Channel: Dn Abel Kassahun Mekuria
በዛሬው ቀን መታሰቢያ ከሚደረግላቸው ቅዱሳን መካከል አንዱ ጻድቁ ኢዮብ ሲሆን፣ ይኸውም ዕረፍቱ ነው። በረከቱ በሁላችን ላይ ይደርብን!!!
https://youtu.be/RtadI2ocC5E?si=lWiVVmX3eUXQHs0c
https://youtu.be/RtadI2ocC5E?si=lWiVVmX3eUXQHs0c
YouTube
መምህር አቤል ካሳሁን ኢዮብ እነደታገሠ ሰምታችኋል ያዕ 5 ፥ 11
✝️✝️✝️የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ በጸሎት ያግዙን✝️✝️✝️አዲሱን የማኅበራችንን የዩቱዩብ ቻናል +++SUBSCRIBE +++ እያደረጋችሁ ትምህርቶችን እና መዝሙሮችን እንዲደርሶት እና ለሌሎች እንዲደርሳቸው ሼር በማድረግም ይተባበሩን::
ከዚህ በፊት የተለቀቁ ትምህርቶችንና ዝማሬዎችን ለማግኘት ከስር የሚገኘውን ሊንክ ይጠቀሙ
https://www.youtube.com/channel/UCol_BHX6I…
ከዚህ በፊት የተለቀቁ ትምህርቶችንና ዝማሬዎችን ለማግኘት ከስር የሚገኘውን ሊንክ ይጠቀሙ
https://www.youtube.com/channel/UCol_BHX6I…
"ወደ ገሊላ ይቀድማችኋል" ማቴ 28፥7
ጌታችን ሞትን ድል አድርጎ ከተነሣ በኋላ ለደቀ መዛሙርቱ ብዙ እና ጥቂት ሆነው ሳለ በተለያየ ጊዜ ራሱን ገልጦ አሳይቷቸዋል። አሁን ደግሞ አስቀድሞ በሴቶች በኩል "ወደ ገሊላ ይቀድማችኋል" ብሎ ያስነገረውን ትንቢት ሊፈጽም፣ ዓሣ ለማጥመድ ወደ ገሊላ ባሕር ለወረዱ ለጴጥሮስና ለስድስቱ ወንድሞቹ የተገለጠበትን ሦስተኛ ታሪክ ዮሐንስ ይጽፍልናል።(ዮሐ 21፥1)
ቅዱስ ጴጥሮስ "ሰላም ለእናንተ ይሁን" የሚለውን የትንሣኤውን ጌታ ድምጽ ከሰማ ፣ የተጠራጠረው ቶማስ እጁን በጎኖቹ አግብቶ "ጌታዬ አምላኬ" ብሎ ሲያምን ከተመለከተ በኋላ "ዓሣ ላጠምድ እሄዳለሁ" ብሎ ሲናገር እናገኘዋለን።(ዮሐ 21፥3) ክርስቶስ ተላልፎ በተሰጠበት በሐሙስ ምሽት ከእሳት ዳር ተቀምጦ ያደረገውን ሊረሳውና ራሱን ይቅር ሊል ስላልቻለ፣ ጌታው ቀድሞ የሰጠውን የወንጌል መረብ ተወና የዓሣውን መረብ ጨብጦ ወደ ገሊላ ባሕር ሮጠ።(ማቴ 4፥19) በኃጢአት ምክንያት የተሰማው ኃፍረትና መሸማቀቅ ሐዋርያነቱን ትቶ በድሮ ማንነቱ ውስጥ ራሱን እንዲደብቅ አደረገው። የካደን ማን ለምስክርነት ይፈልገዋል በሚል ዓይነት ስሜት ለወንድሞቹ "ዓሣ ላጠምድ እሄዳለሁ" አላቸው።
ደስ የሚለው ነገር ግን ይህን አስቀድሞ የሚያውቅ ይቅር ባይ አምላኩ ጴጥሮስን "በገሊላ ቀድሞት ነበር"። በበደሉ ተሸማቆ የተወውን ሐዋርያነት ሥልጣን በፍቅሩ መማለጃነት መልሶ ሊሰጠው፣ አይገባኝም ብሎ ያስቀመጠውን የወንጌል መረብ ዳግመኛ ሊያሲዘው በገሊላ ባሕር ዳር ቀደመው። እኛም አንድ ኃጢአት ይኖረናል። መርሳት ያልቻልነው፣ ንስሐ እንኳን ብንገባበት ራሳችንን ይቅር ለማለት የተቸገርንበት፣ "ከዚህ በኋላማ..." እያሰኘ የድሮ መረብ አስይዞ ወደ ገሊላ የሚመልስ አንድ በደል ይኖረናል። ነገር ግን ጌታ ለቅዱስ ጴጥሮስ እንዳደረገው ለእኛም እንዲሁ ያደርጋል። ከባሕሩ ዳር ይጠብቀናል፣ "ትወደኛለህ" ብሎ ይጠይቀናል፣ ከዚያ በማይለወጥ ፍቅሩ ወልውሎ ሰንግሎ አፍረን ወደ ሸሸነው መንፈሳዊነት ይመልሰናል።
+++ ጌታችን በገሊላ ይቀድመናል! +++
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
[email protected]
ግንቦት 6/ 2015 ዓ.ም.
