TG Telegram Group Link
Channel: Dr. Eyob Mamo
Back to Bottom
Forwarded from Dr. Eyob Mamo
የገንዘብ ፍሰት እውነታዎች!

1. ገንዘብን የማግኛውን መንገድ ካላወኩበት በሰው ላይ ጥገኛ እንደሆንኩ እኖራለሁ፡፡

2. የማገኘውን ገንዘብ በትክክለኛው መንገድ ማውጣትና መጠቀም ካልመድኩ ገንዘቡ የት እንደሚገባ ግራ እንደተጋባሁ እኖራለሁ፡፡

3. በእጄ ያለውን ገንዘብ ኢንቨስት በማድረግ ካላባዘሁት በአኗኗሬ ኋላ ቀር እሆናለሁ፡፡

4. ከማገኘው ገንዘብ ላይ መቆጠብን ካልተለማመድኩ ድንገተኛ ነገር ሲከሰት ግራ እጋባለሁ፡፡

5. ካለኝ ገንዘብ ላይ ለሰዎች መስጠትን ካልተለማመድኩ የመዝራት እና የማጨድን የማያለወጥ ሕግ ስለምገድበው ወደ እኔ የሚመጣውን የገንዘብ ፍሰት አቀዋርጠዋለሁ፡፡

በእነዚህ ወሳኝ ልምምዶችና በመሰል ርእሶች ዙሪያ የተዘጋጀው ስልጠና አያምልጣችሁ፡፡

የስልጠው ርእስ፡- “የገንዘብ አስተዳደር ክህሎት እና ዲሲፕሊን” (Money Management Skills and Discipline)

ስልጠናው የሚሰጠው፡- በዶ/ር ኢዮብ ማሞ

ስልጠናው የሚሰጥበት መንገድ፡- በonline (telegram live)

የስልጠናው ቀናት፡- ሰኔ 19, ሰኔ 26፣ ሐምሌ 3, ሐምሌ 10 እና ሐምሌ 17 (ለአምስት ኃሙስ ምሽቶች)

የስልጠናው ሰዓት፡- ለአምስቱም ኃሙሶች ከምሽቱ 3፡00 እስከ 5፡00 (በኢትዮጲያ አቆጣጠር)

የምዝገባ መረጃ፡- መረጃውን ለመቀበል ከዚህ በታች ባለው የ telegram link inbox በማድረግ ፍላጎቶትን ሲገል መረጃው ይላክሎታል

@DrEyobmamo

እናመሰግናለን!
አምስቱ የማሕበራዊ ሚዲያ ሃሳብ (Comment) ሰጪነት መርሆች
አምስቱ የማሕበራዊ ሚዲያ ሃሳብ (Comment) ሰጪነት መርሆች

በማሕበራዊ ገጾች ያለንን ተሳትፎ የመልካም ተጽእኖ ምንጭ ማድረግ ከፈለግን እነዚህ አምስት ሕጎች ይጠቅሙናል፡፡

1. የምትሰጡት ሃሳብ (Comment) አሉታዊ ከሚሆን ይልቅ አዎንታዊ ቢሆን ይመረጣል፡፡

ምንም እንኳን አንዳንድ ጊዜ አሉታዊ-ተኮር የሆኑ ሃሳቦችን ለመሰንዘር የሚጋብዙን ሁኔታዎች ቢከሰቱም፣ እነሱን ሃሳቦቻችንንም እንኳን ልናመጣ የምንፈልገውን ለውጥ በማጉላት አዎንታዊ ቀለም መስጠት እንደምንችል እናስታውስ፡፡

2. በምትሰጡት ሃሳብ (Comment) ሰዎችን መንቀፍ ላይ ከማተኮር ይልቅ ሰዎችን መደገፍ ላይ ማተኮር ይመረጣል፡፡

ምንም እንኳን አንዳንድ ጊዜ ስህተት አራማጅን ሰው መንቀፍ አስፈላጊ የሚሆንበት ጊዜ ቢኖርም፣ አብዛኛው ዝንባሌያችንና ልምምዳችን ግን የሚደገፉትን ከመደገፍ ይልቅ የሚነቀፉትን መንቀፍ ላይ የሚያተኩር እንዳይሆን መመልከት አስፈላጊ ነው፡፡

