር የሚደነፉት ሲሆነ እነርሱ መናፍቃን ናቸው፡፡ ብለዋል

⛔️ ተገላልጠዉ የሚሄዱት የሚለዉ ማንኛዉም እፍረተ ገላን አጋልጦ በከፊልም በሙሉም የሚያሳይ ያካትታል፡፡

#ለምሳሌ ሴቶች ፀጉርን ማሳየት,የተወጣጠረ ልብስ የሚለብሱ እና ሰፊ ሂጃብን የማይለብሱ ጊዜያዊ ትኩስ ቀበጥ ሴቶችን ያካትታል፡፡



ሙናፊቅነት ከባድ ነዉ ነብዩ ﷺ
ስለሙናፊቆች ሲናገሩ ከጀሀነም መጨረሻዉ እንደሚቀጡ ተናግረዋል፡፡ለሚያልፍ ቀን..ለሚጠፋ ዉበት..አፈር ለሚበላዉ ሰዉነት አላህ ጋር ግልፅ ጦርነት ባንገጥም ጥሩ ነዉ ...ፈጣሪ ጋር የገጠሙት ጦርነት ማለት ትዕዛዝን መጣስ እንደሆነ አንዘንጋ⚠️

       አሚር ሰይድ


4 another channal👇
             hottg.com/Islam_and_Science
💐<<<<<<>>>>>>⭐️<<<<<<>>>>>>💐
hottg.com/IslamisUniverstiy_public_group
  hottg.com/IslamisUniverstiy_public_group
HTML Embed Code:
2025/07/05 20:50:41
Back to Top