አዲስ አበባ
ጌታችን ሞትን ድል አድርጎ ከተነሣ በኋላ ለደቀ መዛሙርቱ ብዙ እና ጥቂት ሆነው ሳለ በተለያየ ጊዜ ራሱን ገልጦ አሳይቷቸዋል። አሁን ደግሞ አስቀድሞ በሴቶች በኩል "ወደ ገሊላ ይቀድማችኋል" ብሎ ያስነገረውን ትንቢት ሊፈጽም፣ ዓሣ ለማጥመድ ወደ ገሊላ ባሕር ለወረዱ ለጴጥሮስና ለስድስቱ ወንድሞቹ የተገለጠበትን ሦስተኛ ታሪክ ዮሐንስ ይጽፍልናል።(ዮሐ 21፥1)
ቅዱስ ጴጥሮስ "ሰላም ለእናንተ ይሁን" የሚለውን የትንሣኤውን ጌታ ድምጽ ከሰማ ፣ የተጠራጠረው ቶማስ እጁን በጎኖቹ አግብቶ "ጌታዬ አምላኬ" ብሎ ሲያምን ከተመለከተ በኋላ "ዓሣ ላጠምድ እሄዳለሁ" ብሎ ሲናገር እናገኘዋለን።(ዮሐ 21፥3) ክርስቶስ ተላልፎ በተሰጠበት በሐሙስ ምሽት ከእሳት ዳር ተቀምጦ ያደረገውን ሊረሳውና ራሱን ይቅር ሊል ስላልቻለ፣ ጌታው ቀድሞ የሰጠውን የወንጌል መረብ ተወና የዓሣውን መረብ ጨብጦ ወደ ገሊላ ባሕር ሮጠ።(ማቴ 4፥19) በኃጢአት ምክንያት የተሰማው ኃፍረትና መሸማቀቅ ሐዋርያነቱን ትቶ በድሮ ማንነቱ ውስጥ ራሱን እንዲደብቅ አደረገው። የካደን ማን ለምስክርነት ይፈልገዋል በሚል ዓይነት ስሜት ለወንድሞቹ "ዓሣ ላጠምድ እሄዳለሁ" አላቸው።
ደስ የሚለው ነገር ግን ይህን አስቀድሞ የሚያውቅ ይቅር ባይ አምላኩ ጴጥሮስን "በገሊላ ቀድሞት ነበር"። በበደሉ ተሸማቆ የተወውን ሐዋርያነት ሥልጣን በፍቅሩ መማለጃነት መልሶ ሊሰጠው፣ አይገባኝም ብሎ ያስቀመጠውን የወንጌል መረብ ዳግመኛ ሊያሲዘው በገሊላ ባሕር ዳር ቀደመው። እኛም አንድ ኃጢአት ይኖረናል። መርሳት ያልቻልነው፣ ንስሐ እንኳን ብንገባበት ራሳችንን ይቅር ለማለት የተቸገርንበት፣ "ከዚህ በኋላማ..." እያሰኘ የድሮ መረብ አስይዞ ወደ ገሊላ የሚመልስ አንድ በደል ይኖረናል። ነገር ግን ጌታ ለቅዱስ ጴጥሮስ እንዳደረገው ለእኛም እንዲሁ ያደርጋል። ከባሕሩ ዳር ይጠብቀናል፣ "ትወደኛለህ" ብሎ ይጠይቀናል፣ ከዚያ በማይለወጥ ፍቅሩ ወልውሎ ሰንግሎ አፍረን ወደ ሸሸነው መንፈሳዊነት ይመልሰናል።
+++ ጌታችን በገሊላ ይቀድመናል! +++
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
[email protected]
ግንቦት 6/ 2015 ዓ.ም.