3. በምትሰጡት ሃሳብ (Comment) አማካኝነት አንድን ሰው ለማድነቅ ብላችሁ ሌሎችን አለማንቋሸሽ ይመረጣል፡፡

ምንም እንኳን አንዳንድ ጊዜ ሰዎችን ስናደንቅ ሊደነቁ የማገባቸውን የሌሎች ሰዎች ሁኔታ ማጋለጣችን ባይቀርም፣ ቀጥተኛ በሆነ መልኩ ሰዎችን ማንቋሸሽ የእኛን የተቀባይነት ደረጃና የመልእክት ጥንካሬ ስለሚያወርደው በጥንቃቄ ማድረግ መልካም ነው፡፡

4. በምትሰጡት ሃሳብ (Comment) አማካኝነት የምትሞግቱት ነገር ካለ ከሰዎቹ ጋር ከመጋጨት ይልቅ ሃሳባችሁን ከሃሳባቸው ጋር በማጋጭ የበረታው ሃሳብ እንዲያሸነፍ መፍቀድ ይመረጣል፡፡

ምንም እንኳን አንዳንድ ጊዜ የሰዎችን ጤና-ቢስ ሃሳብ ለመሞገት የሰዎቹን ማንነት መጥቀስ የግድ ቢሆንም፣ ዋናው ትኩረታችን ግን የሰዎቹን ስም፣ ህልውና እና ማንነት ማንቋሸሽ ሳይሆን የተዛባ ሃሳባቸውን ማዳከም እንደሆነ አንዘንጋ፡፡

5. በምትሰጡት ሃሳብ (Comment) ላይ እርግጠኝነት ከሌላችሁ ሃሳብ ከመስጠት ይልቅ ዝም ማለት ይመረጣል፡፡

ምንም እንኳን አንዳንድ ጊዜ በአንዳንድ ነገሮች ላይ ቀለል ያሉ ሃሳቦችን መሰንዘር ችግር ባይኖረውም፣ የከረረ ስሜትንና አቋምን ለመግለጽ የሚጋብዝ ሁኔታ ሲገጥመን ግን በነገሩና በእውነታው ላይ እርግጠኛነትን መያዛችንን አንዘንጋ፡፡

https://hottg.com/Dreyob

https://m.youtube.com/user/naeleyob623

https://www.facebook.com/Dr-Eyob-Mamo-1050816404958639/
የትም የማይሄደው መርከብ
በአላማ የመኖር ቁልፍ
የትም የማይሄደው መርከብ
በአላማ የመኖር ቁልፍ

(“25 የስኬት ቁልፎች” ከተሰኘው የዶ/ር ኢዮብ ማሞ መጽሐፍ የተወሰደ)

በአንድ ከተማ ውስጥ በየምሽቱ ሰዎችን እየጫነ ለሰዓታት በባህሩ ላይ ወዲህና ወዲያ በመሄድ ካሳለፈ በኋላ በመጨረሻ ሰዎቹን የነበሩበት ስፍራ መልሶ የሚያራግፋቸው መርከብ እንዳለ ይነገራል፡፡

ይህ ግዙፍ መርከብ በውስጡ አለ የተባለ በማንኛውም ዘመናዊ ከተማ ውስጥ የሚገኙ ነገሮችን አካቷል፡፡ መዝናኛው፣ መዋኛው፣ መጫወቻው፣ የሚበላውና የሚጠጣው ሙሉ ነው! የዚህ መርከብ ስም፣ “የትም የማይሄደው መርከብ” በመባል ይታወቃል፡፡

ይህ መርከብ በየምሽቱ ሰዎችን በመጫን ወዲህና ወዲያ ይሄዳል፣ ነገር ግን የትም አይደርስም፡፡ በጉዞው ወቅት ተሳፋሪዎቹ ይጫወታሉ፣ ይበላሉ፣ ይጠጣሉ፣ ይደንሳሉ፣ ይተዋወቃሉ፣ ያወራሉ … በመጨረሻ ግን ራሳቸውን የተነሱበት ቦታ ላይ ያገኙታል፡፡ በእለቱ በተከናወነው ነገር “እጅግ ደስ ከተሰኙ” በኋላ ሌላ የደስታ ምንጭ ፍለጋ ወደየስፍራቸው ይሰማራሉ - ጉዞአቸው ግን የትም አልወሰዳቸውም!

