ሐዋርያዊ መልሶች | United States America (US)
Create: Update:
ዛሬ ቅዳሴ ላይ ከተነበበው የቅዱስ ወንጌል ክፍል:
“እኔ እሄዳለሁ ወደ እናንተም እመጣለሁ እንዳልኋችሁ ሰማችሁ። የምትወዱኝስ ብትሆኑ ከእኔ አብ ይበልጣልና ወደ አብ በመሄዴ ደስ ባላችሁ ነበር።”
[ዮሐንስ 14: 28]
2 ነጥቦችን እናስቀምጥ
1️⃣ ጌታችን ኢየሱስ እኔ ወደ አብ እሄዳለሁ ወደ እናንተም እመጣለሁ አለ.. የምር ግን ጌታ ወደ አብ ሄደ..?? በሚገባ ጌታችን ከሙታን ተለይቶ ተነሥቶ በሥጋ በክብር አረገ በአባቱ ቀኝም ተቀመጠ.. ስለዚህም ቃሉን ጠብቋል.. እንዳለውም ወደ አባቱ ሄዷል..
ይህንን ቃሉን ከጠበቀ ደግሞ ቀጣይ የተናገረውንም እንደሚፈጽም እርግጠኞች ነን ይህም “ወደ እናንተም እመጣለሁ” ያለውን ነው.. ጌታ ኢየሱስ መሄድ ብቻ ሳይሆን ተመልሶም ደግሞ ይመጣል.. ከዛም ይወስደንና ሁል ጊዜ ከእርሱ ጋር እንኖራለን: “ስለዚህ እርስ በእርሳችሁ በዚህ ቃል ተጽናኑ”(1ተሰ 4:17)
2️⃣”ከእኔ አብ ይበልጣል” አለ.. ለዚህ ብዙ ማብራሪያዎች ይሰጣሉ.. ጌታችን አምላክ እንደመሆኑ ከአብ በባህሪው በምንም ባያንስም ሰው እንደመሆኑ ግን ምንም እንኳን አምላክነቱን ባያጎድለውም ህልውናው የጀመረ ወይም የተፈጠረ ሥጋን ነው የተዋሐደውና ሲሞትም ሲደክምም ሲራብ ሲጠማም በዚሁ በሥጋው ነውና ይህ ነገር በአብ ዘንድ ስለሌለ እሱን ለማስረዳት ነው ተብሎ ይፈታል.. ሌሎች ማብራሪያዎችም አሉት ይህ ይበቃል ለጊዜው..
መልካም የጌታ ቀን
@Apostolic_Answers