አዲስ አበባ
+++ ምክር እና ቡጢ... +++
አንዳንዴ ሰው ተቸግሮ ወደ እኛ መጥቶ ሲያወያየን ከግለሰቡ በላይ የምንሰጠውን ምክር የምንወድ ሰዎች አለን። ያ ሰው ምን ሁኔታ ላይ ነው? ምን ይሰማዋል? ብሎ ለመረዳት ከመጣር ይልቅ ልንነግረው ባሰብነው ምክር ቀድሞ ደስ መሰኘት። አውርቶ እስኪጨርስ ትዕግሥት ማጣት። እንዴት ሰምቼ ላሳርፈው ከማለት ይልቅ ከመቼው ነግሬው ላስደንቀው (ይደነቅብኝ) የሚል ጉጉት።
መፍትሔ ብለን የምንነግረው ደግሞ ሸክም ያደከመው ሰውነቱን ጨርሶ ያላገናዘበ የሚሆንበት አጋጣሚ በጣም ብዙ ነው።
አንድ በchildhood psychology የተመረቀ አንድ ወጣት ሰው ነው አሉ። ወላጆች በተሰበሰቡበት የመጀመሪያውን ሥልጠና ሲሰጥ ለጥናቱ የመረጠው ርእስ "ዐሥርቱ ትእዛዛት ለወላጆች"/"Ten commandments for parent" በሚል ነበር። ታዲያ እርሱም እንደ ሌሎች የትዳር ወጉ ደርሶት ልክ አንድ ልጅ ወልዶ ማሳደግ እንደ ጀመረ ያ ይሰጠው የነበረውን የሥልጠና ርእስ መቀየር እንዳለበት ተሰማውና "ዐሥር ማሳሰቢያ ለወላጆች" አለው። ቀጥሎ ሁለተኛ ልጅ ወልዶ ሲያሳድግ አሁንም የቀየረው የሥልጠና ርእስ ድጋሚ ማሻሻያ እንደሚያስፈልገው ተረዳ። ስለዚህ በስተመጨረሻ ርእሱን "ዐሥር ጥቆማ ለወላጆች" አለው ይባላል። አንዳንዴ ለሰዎች የምንሰጠው ምክር ምን ያህል ከባድ እንደ ሆነ ሕይወት እስክታስተምረን ድረስ የምንጨክን እንኖራለን።
አንዳንድ ጊዜ ሰው ጨንቆት ወደ አንተ ሲመጣ ግዴታ የሆነ ወርቃማ አባባል እንድትነግረው ወይም በአነቃቂ ቃላት እንድታግለው ላይሆን ይችላል። ያን ሰው በዝምታ መስማት እና የተዘበራረቀው ሐሳቡን ጊዜ ወስዶ ለአንተ በመናገር እንዲያጠራ ማድረግም ትልቅ እርዳታ ነው።
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
[email protected]
አንዳንዴ ሰው ተቸግሮ ወደ እኛ መጥቶ ሲያወያየን ከግለሰቡ በላይ የምንሰጠውን ምክር የምንወድ ሰዎች አለን። ያ ሰው ምን ሁኔታ ላይ ነው? ምን ይሰማዋል? ብሎ ለመረዳት ከመጣር ይልቅ ልንነግረው ባሰብነው ምክር ቀድሞ ደስ መሰኘት። አውርቶ እስኪጨርስ ትዕግሥት ማጣት። እንዴት ሰምቼ ላሳርፈው ከማለት ይልቅ ከመቼው ነግሬው ላስደንቀው (ይደነቅብኝ) የሚል ጉጉት።
መፍትሔ ብለን የምንነግረው ደግሞ ሸክም ያደከመው ሰውነቱን ጨርሶ ያላገናዘበ የሚሆንበት አጋጣሚ በጣም ብዙ ነው።
አንድ በchildhood psychology የተመረቀ አንድ ወጣት ሰው ነው አሉ። ወላጆች በተሰበሰቡበት የመጀመሪያውን ሥልጠና ሲሰጥ ለጥናቱ የመረጠው ርእስ "ዐሥርቱ ትእዛዛት ለወላጆች"/"Ten commandments for parent" በሚል ነበር። ታዲያ እርሱም እንደ ሌሎች የትዳር ወጉ ደርሶት ልክ አንድ ልጅ ወልዶ ማሳደግ እንደ ጀመረ ያ ይሰጠው የነበረውን የሥልጠና ርእስ መቀየር እንዳለበት ተሰማውና "ዐሥር ማሳሰቢያ ለወላጆች" አለው። ቀጥሎ ሁለተኛ ልጅ ወልዶ ሲያሳድግ አሁንም የቀየረው የሥልጠና ርእስ ድጋሚ ማሻሻያ እንደሚያስፈልገው ተረዳ። ስለዚህ በስተመጨረሻ ርእሱን "ዐሥር ጥቆማ ለወላጆች" አለው ይባላል። አንዳንዴ ለሰዎች የምንሰጠው ምክር ምን ያህል ከባድ እንደ ሆነ ሕይወት እስክታስተምረን ድረስ የምንጨክን እንኖራለን።