“ታላላቅ አእምሮዎች ዓላማ አላቸው፣ ሌሎቹ ግን ምኞት ብቻ ይዘዋል” - Washington Irving

በዚህች ምድር ላይ ከ7 ቢልየን ሕዝብ በላይ ወዲህና ወዲያ ሲመላለስና ዓለም ሕይወት ባላቸው ፍጡራን መሞላቷን ማየት ደስ ያሰኛል፡፡ ሆኖም ይህንን ደስ የሚያሰኝ ነገር ጥቁር ነጥብ የሚጥልበት አንድ አሳዛኝ ነገር አለ፣ ቁጥራቸው ጥቂት ያልሆኑ ሰዎች የሚሄዱበትን አያውቁም፡፡

እነዚህ ሰዎች በቀን ውስጥ ብዙ እንቅስቃሴ ቢያስመዘግቡም፣ የእነዚህ እንቅስቃሴዎች ድምር ውጤቱ ዜሮ ወይም ባዶ ነው፡፡

የብዙ ቁጥሮች ድምር ዜሮ የሚሆነው እንዴት ነው? መልሱ ቀላል ነው፡፡ የብዙ ቁጥሮች ድምር ዜሮ የሚሆነው የተደመሩት ቁጥሮች በሙሉ ዜሮ ሲሆኑ ነው፡፡ የየእለት እንቅስቃሴአችን ዜሮ የሚሆንበት ብቸኛ ምክንያት ካለምንም ዘላቂ እይታ ስለምንተገብረው ነው፡፡

የእለቱ ተግዳሮት የሚያመጣብን ትግልና የጊዜው መልካም ገጠመኝ የሚሰጠን ጊዜአዊ ደስታ ልንገነባው ከሚገባን አጠቃላይ የሕይወት ዓላማ አይነ-ህሊናችንን ይጋርዱታል፡፡ ግንባታ-የለሽ ደስታ፣ ግንባታ-የለሽ ጨዋታ፣ ግንባታ-የለሽ ስራ፣ ግንባታ-የለሽ ወዳጅነት፣ ፍጻሜ የለሽ ሩጫ … ዝርዝሩ ብዙ ነው፡፡

አንድ ሰው ስኬታማነትን በብርቱ ከፈለገ፣ በሕይወቱ ያለው ዓላማ ጉዳይ ግድ ሊለው ይገባል፡፡

https://hottg.com/Dreyob

https://m.youtube.com/user/naeleyob623

https://www.facebook.com/Dr-Eyob-Mamo-1050816404958639/
ስልጠናው ልክ የነገ ሳምንት ይጀምራል !!!

ሳትዘናጉ ተመዝገቡ!

የምዝገባ መረጃውን ለመቀበል ከዚህ በታች ባለው የ telegram link inbox በማድረግ ፍላጎቶትን ሲገልጹ መረጃው ይላክሎታል

@DrEyobmamo
#Temer real estate

09-46-14-24-08

ፒያሳ ሊይሴ ገ/ማርያም ትምህርት ቤት አጠገብ 3ኛ ሳይታችን ሽያጭ ጀምረናል።

➢ ሙሉ ክፍያ ከ6.9 ሚሊዮን ብር ጀምሮ

➢ ከባለ 1 እስከ ባለ 3 መኝታ ቤቶች

➢ ከ63 ካሬ እስከ 146 ካሬ

👉ቅድመ ክፍያ 10% ብቻ

ከ 30% ጀምሮ ለሚከፍሉ ደንበኞቻችን 25% ቅናሽ ያገኛሉ።

በተጨማሪም የንግድ ሱቆች ፒያሳ አድዋ00 ፊት ለፊት ከ3.9ሚሊዮን ብር ጀምሮ

👉 በተለያዪ አካባቢዎች የመኖሪያ ቤቶች እና ሱቆች አሉን ።

1ኛ  ሳር ቤት አፍሪካ ህብረት ፊት ለፊት ሳይት

2ኛ  አያት ፈርስ ቤት ሳይት

3ኛ  ጋርመንት አፍሪካ CDC ፊት ለፊት ሳይት

4ኛ  አያት አደባባይ ፊት ለፊት ሳይት

5ኛ  አያት ሎማያድ ሳይት

6ኛ  ሱማሊ ትራ ሳይት ለሽያጭ አውጠናል

👉 ማሳሰቢያ ፤- ምንም አይነት የዋጋ ጭማሬ አናደርግም ።

ለበለጠ መረጃ

09-46-14-24-08
መኖር!

ያለፈውን ስህተታችሁን
እያሰባችሁ፣ “ምነው ባላደረኩት ኖሮ” እያላችሁ ከመጸጸት ይልቅ ትምህርታችሁን ወስዳችሁ መኖር!

ስለሁኔታዎቻችሁ ከመጨነቅ ይልቅ መለወጥ የምትችሉት ላይ እየሰራችሁ የማትችሉትን ግን በመቀበል መኖር!

ሰዎች እንዲያደርጉላችሁ እየጠበቃችሁ ሳይሆን ሲቀር ቅሬታ ውስጥ ከመግባት ይልቅ ለተደረገላችሁ እያመሰገናችሁ መኖር!

የሰላም ኑሮ ተመኘሁላቸሁ!

https://hottg.com/Dreyob

https://m.youtube.com/user/naeleyob623

https://www.facebook.com/Dr-Eyob-Mamo-1050816404958639/
ለብቸኛ ወላጆች (single parents) ቅናሽ!

ልጃችሁን ለብቻችሁ ሆናችሁ በማሳደግ ላይ ያላችሁ single parents ባቀረባችሁ ተደጋጋሚ ጥያቄ መሰረት ለተማሪዎች የተደረገው ቅናሽ ለእናንተም እንደተረገላችሁ እናሳስለን፡፡

የስልጠው ርእስ፡- “የገንዘብ አስተዳደር ክህሎት እና ዲሲፕሊን” (Money Management Skills and Discipline)

ስልጠናው የሚሰጠው፡- በዶ/ር ኢዮብ ማሞ

ስልጠናው የሚሰጥበት መንገድ፡- በonline (telegram live)

የስልጠናው ቀናት፡- ሰኔ 19, ሰኔ 26፣ ሐምሌ 3, ሐምሌ 10 እና ሐምሌ 17 (ለአምስት ኃሙስ ምሽቶች)

የስልጠናው ሰዓት፡- ለአምስቱም ኃሙሶች ከምሽቱ 3፡00 እስከ 5፡00 (በኢትዮጲያ አቆጣጠር)

የምዝገባ መረጃ፡- መረጃውን ለመቀበል ከዚህ በታች ባለው የ telegram link inbox በማድረግ ፍላጎቶትን ሲገል መረጃው ይላክሎታል

@DrEyobmamo
ለራሳችሁ የምትናገሩት ነገር አቅም!

“ሰዎች አንድን ነገር ሲናገሯችሁ ያንን ነገር የምትሰሙት አንድ ጊዜ ብቻ ነው፤ ለራሳችሁ አንድን ነገር ስትናገሩ ግን ያንን ነገር የምትሰሙት ሁለት ጊዜ ነው” (Unknown source)፡፡

በጉዳዩ ላይ በሚገባ እንድናስብበት የሚያስታውስ አባባል ነው፡፡

አንድን ነገር አንድ ሰው ሲናገረን ንግግሩ አንድ ጊዜ ወደ ጆሯችን ይገባል፡፡ አንድን ነገር ለራሳችን ስንናገር ግን በመጀመሪያ ያንን ሃሳብ ከአንደበታችን በማውጣት፣ ከዚያ ደግሞ ያንን በንግግር ያወጣነውን ነገር በመስማት ድርብ ተጽእኖን እናስተናግዳለን፡፡

ይህንን አባባል በአዎንታዊውም ሆነ በአሉታዊው ገጽታው ልንመለከተው እንችላለን፡፡

ለምሳሌ፣ “እኔ ምንም ነገር የማይሳካልኝ ሰው ነኝ” ብዬ በምናገርበት ጊዜ ማንነቴ ይህንን ሃሳብ በመናገርም ሆነ በማድመጥ ተሳታፊ በመሆኑ ምክንያት ያለመቻል ስሜት በእጥፍ ይጫነኛል፡፡

ከዚህ በተቃራኒ፣ “እኔ የሚሳካልኝ ሰው ነኝ! ያሰብኩትን ማድረግና ማሳካት እችላለሁ!” በምልበት ግዜ የዚህም መልካም ሃሳብ ተናጋሪውም፣ ሰሚውም በመሆነ ድርብ የመቻል ስሜትን አስተናግዳለሁ፡፡

ሰዎች፣ “አትችሉም” ሲሏችሁ፣ እናንተ ደግሞ በተቃራኒው፣ “እችላለሁ” ስትሉ የሚያሸንፈው የእናንተ ነው፡፡ ምክንያቱም የእናንተ ንግግር ድርብ አቅም ስላለው ማለት ነው፡፡