አንዳንድ ጊዜ ሰው ጨንቆት ወደ አንተ ሲመጣ ግዴታ የሆነ ወርቃማ አባባል እንድትነግረው ወይም በአነቃቂ ቃላት እንድታግለው ላይሆን ይችላል። ያን ሰው በዝምታ መስማት እና የተዘበራረቀው ሐሳቡን ጊዜ ወስዶ ለአንተ በመናገር እንዲያጠራ ማድረግም ትልቅ እርዳታ ነው።
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
[email protected]
ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን
በአማን ተንሥአ!
እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው አደረሳችሁ፤
ክፍል ዘጠኝ ትምህርታችንን ዛሬ ልክ በኢትዮጵያ አቆጣጠር ከምሽቱ 4:00 ሰዓት ላይ በዚህ https://hottg.com/Dnabel የቴሌግራም ቻናል በlive stream ትምህርቱ ይሰጣል።
እንደ አማራጭ ይህን ከታች የተቀመጠውን ሊንክ በመጠቀም ደግሞ በzoom ልትቀላቀሉን ትችላላችሁ።
https://us05web.zoom.us/j/84709079682?pwd=obn6Rc8YrJjSTaAAeRwKmNbMC2kY8n.1
በአማን ተንሥአ!
እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው አደረሳችሁ፤
ክፍል ዘጠኝ ትምህርታችንን ዛሬ ልክ በኢትዮጵያ አቆጣጠር ከምሽቱ 4:00 ሰዓት ላይ በዚህ https://hottg.com/Dnabel የቴሌግራም ቻናል በlive stream ትምህርቱ ይሰጣል።
እንደ አማራጭ ይህን ከታች የተቀመጠውን ሊንክ በመጠቀም ደግሞ በzoom ልትቀላቀሉን ትችላላችሁ።
https://us05web.zoom.us/j/84709079682?pwd=obn6Rc8YrJjSTaAAeRwKmNbMC2kY8n.1
ከመላእክት ጋር አብረን የምንዘምርበትን የዜማ ሥርዓት ለሠራልን፣ ከእግዚአብሔር ዘንድ የወረደውን የምስጋና ማዕድ ለእኛ እንደሚገባ አድርጎ ላደረሰ ታማኝ መጋቢ፣ ለዘማሪው፣ ለተርጓሚው፣ ለባለ ቅኔው ለቅዱስ ያሬድ ማኅሌታይ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሰን።
-የአንደበት አመጽ ጸጋን አስገፍፎ እንዴት የመልአክነትን ክብር እንደሚያሳጣ በሳጥናኤል አየን!
-የአንደበት ፍሬ እንዴት እንደሚያከብር እና ምድራዊ መልአክ እንደሚያደርግ ደግሞ በቅዱስ ያሬድ ማኅሌታይ ተመለከትን!
አቤቱ የያሬድን ልሳን ስጠኝ!
ዲያቆን አቤል ካሣሁን
[email protected]
https://hottg.com/Dnabel
-የአንደበት አመጽ ጸጋን አስገፍፎ እንዴት የመልአክነትን ክብር እንደሚያሳጣ በሳጥናኤል አየን!
-የአንደበት ፍሬ እንዴት እንደሚያከብር እና ምድራዊ መልአክ እንደሚያደርግ ደግሞ በቅዱስ ያሬድ ማኅሌታይ ተመለከትን!