ሰዎች፣ “ትችላላችሁ” ቢሏችሁም፣ እናንተ ግን “አልችልም” ካላችሁ የእናንተ ሃሳብ በራሳችሁ ሁለቴ ስለሚደገም እንደማትችሉ ነው የምትቀበሉት፡፡
ለራሳችሁ የምትናገሩትን ነገር በጥንቃቄ አድርጉት!

https://hottg.com/Dreyob

https://m.youtube.com/user/naeleyob623

https://www.facebook.com/Dr-Eyob-Mamo-1050816404958639/
አንድ ሰው ለተወሰኑ ሳምንታት ከእኔ ጋር የግል coaching ከወሰደ በኋላ እንዲህ ሲል ጻፈልኝ፡-

“ሰዎችን ለማስደሰት መታገልና እንዲወዱኝ መጋጋጥ አቁሜያለሁ!!!”

አስገራሚ ለውጥ!

መሆን ያለበት የአኗኗር ዘይቤ!
ሰባት ቀናት ብቻ ቀሩት!

የስልጠው ርእስ፡- “የገንዘብ አስተዳደር ክህሎት እና ዲሲፕሊን” (Money Management Skills and Discipline)

ስልጠናው የሚሰጠው፡- በዶ/ር ኢዮብ ማሞ

ስልጠናው የሚሰጥበት መንገድ፡- በonline (telegram live)

የስልጠናው ቀናት፡- ሰኔ 19, ሰኔ 26፣ ሐምሌ 3, ሐምሌ 10 እና ሐምሌ 17 (ለአምስት ኃሙስ ምሽቶች)

የስልጠናው ሰዓት፡- ለአምስቱም ኃሙሶች ከምሽቱ 3፡00 እስከ 5፡00 (በኢትዮጲያ አቆጣጠር)

የምዝገባ መረጃ፡- መረጃውን ለመቀበል ከዚህ በታች ባለው የ telegram link inbox በማድረግ ፍላጎቶትን ሲገል መረጃው ይላክሎታል

@DrEyobmamo

እናመሰግናለን!
#Temer real estate

09-46-14-24-08

ፒያሳ ሊይሴ ገ/ማርያም ትምህርት ቤት አጠገብ 3ኛ ሳይታችን ሽያጭ ጀምረናል።

➢ ሙሉ ክፍያ ከ6.9 ሚሊዮን ብር ጀምሮ

➢ ከባለ 1 እስከ ባለ 3 መኝታ ቤቶች

➢ ከ63 ካሬ እስከ 146 ካሬ

👉ቅድመ ክፍያ 10% ብቻ

ከ 30% ጀምሮ ለሚከፍሉ ደንበኞቻችን 25% ቅናሽ ያገኛሉ።

በተጨማሪም የንግድ ሱቆች ፒያሳ አድዋ00 ፊት ለፊት ከ3.9ሚሊዮን ብር ጀምሮ

👉 በተለያዪ አካባቢዎች የመኖሪያ ቤቶች እና ሱቆች አሉን ።

1ኛ  ሳር ቤት አፍሪካ ህብረት ፊት ለፊት ሳይት

2ኛ  አያት ፈርስ ቤት ሳይት

3ኛ  ጋርመንት አፍሪካ CDC ፊት ለፊት ሳይት

4ኛ  አያት አደባባይ ፊት ለፊት ሳይት

5ኛ  አያት ሎማያድ ሳይት

6ኛ  ሱማሊ ትራ ሳይት ለሽያጭ አውጠናል

👉 ማሳሰቢያ ፤- ምንም አይነት የዋጋ ጭማሬ አናደርግም ።

ለበለጠ መረጃ

09-46-14-24-08
ሌላም አለ እኮ!