አቤቱ የያሬድን ልሳን ስጠኝ!
ዲያቆን አቤል ካሣሁን
[email protected]
https://hottg.com/Dnabel
ሰላም ክቡራን፣
የዕብራውያን መልእክት ሐተታ ትምህርታችንን ከተወሰኑ የዕረፍት ጊዜያት በኋላ እንደ አዲስ ከትምህርቱ ሂደት ማሻሻያ ጋር የምንጀምር ይሆናል። እስከዚያው ግን እስከ ዛሬ በነበረን ቆይታ ያላችሁን አስተያየት በcomment መስጫ ቦታው ላይ ማስቀመጥ ትችላላችሁ።
ቸር ያገናኘን!
የዕብራውያን መልእክት ሐተታ ትምህርታችንን ከተወሰኑ የዕረፍት ጊዜያት በኋላ እንደ አዲስ ከትምህርቱ ሂደት ማሻሻያ ጋር የምንጀምር ይሆናል። እስከዚያው ግን እስከ ዛሬ በነበረን ቆይታ ያላችሁን አስተያየት በcomment መስጫ ቦታው ላይ ማስቀመጥ ትችላላችሁ።
ቸር ያገናኘን!
"በክርስቶስ ኢየሱስም በሰማያዊ ስፍራ ከእርሱ ጋር አስቀመጠን" ኤፌ 2፥6-7
እንኳን ለበዓለ ዕርገት በሰላም አደረሰን!
እንኳን ለበዓለ ዕርገት በሰላም አደረሰን!
+++ "እመቤታችን ከጌታ ዕርገት በኋላ" +++
መድኃኔዓለም ክርስቶስ በቅዱስ መስቀሉ ላይ ባፈሰሰው ክቡር ደሙ የመሠረታትን ቤተ ክርስቲያን ለሐዋርያቱ አደራ ሰጥቷል፡፡ በመጀመሪያው ምዕት ዓመት በነበረው የቤተ ክርስቲያን ሕይወት ውስጥ የጌታ እናቱ እመቤታችን የነበራት ድርሻ ትልቅ ነበር፡፡ ከክርስቶስ ዕርገት በኋላ እመቤታችን በሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ ቤት ሳለች፣ የሐዲስ ኪዳኗ ቤተ ክርስቲያን ራስ እና ፈጻሚ የሆነው ክርስቶስ የተገኘባትን እርሷን ለማየት ከሁሉም የዓለም ክፍላት የሚመጡ ሰዎች ብዙ ነበሩ፡፡ ድንግልም ወደ እርሷ የመጡትን ሁሉ እየባረከች፣ ያዘኑትንም እያጽናናች፣ በንስሓ ሕይወት እንዲኖሩ በመምከር ተስፋና ደስታን እየሞላች ትሸኛቸው ነበር፡፡ በርግጥም እግዚአብሔር ሰው ሆኖ በምድር ላይ ለመገለጡ፣ እንደ ሕፃናት ጥቂት በጥቂት ለማደጉና በመጨረሻም ለፈጸመው የቤዛነት ሥራው ሁሉ እናቱና አገልጋዩ ከምትሆን ከእመቤታችን የበለጠ ምስክር ከየት ሊመጣ? እርሷን ለማየት ባይጓጉ ነበር የሚደንቀን፡፡
ከሰባ ሁለቱ አርድዕት አንዱ የሆነው ቅዱስ ሉቃስም ወንጌሉን ሲጽፍ በሕይወቷ ውስጥ የተፈጸሙ እርሷ ብቻ የምታውቃቸውንና ብቻዋን ሆና የሰማቻቸውን እንደ ብሥራት ያሉ ታሪኮችን በመንገር እረድታዋለች፡፡ ቀዳሜ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስ በቃልም በመጽሐፍም አይሁድን ተከራክሮ ድል ባደረጋቸው ጊዜ፣ ተቆጥተው ድንጋይ ሲያነሡበትና ሲከቡት ከሩቅ በማየቷ የሰማዕትነት ሥራውን በጽናት ይፈጽም ዘንድ በጸሎቷ እንዳበረታችው በጥንታውያን የታሪክ መዛግብት ሰፍሮ እናገኛለን፡፡