በአንድ ቦታ ብቻ አትወሰኑ፣ የተለያዩ ቦታዎችን ተመልከቱ፣ ጎብኙ፡፡ ይህንን ስታደርጉ ልምምዳችሁና ምልከታችሁ እየሰፋ ይሄዳል፡፡ ሆኖም፣ የሚኬድበትንና የማይኬድበትን በጥቃቄ መምረጣችሁን አትዘንጉ፡፡

በአንድ የማሕበራዊ ግንኙነት አጥር ውስጥ አትገደቡ፣ የተለያዩ ሰዎችን ተዋወቁ፡፡ ይህንን ስታደርጉ የተለያየ ማሕበራ ንክኪ ያላቸውን ሰዎች በማወቅ መረባችሁ እየሰፋና እያደገ ይሄዳል፡፡ ሆኖም፣ ማንን በምን አይነት ክፍትነትና ተጋላጭነት እንደምትቀርቡ ጥንቃቄ ውሰዱ፡፡

በአንድ የስራና የገቢ ምንጭ ሁኔታ አትቆለፉ፣ የተለያዩ የስራ እድሎችን ተመልከቱ፡፡ ይህንን ስታደርጉ አዳዲስ የስራ እና የገቢ ምንጭ እድሎችን ታገኛላችሁ፡፡ ሆኖም፣ ይህንንም ያንንም በመሞከር ሰበብ ትኩረት የሌለው ሩጫ ውስጥ እንዳትገቡ አስቡበት፡፡

https://hottg.com/Dreyob

https://m.youtube.com/user/naeleyob623

https://www.facebook.com/Dr-Eyob-Mamo-1050816404958639/
ሰባት ቀናት ብቻ ቀሩት!

የስልጠው ርእስ፡- “የገንዘብ አስተዳደር ክህሎት እና ዲሲፕሊን” (Money Management Skills and Discipline)

ስልጠናው የሚሰጠው፡- በዶ/ር ኢዮብ ማሞ

ስልጠናው የሚሰጥበት መንገድ፡- በonline (telegram live)

የስልጠናው ቀናት፡- ሰኔ 19, ሰኔ 26፣ ሐምሌ 3, ሐምሌ 10 እና ሐምሌ 17 (ለአምስት ኃሙስ ምሽቶች)

የስልጠናው ሰዓት፡- ለአምስቱም ኃሙሶች ከምሽቱ 3፡00 እስከ 5፡00 (በኢትዮጲያ አቆጣጠር)

የምዝገባ መረጃ፡- መረጃውን ለመቀበል ከዚህ በታች ባለው የ telegram link inbox በማድረግ ፍላጎቶትን ሲገል መረጃው ይላክሎታል

@DrEyobmamo

እናመሰግናለን!
በልክና በሚዛናዊነት ይሁን!

• ካለልክ ማሰብ (overthinking) - የመላ-ምት ውሳኔዎች ውስጥ ይጨምረናል፡፡

• ካለልክ ማመን (over trust) - ለጉዳት ያጋልጠናል፡፡

• ካለልክ ራስን መግለጥ (overshare) - ለጥቅመኞች አሳልፎ ይሰጠናል፡፡

• ካለልክ መጠንቀቅ (over caution) - ኋላ ቀርነት ያስከትልብናል፡፡

• ካለልክ መተማመን (overconfidence) - ለጭፍን እርምጃ ያነሳሳናል፡፡

አልፎ አልፎ በእነዚህ አይነት ልምምዶች ውስጥ ማለፍ የግድ የሚሆንበት ጊዜ የመኖሩ እውነታ እንደተጠበቀ ሆኖ፣ ልምምዶቹ እየጎዱን እንደሆነ ካሰብን ልኩን ለማሰያዝ እንስራ፡፡

https://hottg.com/Dreyob

https://m.youtube.com/user/naeleyob623

https://www.facebook.com/Dr-Eyob-Mamo-1050816404958639/
“የእባብ ማሳደድ” ውጤት (The snake chasing effect)

እንዲህ የሚል አባባል አለ፡-

አንድ ሰው በሚያሳዝን ሁኔታ በመርዛማ እባብ ቢነደፍ ያለው አማራጭ ሁለት ነው፡፡ አንደኛው፣ የነደፈውን እባብ ተከታተሎ በመግደል ለመበቀል መሞከር ሲሆን፣ ሁለተኛው መርጫው ደግሞ በመጀመሪያ ለቁስሉ ትኩረት በመስጠት መርዙ እንዳይጎዳው ለራሱ አስፈላጊውን ክትትል ማድረግ ነው፡፡

እኛን የነደፈው እባብ ሌሎችን እንዳይነድፍ ከማድረግ አንጻርና ከመሳሰሉት አመለካከቶች (logic / አመክንዮ) አንጻር ብዙ የመወያያ ሃሳቦች ማምጣት የመቻላችን እውነታ እንደተጠበቀ ሆኖ፣ ሊቀድም የሚገባው ግን ምን እንደሆነ ግልጽ ነው፡፡

በምንም ዓይነት ሁኔታም ሆነ በየትኛውም ሰው ስትጎዱ ለበቀልና አጸፋ ለመመለስ ከመንቀሳቀሳችሁ በፊት ለራሳችሁ የመጠንቀቃችሁን ጉዳይ ቅድሚያ ስጡ፡፡

ይህንን ስታደርጉ . . .