እመቤታችንን የማየት ዕድል ካገኙት አንዱ የሆነው ቅዱስ ዲዮናስዮስ ዘአርዮስፋጎስ እርሷን ባየ ጊዜ ሐዋርያቱ ሰው መሆኗን ባይነግሩት ኖሮ አምላክ መስላው እንደ ነበር ጽፏል፡፡ የፊቷን ደም ግባትና ሰላም፣ በእርሷም ላይ ይንጸባረቅ የነበረውን የቅድስና ብርሃን አይቶ በልጇ የማያምን እንደ ሌለም መስክሯል፡፡ የቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ ደቀ መዝሙርና የአንጾኪያ ሊቀ ጳጳስ የነበረው ቅዱስ አግናጥዮስም ለመምህሩ (ቅዱስ ዮሐንስ) በላከለት መልእክት፣ ክርስቲያኖች በሚሳደዱበት በዚያ ዘመን የእግዚአብሔር እናቱ እመቤታችን በስደቱ ደስተኛ እንደ ሆነች፣ በመከራዎችም ውስጥ ሆና እንደማታጉረመርምና እርሷንም ይነቅፉ በነበሩ ሰዎች እንዳልተቆጣች ይናገራል፡፡
እመቤታችን በልጇ ሕይወት ውስጥ ወሳኝ ታሪኮች የተፈጸሙባቸውን ስፍራዎች መጎብኘት ትወድ ነበር፡፡ የልደቱን ነገር፣ የእረኞችና የመላክቱን ዝማሬ፣ የጥበበኞቹን ስጦታ አስባ ቤተልሔም ትሄዳለች፡፡ ከሁሉም በላይ ግን መከራ ወደ ተቀበለበት ስፍራ መሄድ ታዘወትራለች፡፡ በዚያም የተቀበላቸውን ሕማማት፣ የደረሰበትን ተዋርዶ እና መከዳቱን እያሰበች ታነባለች፡፡ ‹ይህ ልጄ የተገረፈበት፣ ይህ የእሾህ አክሊል የተቀዳጀበት፣ ይህ ደግሞ መስቀል ተሸክሞ የሄደበት፣ ይህ የተሰቀለበት ነው› ትላለች፡፡ ወደ መቃብሩ ስፍራ ስትመጣ ግን በልዩ ደስታ እየተሞላች ‹‹ይህ በሦስተኛው ቀን ከሞት የተነሣበት ቦታ ነው›› ትል ነበር፡፡
በተሰጣት ቃል ኪዳን እኛ ኃጥአን የሆንን ልጆቿን ታስምረን!
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
[email protected]
አዲስ አበባ
መድኃኔዓለም ክርስቶስ በቅዱስ መስቀሉ ላይ ባፈሰሰው ክቡር ደሙ የመሠረታትን ቤተ ክርስቲያን ለሐዋርያቱ አደራ ሰጥቷል፡፡ በመጀመሪያው ምዕት ዓመት በነበረው የቤተ ክርስቲያን ሕይወት ውስጥ የጌታ እናቱ እመቤታችን የነበራት ድርሻ ትልቅ ነበር፡፡ ከክርስቶስ ዕርገት በኋላ እመቤታችን በሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ ቤት ሳለች፣ የሐዲስ ኪዳኗ ቤተ ክርስቲያን ራስ እና ፈጻሚ የሆነው ክርስቶስ የተገኘባትን እርሷን ለማየት ከሁሉም የዓለም ክፍላት የሚመጡ ሰዎች ብዙ ነበሩ፡፡ ድንግልም ወደ እርሷ የመጡትን ሁሉ እየባረከች፣ ያዘኑትንም እያጽናናች፣ በንስሓ ሕይወት እንዲኖሩ በመምከር ተስፋና ደስታን እየሞላች ትሸኛቸው ነበር፡፡ በርግጥም እግዚአብሔር ሰው ሆኖ በምድር ላይ ለመገለጡ፣ እንደ ሕፃናት ጥቂት በጥቂት ለማደጉና በመጨረሻም ለፈጸመው የቤዛነት ሥራው ሁሉ እናቱና አገልጋዩ ከምትሆን ከእመቤታችን የበለጠ ምስክር ከየት ሊመጣ? እርሷን ለማየት ባይጓጉ ነበር የሚደንቀን፡፡