1. ለሆነባችሁ ነገር ሁሉ አጸፋ ለመመለስ ስትሯሯጡ ራሳችሁን ከማከም ችላ በማለታችሁ ምክንያት ከሚመጣ ጉዳት ትጠበቃላችሁ፡፡

2. ለሆነባችሁ ነገር ሁሉ አጸፋ ለመመለስ ስትታገሉ ከዋናው ዓላማችሁ መስመር ትወጣላችሁ፡፡

3. ይህ አይነቱ ምላሽ ሰጪነት መነሻው ስሜታዊነት በመሆኑ፣ ከዚያኛው ወገን ሌላ ስሜታዊ ምላሽን ሊወልድ ስለሚችልና የዑደቱ መጨረሻ ስለማይታወቅ ላልተጠበቁ ውጤቶች ራሳችሁን ታጋልጣላችሁ፡፡

በመጀመሪያ ራሳችሁን ጠብቁ፡፡ ሲቀጥል፣ በቅድሚያ ራሳችሁን አክሙ፡፡

መልካም ቀን!

https://hottg.com/Dreyob

https://m.youtube.com/user/naeleyob623

https://www.facebook.com/Dr-Eyob-Mamo-1050816404958639/
ስድስት ቀናት ብቻ ቀሩት!

የስልጠው ርእስ፡- “የገንዘብ አስተዳደር ክህሎት እና ዲሲፕሊን” (Money Management Skills and Discipline)

ስልጠናው የሚሰጠው፡- በዶ/ር ኢዮብ ማሞ

ስልጠናው የሚሰጥበት መንገድ፡- በonline (telegram live)

የስልጠናው ቀናት፡- ሰኔ 19, ሰኔ 26፣ ሐምሌ 3, ሐምሌ 10 እና ሐምሌ 17 (ለአምስት ኃሙስ ምሽቶች)

የስልጠናው ሰዓት፡- ለአምስቱም ኃሙሶች ከምሽቱ 3፡00 እስከ 5፡00 (በኢትዮጲያ አቆጣጠር)

የምዝገባ መረጃ፡- መረጃውን ለመቀበል ከዚህ በታች ባለው የ telegram link inbox በማድረግ ፍላጎቶትን ሲገል መረጃው ይላክሎታል

@DrEyobmamo

እናመሰግናለን!
#Temer real estate

09-46-14-24-08

ፒያሳ ሊይሴ ገ/ማርያም ትምህርት ቤት አጠገብ 3ኛ ሳይታችን ሽያጭ ጀምረናል።

➢ ሙሉ ክፍያ ከ6.9 ሚሊዮን ብር ጀምሮ

➢ ከባለ 1 እስከ ባለ 3 መኝታ ቤቶች

➢ ከ63 ካሬ እስከ 146 ካሬ

👉ቅድመ ክፍያ 10% ብቻ

ከ 30% ጀምሮ ለሚከፍሉ ደንበኞቻችን 25% ቅናሽ ያገኛሉ።

በተጨማሪም የንግድ ሱቆች ፒያሳ አድዋ00 ፊት ለፊት ከ3.9ሚሊዮን ብር ጀምሮ

👉 በተለያዪ አካባቢዎች የመኖሪያ ቤቶች እና ሱቆች አሉን ።

1ኛ  ሳር ቤት አፍሪካ ህብረት ፊት ለፊት ሳይት

2ኛ  አያት ፈርስ ቤት ሳይት

3ኛ  ጋርመንት አፍሪካ CDC ፊት ለፊት ሳይት

4ኛ  አያት አደባባይ ፊት ለፊት ሳይት

5ኛ  አያት ሎማያድ ሳይት

6ኛ  ሱማሊ ትራ ሳይት ለሽያጭ አውጠናል

👉 ማሳሰቢያ ፤- ምንም አይነት የዋጋ ጭማሬ አናደርግም ።

ለበለጠ መረጃ

09-46-14-24-08
HTML Embed Code:
2025/06/27 17:37:57
Back to Top