ከሰባ ሁለቱ አርድዕት አንዱ የሆነው ቅዱስ ሉቃስም ወንጌሉን ሲጽፍ በሕይወቷ ውስጥ የተፈጸሙ እርሷ ብቻ የምታውቃቸውንና ብቻዋን ሆና የሰማቻቸውን እንደ ብሥራት ያሉ ታሪኮችን በመንገር እረድታዋለች፡፡ ቀዳሜ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስ በቃልም በመጽሐፍም አይሁድን ተከራክሮ ድል ባደረጋቸው ጊዜ፣ ተቆጥተው ድንጋይ ሲያነሡበትና ሲከቡት ከሩቅ በማየቷ የሰማዕትነት ሥራውን በጽናት ይፈጽም ዘንድ በጸሎቷ እንዳበረታችው በጥንታውያን የታሪክ መዛግብት ሰፍሮ እናገኛለን፡፡
እመቤታችንን የማየት ዕድል ካገኙት አንዱ የሆነው ቅዱስ ዲዮናስዮስ ዘአርዮስፋጎስ እርሷን ባየ ጊዜ ሐዋርያቱ ሰው መሆኗን ባይነግሩት ኖሮ አምላክ መስላው እንደ ነበር ጽፏል፡፡ የፊቷን ደም ግባትና ሰላም፣ በእርሷም ላይ ይንጸባረቅ የነበረውን የቅድስና ብርሃን አይቶ በልጇ የማያምን እንደ ሌለም መስክሯል፡፡ የቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ ደቀ መዝሙርና የአንጾኪያ ሊቀ ጳጳስ የነበረው ቅዱስ አግናጥዮስም ለመምህሩ (ቅዱስ ዮሐንስ) በላከለት መልእክት፣ ክርስቲያኖች በሚሳደዱበት በዚያ ዘመን የእግዚአብሔር እናቱ እመቤታችን በስደቱ ደስተኛ እንደ ሆነች፣ በመከራዎችም ውስጥ ሆና እንደማታጉረመርምና እርሷንም ይነቅፉ በነበሩ ሰዎች እንዳልተቆጣች ይናገራል፡፡
እመቤታችን በልጇ ሕይወት ውስጥ ወሳኝ ታሪኮች የተፈጸሙባቸውን ስፍራዎች መጎብኘት ትወድ ነበር፡፡ የልደቱን ነገር፣ የእረኞችና የመላክቱን ዝማሬ፣ የጥበበኞቹን ስጦታ አስባ ቤተልሔም ትሄዳለች፡፡ ከሁሉም በላይ ግን መከራ ወደ ተቀበለበት ስፍራ መሄድ ታዘወትራለች፡፡ በዚያም የተቀበላቸውን ሕማማት፣ የደረሰበትን ተዋርዶ እና መከዳቱን እያሰበች ታነባለች፡፡ ‹ይህ ልጄ የተገረፈበት፣ ይህ የእሾህ አክሊል የተቀዳጀበት፣ ይህ ደግሞ መስቀል ተሸክሞ የሄደበት፣ ይህ የተሰቀለበት ነው› ትላለች፡፡ ወደ መቃብሩ ስፍራ ስትመጣ ግን በልዩ ደስታ እየተሞላች ‹‹ይህ በሦስተኛው ቀን ከሞት የተነሣበት ቦታ ነው›› ትል ነበር፡፡
በተሰጣት ቃል ኪዳን እኛ ኃጥአን የሆንን ልጆቿን ታስምረን!
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
[email protected]
አዲስ አበባ
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
እግዚአብሔር አሕዛብ ያለ ሐዋርያት ስብከት በሥላሴ ማመን እንደማይችሉ፣ ሐዋርያትም ያለ መንፈስ ቅዱስ መውረድ በየአገሩ ቋንቋዎች ሁሉ መስበክ እንደማይችሉ ዐወቀ፡፡ ስለዚህም በሰናዖር ሜዳ የተበተኑትን የዓለምን ቋንቋዎች በሐዋርያት አንደበት ሰብስቦ ያኖር ዘንድ ቅዱስ መንፈሱን ላከ፡፡ የተላከውም መንፈስ ያለ አንድ ቋንቋ የማይናገረውን የሐዋርያቱን አንደበት በቅጽበት አሰለጠነው። በእውነት እንደ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ያለ አስማሪ ማን ነው?!በዚህችም እለት ሐዋርያቱ በዓለም ሁሉ ቋንቋዎች ተሞልተው ከእርሷ የወጡባት የጽዮን አዳራሽ (ጽርሐ ጽዮን) እንደ ምን ያለች ናት?! መንፈስ ቅዱስ ከዚያም በፊት ከዚያም በኋላ ታይታ የማትታወቅ ልዩ ትምህርት ቤት አደረጋት፡፡
ሐዋርያቱም በመንፈስ ቅዱስ ተሟሙቀው በሰበኩት በመጀመሪያ ዕለት ስበከት ብዙዎችን አሳምነው አጠመቁ። በዚህ የመከር በዓል አይሁድ ከአዲሱ እህል ለእግዚአብሔር ቁርባን ሲያቀርቡ፣ ሐዋርያቱ ግን የክርስቶስ አካል ለሆነችው ለሐዲሲቷ ቤተ ክርስቲያን ከእህል ቁርባን ይልቅ የሚወደዱ ምእመናንን ስጦታ አድርገው አቀረቡ። በአይሁድ የመከር በዓል ቀን በሐዋርያቱ በተሰጠ ትምህርት የእግዚአብሔር እርሻ የሆኑ ምዕመናን በዝተው አብበው ተገኙ። እውነትም የመከር በዓል!!!
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
[email protected]
ሐዋርያቱም በመንፈስ ቅዱስ ተሟሙቀው በሰበኩት በመጀመሪያ ዕለት ስበከት ብዙዎችን አሳምነው አጠመቁ። በዚህ የመከር በዓል አይሁድ ከአዲሱ እህል ለእግዚአብሔር ቁርባን ሲያቀርቡ፣ ሐዋርያቱ ግን የክርስቶስ አካል ለሆነችው ለሐዲሲቷ ቤተ ክርስቲያን ከእህል ቁርባን ይልቅ የሚወደዱ ምእመናንን ስጦታ አድርገው አቀረቡ። በአይሁድ የመከር በዓል ቀን በሐዋርያቱ በተሰጠ ትምህርት የእግዚአብሔር እርሻ የሆኑ ምዕመናን በዝተው አብበው ተገኙ። እውነትም የመከር በዓል!!!
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
[email protected]
አዳም "አትብላ" ለሚለው የመጀመሪያ ድምጽ ቢታዘዝ ኖሮ፣ "አፈር ነህና፥ ወደ አፈርም ትመለሳለህ" የሚለውን ሁለተኛውን ድምጽ ባልሰማ ነበር።
"ነገ እንሞታለንና እንብላ እንጠጣ" የሚለውን የዐሣማ ፍልስፍና (pig philosophy) እንተው።
"ነገ እንሞታለንና እንጹም!"
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
[email protected]
"ነገ እንሞታለንና እንብላ እንጠጣ" የሚለውን የዐሣማ ፍልስፍና (pig philosophy) እንተው።
"ነገ እንሞታለንና እንጹም!"
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
[email protected]
በመንገድ እየሄድህ ሳለ በድልድይ ስር ስታልፍ ድንገት ከላይ የሚንጠባጠብ የቆሸሸ ውኃ ቢነካህ ሁኔታው ሊያናድድህ ይችላል። ነገር ግን ያ ቦታ እንደሚያፈስ እያወቅህ ተመላልሰህበት ከበሰበስህ ግን ጥፋቱ የአንተ እንጂ የማንም አይደለም። ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንደሚለው አንዳንዴ ልክ እንደዚያ ጠብታ ሰይጣን ወደ ኅሊናህ ሊያስገባ የሚሞክረው ነፍስህን የሚያቆሽሽ ክፉ ሐሳብ ይኖራል። አንዴ የነካህ ክፉ ሐሳብ ግን ተመላልሶ እንዲያቆሽሽህ ከፈቀድህ ተወቃሹ አንተ እንጂ ሰይጣን አይሆንም።
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
“ለዘላለም የሚኖር ስሙም ቅዱስ የሆነ፥ ከፍ ያለው ልዑል እንዲህ ይላል፦ የተዋረዱትን ሰዎች መንፈስ ሕያው አደርግ ዘንድ፥ የተቀጠቀጠውንም ልብ ሕያው አደርግ ዘንድ፥ የተቀጠቀጠና የተዋረደ መንፈስ ካለው ጋር በከፍታና በተቀደሰ ስፍራ እቀመጣለሁ”
ኢሳይያስ 57:15
ኢሳይያስ 57:15
HTML Embed Code: